1 125
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+27 أيام
-4830 أيام
أرشيف المشاركات
1 125
🍃የማለዳ ውብ ስንቅ🍃
فذكر إنما أنت مذکر
21:አስታውስም፤አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና።
እኔም ማስታወስ ወደድኩኝ
ረቡዕ 4/13/2018
✨መልካም ቀን✨
1 125
♻️የምሽት ውብ ስንቅ♻️
ኢማም ኢብኑል ጀውዚ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ፦
አንተ የኃጢአት ምርኮኛ ሆይ! ላለፈው ኃጢአትህ አልቅስ።ከኃጢአትህ ሳትመለስ ሞት ከመጣህ ወዮውልህ።ለተውበትም ጥሪ ተደርጎለት ምላሹን ያልሰጠ ሰው ዋ! ኪሳራው።ሳትዘጋጅ ወደ መጨረሻዋ ሃገር በሞት በተጠራህ ጊዜ እንዴት ትሆነው ይሆን? አንተ ትልቅ ኃጢአትን የሠራህና ሕጉን ያላከበርክ ሰው አይደለህምን? ሚዛኑ ላይ በተቀመጠ ጊዜ ሚዛኑን የሚደፋ አንኳር መልካም ሥራ አለህን? ተግባርህ ቅርፊት እንጂ አንኳር አይደለም፣ ሚዛኑን የሚደፋው ደግሞ ቅርፊቱ ሳይሆን አንኳሩ ነውና።አንተ የአደም ልጅ ሆይ! ከቸልተኝነት የበለጠ ከባድ እንቅልፍ የለም፣ ከስሜታዊነት የበለጠ ባርነት የለም፣ከልብ ሞት የበለጠ አደጋ የለም፣ ከግራጫው ሽበት የበለጠ አንደበተ ርቱዕ ማስጠንቀቂያ የለምና ንቃ!። ኃጢአተኛው በተውበት ክብር ውስጥ ይግባ፣ ጎህ በቀደደም ጊዜ ምላሽ የሚያገኝበትን በር ያንኳኳ።እውነተኛ ሙኽሊስ የሆነም ሰው በሩን አንኳኩቶ ባዶውን አይመለስምና። የተጠራ ሰው እንዴት በባዶው ይመለሳል? ዋናው ጉዳይ በእውነተኛ ተውበት ውስጥ መሆንህ ነውና ንቃ!።
📚ابن الجوزي | الفوائد
ማክሰኞ 3/13/2018
💐የብስራት ለይል ተመኘሁላችሁ💐
1 125
☆Anahira☆
🎀 ክፍል 25
ፊቷን አስተካክላ በሩን ስትከፍተው ኢነብ ነው በጣም ደነገጠች
<<እ……?>> አለችው በመመናጨቅ ይሁን? በድንጋጤም
<<ሰዓትሽን አገኘሁት ይኸው>>
ብሎ የጣለችበትን በመንገር ሰጣት አመስግና ተቀብላው በሩ ዘጋችው እና መነፋረቅ ጀመረች ለምን እንዲህ እንደምትሆን? ለምን እሱን እንደወደደችው በራሱ ራሷን ብትጠይቅ መልስ አጣችለት ከምንም በላይ የሌላ ሰው መሆኑ አመማት በራሷ ሚዛን ላይ ራሷን ስትመዝን ቀለለባት ከደቂቃዎች በፊት እኮ ክፍሉ የሄደችው እንደምታያቸው የholiwood ፊልሞች ሌላ ታሪክ ልትፈጥር ነበር ቆይታ አደብ ገዛች እንጂ ፈጠረኝ ብላ የምታምነውን አምላክ ፈራችው የአቢ ቃል ታወሳት ኢነብ በራሱ ትዝ አላት እውነት ድንገት የመጣላትን ብታደርግ በእድሜው አይኗን አያያትም ነበር ከማንም ይቅርታን አታገኝም መልሳ ምንም አለማድረጓ ትንሽም ቢሆን አረጋጋት
ኒሳዕን ተሰንስብቼ ወደ ክፍላችን ስሄድ አትሮን ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወስዷታል ልቀሰቅሳት አስቤ አሳዘነቺኝ ፊቷም ልክ አልነበረም ቆይ ምን ሆና ይሁን? አልኩ በልቤ እንደውም እጠይቃታለሁ እኔ ስሆን ብቻ ምን እንደሆንኩ እየጠየቀቺኝ እሷን ዝም ማለት የለብኝም የሆነችውን እንደማትነግረኝ አውቃለሁ ግን ቢያንስ ፍንጭ አገኛለሁ ብዬ ስላሰብኩ ቀሰቀስኳት
<<አትሮን?………አትሮኖስ?……ተኛሽ እንዴ? ነቃ በይ ገና እኮ ነው>> እያልኩ ትከሻዋ አካባቢ ስነካት
<<ኢ……ነብ>>ብላ ባነነች ዘወር ብላ አይታኝ መልሳ ድንጋጤ በሚመስል መልኩ እያየቺኝ
<<ቅዥት መሰለኝ>> አለቺኝ ምንድነው ብዬ እንኳን እኮ አልጠየቅኳትም
<<አይዞሽ ተረጋጊ>> አልኳት ሲከፋት መጥፎ ስሜት ውስጥ ስትሆን ትቃዣለች አቅፌ ብቻ አረጋጋኋት
<<ምነው? ከፍቶሻል እንዴ? እመጣለሁ ብለሽን እኮ በዛው ቀረሽ!>>አልኳት እሷም በረጅሙ እየተነፈሰች
<<ሆኛለሁ መሆን እንደሌለብኝማ ሆኛለሁ ግን ደግሞ አልነግርሽም ማለት መፍትሔ ቢኖረው እነግርሽ ነበር ግን ስለሌለው አልነግርሽም>>
<<እንፈልግለታለና ንገሪኝ?……… ምን ችግር አለው?>>
<<በቃ የምሰራበት ቦታ ላይ ከአለቃዬ ፍቅር ያዘኝ እሱ ደግሞ ባለትዳር ነው አየሽ ይሄ ምን አይነት መፍትሔ ይኖረዋል?>> አለቺኝ በጣም ደነገጥኩ እና
<<እኔንጃ አትሮን እኔ አላውቅም ግን እንዴት?>> ስላት ከት ብላ እየሳቀች
<<ኧረ……እኔ ስቀልድ ነው ማለት በአጭሩ ሊይዘኝ ከማይገባ ሰው ነው ፍቅር የያዘኝ>>
<<አውቀዋለሁ ማለት የማይገባ ሰውስ እንዴት ልትዪው ቻልሽ?>>
<<ታውቂዋለሽ መሰለኝ የማይገባ ሰው ያልኩት ደግሞ ያው እምነታችን ተመሳሳይ አይደለም ሲቀጥል ቤተሰቦቹ ይህን ላይወዱት ይችላሉ አባቱ ቢያዝብኝስ? ልጁን ለብዙ ነገር እየጠበቀው እኔ መጥቼ ነገሮቹን ሳበላሻቸው አሰብሽው? ቢያንስ እሱ እንኳን የሚፈልገኝ ቢሆን ምንም አልነበረም ግን አይወደኝም በቃ ትንሽ ገመድ ነው ያለው በጣም ትንሽ እሱንም እኔ ያለኝ ስሜት ብቻ ይመስለኛል>>
<<እሺ ማን እንደሆነ ንገሪኝ እና መፍትሄ እንፈልግለት ግድ የለሽም ንገሪኝ?>>
<<አንቺ ብዙም አታውቂውም በምልክት ከምነግርሽ ደግሞ አንድ ቀን ከርቀትም ቢሆን ባሳይሽ አይሻልም?>>
<<እሺ የት ነው የሚኖረው?>>
<<እዚሁ አ-አ ውስጥ>>
<<ግን እንዴት ወደድሽው?>>
<<የሚረታ ስብዕና አለው እምነቱ ላይ ጥሩ ነው መልክ አለው ፀባይ 100% ወንድም የሚሆነኝ ይመስለኛል እሺ ቢለኝ ብቸኝነቴን እንዳላስብ የሚያደርግ ሰፊ ቤተሰብ አለው ከዚህ በላይ ምን ያስፈልገኛል?>>
<<ምንም ግን መላዒካ አደረግሽው አንቺ በህይወትሽ ውስጥ የፈለግሻቸውን ነገሮችን ሁሉ መያዙ ይገርማል እሺ ስንት አመቱ ነው?>>
<<እኩያዬ ነው ምናልባት የወራት ልዩነት ቢኖረን ነው>>
እንደመደንገጥም እንዳለማመንም ድምፄ እየተሰላ
<<አትሮን ስለኢነብ ነው እንዴ የምናወራው? እንደማይሆንም ታውቂያለሽ አይደል?>> አልኳት ኧረ በሚል መልኩ ፈገግ ብላ
<<ነዚፍ ይባላል ስሙን አስቀድመሽ ሳልጠየቅሺኝ ነው>> አለቺኝ ያን ጊዜ ተረጋጋሁ
<<እሺ አሁን ደግሞ ስለቤተሰቦቹ አንዳንድ ነገር በዪኝ>> ስላት ከአልጋው ብድግ ብላ
<<በቃ ይበቃናል ተነሺ ይህን ነገር እዚህ ጋር እንዝጋው……ለመነሳት እርዳታዬን ትፈልጊያለሽ?>> አለቺኝ ባልኳት ነገር ደስ የተሰኘች አትመስልም እሺ ብያት ተነሳሁ እሷም ፊቷን ተጣጥባ ልንወጣ ስንል ኢነብ አስቆመን እኔን ሳይሆን እሷን ነበር የጠራት ዞረች
<<አቤት ኢነብ ምነው? ፈለግከኝ?>>
<<አይ ሳይሆን……>> ወደእሷ ከደረሰ በኋላ
<<ቅድም ካየሁት ፊትሽ ብሶበታል omega 3 ነው እንኪ ምናልባት እንዲስተካከል ይረዳው ይሆናል>> አላት ደስ እያላት ተቀበልችው እና ወደ እኔ እየመጣች
<<ፊቴ የዚህን ያህል ያስታውቃል ማለት ነው? ሰሞኑን ጥሩ እንቅልፍ የለኝም ለዛም ይመስለኛል እንደዚህ እየሆነ ያለው>> አለቺኝ
<<አዎ እንደበፊቱ ጥርት አላለም ጭንቀት ምናምን እንደዚህ ያደርጋል ይላሉ ኢነብን ደግሞ ታውቂዋለሽ ያለምክንያት የሚጨነቅ ሰው ስለሆነ እንደዚህ አይነት የፊት መድሃኒቶችን አያጣም>> አልኳት እና የተደወለለት ታክሲ መጥቶ ስለነበር ተያይዘን ገባን
የአትሮን ነገር ግራ ይገባል ምን እየሆነች እንደሆነ ለማወቅም በጣም ይከብዳል ቤት ከደረስን በኋላ ትንሽ አጫውታኝ ሄደች ቤቱ አስጠልቷታል በየጊዜው ስለ ኒሳዕ ብቻ ነው የሚወራው በቃ ደብሯታል በመንገዷ ካገኘችው አንድ ካፌ ለማምሸት አሰበች እና ወደ እዛ ካፌ ገባች
ካፌ ይሁን እንጂ የspain ባህላዊ ምሽት ቤት ነው በህይወቷ ምሽት ቤት ምን እንደሆነ አታውቅም ዛሬን ግን ከወደ ጥግ የተደረደሩት መጠጦች ይወሰውሷት ይዘዋል በአንድ በኩል ፍርሃት እንዳልሆነች እያደረጋት ነው ጠጥቼ ቤት ብገባ ምን ይሉኝ ይሁን? በሌላ በኩል ደግሞ እምነታቸውን እኔ ላይ እንዲንፀባረቅ ማስገደድ አይችሉም እኔ እኔን ነኝ እነሱም እነሱን
<<ወንድም አንድ ትሰጠኝ?>>
<<ምን ልስጥሽ?>> አላት ስሙን አታውቀው ነገር ሆኖ ተቸግራለች
<<አንዱን ዝም ብለህ አንዱን ስጠኝ>> ውድ የሚለውን መጠጥ ከፍቶ በብርጭቆ አንቆረቆረላት አንድ ጊዜ ቀመሰችው ምላሷን አቃጠላት ምናልባት እሾህ የበቀለበትን ያህል ከደቂቃዎች በኋላ ግን ምላሷ ያንን ፈተና ለምዶት በደንብ መጠጣት ያዘች በዚህ መሃል ስልኳ ጠራ
አይኗን ጭፍን ግልጥ እያደረገች የደዋዩን ማንነት ለማወቅ ሞከረች
"ኢነብ" ይላል በድጋሚ ሲጮህ አነሳችው
15🥰
ይቀጥላል☆ ☆ ☆ . . . . .
1 125
🍃የማለዳ ውብ ስንቅ🍃
ውብ ጣፋጭ ቲላዋህ
ቀልብን የሚማርክ ልብን የሚያሰክን
ከአሏህ ቃል ውጭ ከቶ ምን ይገኝ ይሆን?!
ማክሰኞ 3/13/2018
✨መልካም ቀን✨
1 125
☆Anahira☆
🎀 ክፍል 24
☆<<ስሚኝ ነገ አልረሳም አሁን ግን ብርድ ነው በአላህ ስሚኝ እሺ በዪኝ ወደ ቤት እንሂድ?>>
<<አልፈልግም አንተ ሂድ>>
<<ኧረ አታስቂኝ ያላንቺ እዛ ቤት ምን ልሆን ነው የምሄደው?……ወይ>>
<<ወይ ምን?¿!>>
<<ወይ ኡሚዬ ጋር እንሂድ እንዴ? የመጠበቅ አቅም ካለሽ ዛሬን እዛ እንደር እና እሷ ትስራልሽ ያው ማስቸገር ቢሆንብንም>>
<<እሱማ ጥሩ ሃሳብ ነው በቃ እንሂዳ>>
<<እሺ ቀስ እያልሽ ቆይ እጅሽን ስጪኝ እና ቀስ ብለሽ ተነሺ አዎ እንደዛ>>
እጄን ይዞ አነሳኝ እና በድጋሚ ወደ መኪናው ገባን ብዙም ሳንቆይ ነበር የደረስነው ገና እራት ለመብላት እየተዘጋጁ ነበር ስንደርስ በደስታ ተቀበሉን
<<ኡሚዬ አዚዛ ባቅላባ አምሯት እንዳመጣላት ነግራኝ ረሳሁት እና እስኪ ልታዘጋጂላት ትችያለሽ?……አውፍ በይን ግን በምሽት መጥተን…>>
<<ኧረ አብሽር አትጨነቅ የኔ ልጅ አሁን አዘጋጅላታለሁ እናንተ ከደከማችሁ አረፍ በሉ>>
አለችን ከአትሮን ጋር ለማውራት ባስብም ፊቷ ላይ ጥሩ ነገር ስላላየሁ ዝም አልኳት እና ከኢርቫ ጋር አንድ መኝታ ክፍል ተስተካክሎልን ገባን ወዲያው ልብስ ቀይሮ ሲወጣ
<<ወደ የት ነህ?>> አልኩት
<<ኡሚዬን ላግዛት ነው ትንሽ አግዣት እመጣለሁ>> ብሎኝ ሄደ
ሰዓቱ እየሄደም ብቻ ሳይሆን እየሮጠ ነው ማለት ይቀላል ባይ ብጠብቅ ማንም ባቅላባውን ሳያመጣ ቀረ የጠበቅኩትበት ጊዜ ዘመናት መሰለኝ እንቅልፍ ይዞኝ ሄደ ከደቂቃዎች በኋላ ኢርቫ ሲመጣ አልሃምዱሊላህ እንቅልፍን ለፈጠረ ጌታ የለሁም ንጋት ላይ ትንሽ ትንሽ ትዝ ይለኛል ሲቀሰቅሰኝ
እንደማልፈልግ ነገርኩት እንድነሳ ቢጠይቀኝም እንኳን እንዳልፈለግኩ በቃ መከራውን አይቶ በመጨረሻ ሰዓት እሱም ተኛ
ንጋት ነው የንጋት ሷላትም አዛን ከእያንዳንዱ የእጅ ስልክ ይደመጣል ቀድሜው ነቅቼ ስለነበር በወገቤ ላይ ያሳረፈውን እጁን እያነሳሁ ትራሱን አቃንቼ ተቀመጥኩ ትንሽ ከተረጋጋሁ በኋላ ቀሰቀስኩት
<<ስማኝ እንጂ………ኢርቫ>>
<<ነዓም ምነው?>> እሱም ተነስቶ ለመቀመጥ ይመቻቻል
<<ባቅላባውስ? ብቻህን በላኸው?>> አፍንጫዬ እነፋነፋል
<<ኧረ አልበላሁም ብሳሳት ብሳሳት እንደዚህ አይነት ስህተት እሳሳላታለሁ?……… ይኸው እዛ ጋር አለ ማታ ስቀሰቅስሽ ጊዜ እንቢ አልሺኝ ቆይ ላምጣልሽ?>>
<<አይ ሳይሆን እየሸተተኝ ነው>>
<<እኮ እዤልሽ ልምጣ>>
እየሮጥኩ ትቼው መታጠቢያ ቤት ተዘረርኩ ከዛ ቀፋፊ የማስመለስ ድምፆች ይስተጋባሉ ኢርቫ እሱ ያስቸገርኩትን ግን ማንን አስቸግር ነበር? ከደቂቃዎች በኋላ ተረጋግቼ እንደዛ በስቃይ ያሰራሁትንም ባቅላባ ሳልበላ ቀረሁ
<<ቆይ ግን ምን አይነት ልጅ ቢሆን ነው እንደዚህ ገና በ4 ወሩ የሚያሰቃይሽ የሚቀሩትን 5 ወራት አሰብሻቸው?>> ለቁርስ ቀርበን ኢነብ ነበር ይህን ያለው
<<እኔ ምን አውቄ አንዳንድ ሌሊት ስንቆራጠጥ አድራለሁ መኝታ የለኝም አንዳንድ ጊዜ ይኸው እንደምታዩት ቃር ነው ብቻ አላህ በሰላም ይገላግለኝ>>
<<(ኢነብ):-አሚን ፣(ኢርቫ):- አሚን ፣(አትሮኖስ):- አሜን>> አሉኝ እና መመገብ ቀጠልን የቁርሱ መርሃ ግብር እንደተጠናቀቀ ኢርቫ
<<አትሮን ዛሬ ስራ ካልገባሽ ሚናሃን ቤት እንድታደርሺልኝ እ……በዚህ ትተባበሪኛለሽ? አሁን ከወሰድኳት ቀኑን ሙሉ ብቻዋን መዋሏ ጥሩ አይደለም ብዬ ነው>> አላት
<<ችግር የለም አታስብ ወደ አስር ሰዓት አካባቢ አመጣታለሁ እስከዛ ድረስ እዚህ ትውላለች>> አለችው አመስግኗት ሊወጣ አለ እና ተመልሶ መጥቶ
<<አዚዘቲ ምንም ነገር ከፈለግሽ እኔ ስመጣ ትጠይቂኛለሽ ኡሚዬን ግን እንዳታስቸግሪያት እሺ አደራሽን እኔ ስመጣ የፈለግሽውን አደርግልሻለው እሷን ግን እንዳታስቸግሪ ተግባባን?>>
<<አዎ ተግባብተናል>> አልኩት እና ተቃቅፈን ተለያየን ከዛ ከአትሮን እና እናቴ ከአያቴም ጋር ውሎውን አሊፍ ብለን ጀመርን በጣም ደስ ይል ነበር ረፋዱ ላይ መምጣቴን ሰምታ ኒሳዕ ወደ ቤታችን ጎራ አለች ኢነብ የለም ስራ ነው እሷም እሱን ፈላጊ ትመስላለች ያው ፍላጎታቸውን ገሃድ አውጥቶ ሸሪዓዊ ባል እና ሚስት ብሎ የሚሰይማቸው አካል ነው ያጡት አብዛኛውን ነገር ያወራችው ስለ አቢ አለመመለስ ነው ቶሎ አለመምጣቱ ከንክኗታል ኒቃቧን ወደ ኋላ ለመገለጥ ከምራዋለች በክብ ፊቷ ላይ እንደ ኮከብ የተጣሉት ሁለት አይኖቿ አጂብ ያስብላሉ ጥርሷ የተሰደረ ምንም እንከን የሌለው ነው
አትሮን የሰራችልኝን የስጋ ሾርባ 🍜ይዛ ስትመጣ ከኒሳዕ ጋር ሰላም ተባባሉ ኒሳዕ ሰፍ ብላ ብታናግራትም አትሮን ግን እንደዛ አልሆነችላትም ፍፁም ቁጥብ እና የተቀዛቀዘ ምላሽ ነበር የምትሰጣት ምን ሆነች? ሌላ ጊዜ ለሰው የነበራት ትህትና ልብ ያርዳል ዛሬን ደርሶ ትነጫናጭ እና ጅንን ባይ ለምን ያደርጋታል? አልኩ በልቤ ለኒሳዕም ሾርባ🍜 ይዛላት መጣች
ዛሬን ያለወትሮው ኢነብ በጊዜ ወደ ቤት መጥቷል ገና ከውጪ "አሰላሙ አለይኩም" የሚል ድምፅ ሲሰጥ ኒሳዕ ፊቱን ተሸፋፍና ተቀመጠች ከገባ በኋላ
<<…… ወአለይከሰላም ዛሬ እንዴት በጊዜ መጣህ?>> አልኩት ሁለቱም ሴቶች ምን እንደሆነ ለማወቅ ጆሮዋቸው እኩል ቆሟል
<<ያው ግምገማ እና የማስጎብኘት ስራ ነበር እሱን እንደጨረስኩ መጣሁ>> አለኝ
ኒሳዕ በኒቃሟ የአይን ክፍተት አሻግራ አየችው አትሮን ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ወደ እሱ ዞራ ነበር የተቀመጠችው ያቺ ቅጽበት እንኳን ኢነብን እንዳፈቀረችው ያስታውቅ ነበር የሚያስተውል ጠፋ እንጂ አይን አይኑን ታየዋለች
<<በቃ አረፍ ልበል>> ብሎ ተነስቶ ሲሄድ ኒሳዕን በአይኑ የጎንዮሽ አይቷት ሄደ አትሮን የማታውቀው እሳት እየገረፋት ዝም አቀረቀረች
<<አትሮን………አትሮን ኧረ የት ሄድሽ?>> ከብዙ ጥሪ በኋላ
<<የት ሄድኩ?>> አለቺኝ ምንም መልስ ስላልነበረኝ
<<ከኒሳዕ ጋር የያዝነውን ጨዋታ ምነው ችላ አልሽው?>>
<<አይ ብዙም ሃሳብ የምሰጥበት ጉዳይ ስላልነበረ ነው ቆይ አንድ ጊዜ ጠብቁኝ መጣሁ>> ብላን ተነሳች
ደረጃውን ወጥታ እንደጨረሰች ፊት ለፊት ወደ ምታገኘው ክፍል ከፍታ ገባች አዎ ያ ክፍል የኢነብ ክፍል ነው እሱ በሌለበት እንጂ እያለ ገብታ አታውቅም ማለትም ከሙኒራ ጋር የተተኮሱ ልብሶችን ሲያስገቡ የእሱንም ጀለቢያዎች ልታስቀምጥ ካልሆነ ዛሬን ግን ለምን እንደመጣች በራሱ ለራሷ አታውቅም ብቻ ስትደርስ እና ምን ታደርጊያለሽ ሲላት እንጂ
<<አትሮን አትሮን ውጪ እንጂ ምንድነው የምትጠብቂው? ይሄ እኮ የእኔ ክፍል ነው>> አላት አክሎ
<<ለምን መጣሽ አንድ ክፍል የመገኘታችንን ሃራምነት ላንቺ ማስረዳት አለብኝ እንዴ?>> አላት እሷም ይህን ሲል ድንገት የመጣላትን
<<ከትላንት ወዲያ ሰዓቴን እዚህ ልብስ ሳስተካክል የጣልኩት መሰለኝ ቁም ሳጥንህ ውስጥ እይልኝ?>> አለችው እውነት ስለመሰለው ሳጥኑን ከፍቶ ከካዝናው ውጪ ባለው ቦታ ሁሉ ፈለገላት በዚህ ጊዜ ከእጇ ላይ ፈትታ ጣለችው
<<አትሮን እዚህ የለም ወይ በኋላ መስጂድ ስሄድ ትፈልጊዋለሽ አሁን ግን ሂጂ እኔም ማረፍ እፈልጋለሁ አብረንም መሆን የለብንም>> አላት
1 125
♻️የምሽት ውብ ስንቅ♻️
አንዳንዴ ጥሩ ሰዎች ጋር በመሆናችን ምክንያት ደስተኛ እንሆናለን !
በተስፋቸው የደረቀ ልባችን ይለመልማል፣ በፍቅራቸው ብርሀን ጨለማችን ይገፈፋል፣ በመልካም አስተሳሰባቸው ያስደምሙናል።ስለነሱ ባሰብን ቁጥር ደስታ እና ተስፍ ከልባችን ይፈነጥቃሉ።የትም ቦታ ከነርሱ ጋር ብትሆን አይከፋህም፣ እንደ ኮኮብ መሪ ይሆኑሀል። ጭራሽ ባይደላህ ያሰብከው ሀጃ ባይሳካም፤ እነሱ አንተ ጋር ሰለሆኑ ብቻ የደስታ ጥግ እንዲሰማህ ያደርጉሀል!!!
እንደዚህ አይነት ምርጥ ሰዎችን ከጎናችን አላህ ያብዛልን።
ሰኞ 2/13/2018
💐የብስራት ለይል ተመኘሁላችሁ💐
1 125
ትዝታ ማለት...
➝ ትዝታ ማለት... ቁስሉ ዳነ ብለህ ካሰብክ በኋላ፣ በትንሽ የቃላት ጭረት እንደገና ደምቶ የሚያመህ እውነተኛው የልብ ጠባሳ ነው!💔
1 125
🍃የማለዳ ውብ ስንቅ🍃
መቼም የማይጠገብ የማይሰለች የማይለመድ ለአንደብትም ሆነ ለጆሮ ሁሌም አዲስ የሆነ እርሱ ቁርዓን ነው።ኑ በቁርዓን ቀልባችንን እናርጥባት
ሰኞ 2/13/2018
✨መልካም ቀን✨
1 125
☆Anahira☆
🎀 ክፍል 23
☆ጊዜያት ያለከልካይ መጓዝ ጀምረዋል
ᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔ
የመغሪብ ሷላት አዛን ሊል የእጅ ሰዓቷ ያዘግማል ከስራ እንደተመለሰች ዛሬ ያለወትሮው ኢነብ ቤት ቶሎ ተገኝቷል ቀርባ ልትጠይቀው ፈለገች ግን ደግሞ ስልክ እያናገረ ነው #አትሮኖስ
<<……ኢነብ ሳልረዳህ ቀርቼ እኮ አይደለም በስልክ እንደዚህ አይነት ነገር ብንጠይቅ ንቀት ይመስልብናል ነው እያልኩህ ያለሁት>>
<<እስከዛስ? እ……? እስከዛስ ድረስ ኒሳዕ ብታገባስ?>>
<<ኧህ…… እሱም ቢሆን ለኸይር ነው ምን ችግር አለው?>>
<<ሃ ሃ ሃ…… አቢ የእውነትም ጥሩ መካሪ ነህ ባጣትስ እኮ ነው ያልኩህ እንደ መንገደኛ ሳይሆን አንድ ጊዜ እንደ አባት አስብ እስኪ አንድ ጊዜ መጥተህ ጠይቅልኝ አቢ>>
<<እሺ የቀረኝ ሁለት ሳምንት ነው አሁን ወደ መስጂድ እየገባሁ ነው ……… ወሰላሟለይክ>> ምላሹን ሳይጠብቅ ጆሮው ላይ ዘጋበት
ኢነብ ተብከነከነ የሚያደርገውን አጣ ከተቀመጠበት የበረንዳ መጅሊስ ተነስቶ መንጎራደድ ጀመረ አትሮኖስ ወደ ቤት መግቢያው ላይ ጫማዋን እያወለቀች ሽቅብ አየችው እሱም
<<ጆሮዬ ላይ ዘጋው ዘጋው እኮ መጀመሪያም ይህ እንደሚሆን አውቄ ነበር ከመሄድህ በፊት አንድ ነገር አድርግ ብለው እመለሳለሁ ብሎ አዘናጋኝ አሁን ከሄደ በኋላ ደግሞ አልመጣ አለ>>
ዝም ብላ አየችው እና
<<ኡሚ የት ናት?>> አለችው የጠየቃት ሌላ መልስ የማይመስል ጥያቄዋ ሌላ ሲሆንበት እየተበሳጨ ቆም አለ እና ቁልቁል እያያት
<<አላ……አላውቅም ክፍሏ ትሆናለች>> አላት የእጅ ሰዓቷን ቃኝታ
<<አዛን ሊል ነው መስጂድ አትሄድም?>> አለችው ይህን ስትለው ትንሽ ተረጋጋ
<<እ……እሄዳለሁ…… እሄዳለሁ እንጂ>>አላት እና ወደ ውስጥ ገባ ሲሄድ በአይኗ ሸኘችው እና ተቀምጦበት ወደነበረበት መጅሊስ ሄዳ እየተቀመጠች
<<ኒሳዕ አህመድ ………የኢነብ ኒሳዕ ግን አትሮኖስስ?…………የኢነብ አቲካ መሆን አትችልም?>> አለች እና በቅርታ ፈገግ አለች ከግራ አይኗ አንድ የእንባ ዘለላ ተንሸራተተ ምን እንደሚሰማት አታውቅም ግን ስለኒሳዕ ቤት ውስጥ በተነሳ ቁጥር ልትቆጣጠረው የማትችለው የቅናት መንፈስ አለ እሱን ለመደበቅ ደግሞ ብዙ ትጥራለች እውነት ለኢነብ እንደዛ አይነት ስሜት አለኝ? ብላ ራሷን ትጠይቃለች
ሰሞኑን ደግሞ አንዳንድ የድሮ ትዝታዎች ስለኢነብ ብዙ ሃሳብ ይመላለስባታል በአንድ ወቅት ዳንኤል የተባለ የክፍላቸው ተማሪ የፍቅር ጥያቄ አቅርቦላት የሰጣትን ወረቀት አመድ አደረገው እሱንም አጠገቧ እንዳይደርስ አስፈራርቶት ነበር ያ አጋጣሚ ደግሞ አሁን እሷ ጋር ኒሳዕን ይወዳታል ከሚለው የቅናት መንፈስ ደርሶ ያረጋጋታል ከእዛ ክስተት በኋላ ወደ ቤት ሲገቡ እሱ ወደ ኋላ ቀርቶ አንድ ነገር አላት
<<አትሮን ምናልባት እንደጎዳሁሽ ከተሰማሽ ይቅርታ ይህ ነገር እናትሽንም ካስታወሰሽ በድጋሚ ይቅርታ ግን እናትሽን አትርሻት የእናትሽን ታሪክ አትርሽው አንቺ ገና ነሽ ህፃን ነሽ እያልኩ ሳይሆን ግን ለእንደዚህ አይነት ነገር አሁን ሰዓቱ ይመስልሻል? ለዳንኤል ትክክለኛውን ምላሽ ነው የሰጠሁት ለአቢ የእናትሽ አደራ ነሽ ለእኔ ደግሞ የአቢ አደራ ነሽ ስለዚህ ከሚንሃ ባልተናነሰ አንቺን የመጠበቅ ሃላፊነት አለብኝ እንደዛ ተረጂኝ እ……? እንደዛ ስላደረግኩት ቅር ብሎሻል?>> ፈገግ እያለች
<<አይ አ…ይ አላለኝም ስለዚህ ባለፈው በእኔ ምክንያት ስለመቀጣትህ ይቅርታ አድርገህልኛል ማለት ነው?>> አለችው
<<እምምም………መሰለኝ አሁን ብዙ አብረን መቆየት የለብንም ያው ሃራም ነው>> አላት የፈግታዋን አፀፋ በፈገግታ መልሶ ወደ ውስጥ ገባ
በምናቧ ካስታወሰችው በኋላ አሁንም ፈገግ አለች (ይወደኛል ግን አይወደኝም) ምን ማለት ነው ግን?………… አለች በልቧ
<<አትሮን ምነው ብቻሽን በጨለማ? በዛ ላይ በዚህ ብርድ? የበረንዳውን መብራት አታበሪም¿?>> ሙኒራ ደርሳ ጥያቄዎቿን ስታዘንብባት ከገባችበት አለም ብንን አለች እና
<<አ…… አሁን ገና መምጣቴ ነው ……እ ትንሽ ለማረፍ አስቤ>> አለቻት እየተንተባተበች እና የድንጋጤዋን ፈገግ እያለች ስስ እና ስርጉድ ጉንጮቿ ቀልተዋል
<<ደህና ነሽ? የእኔ ውድ ፊትሽ ልክ አይደለም እኮ>> አለቻት አትሮንም ተነስታ እየሳመቻት
<<ወደ ክፍሌ ልሂድ ኡሚዬ በቃ ልብሴንም ልቀይር>> አለቻት እና ሄደች ሙኒራ ግራ ገብቷታት
<<አተነፋፈሷ በራሱ እኮ ልክ አይደለም>> አለች ስትስማት የነበረውን የአተነፋፈሷን አለመረጋጋት እያሰበች የበረንዳውን እና በግቢው ውስጥ ባሉት ዛፎች ውስጥ የተጠለፉትን አምፑሎች መብራት አብርታ ስትገባ ከኢነብ ጋር ተገናኙ ወደ መስጂድ ለመሄድ እየወጣ ነበር
<<እ?…… አቢ ምን አለህ?>> አለችው
<<በቃ ገና ሁለት ሳምንት ይቀረኛል ነው እያለኝ የነበረው ምንም ግድ አልሰጠውም>> አላት እያቀፈችው
<<አይዞህ ኢነብዬ አትዘንበት እሱም እኮ ችግር ሆኖበት ነው>>
<<እምምም……ይሆናል ግን ብዙ አትከራከሪለት ፍቅር ሌላ ነገር አባትነት ሌላ ጉዳይ አንቺ ስለምትወጂው ብቻ ስህተቱን ልክ ነው ብለሽ አትከራከሪለት>>
ብሏት ሄደ ሙኒራ ማለት ኢነብ እንደገለፀው ለባሏ እንዲሁ ሽንጧን ገትራ የምትከራከር ሴት ናት ከአላህ ባታች ማንም ከሱ በኋላ እንጂ ከእሱ በፊት ሊሆን አይችልም ኢነብን እስከ መኪናው በአይኖቿ ሸኝታው ወደ ቤት ገባች
ᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔ
ከኢሻ ሷላት በኋላ
ᚓᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔᚔ
ኢርቫ ከመስጂድ ሲመጣ ቁርአን እያነበብኩ ነበር አንገቴን ዘመም አድርጌ አየሁት እሱን ሳይሆን እጁን የላኩትን ነገር እንደረሳው ሳይ እናቱን እንዳጣ ህፃን ተነፋረቅኩ ደግሞ ስርዓት አልባ አለቃቀስ
<<እንዴ ምን ሆንሽብኝ? ቆየሁ እንዴ?……… አረፈድኩ?>>
<<ባ…ባቅላ…ባው የታለ? ያልኩህ ባቅላባ ባቅላባውን ረስተኸዋል እኮ እህ እህ ህ እህ ህ እህ………>>
<<ውይ አውፍ በዪኝ……… አዚዘቲ እና ከቻልሽ ነገ ላምጣልሽ?>>
<<አይ አይ አሁን ነው የምፈልገው?>>
<<በቃ እሺ ወፍራም ልብስ ላምጣልሽ እና እንወጣለን ወይ እንደዛ ይሻላል?>>
<<አዎ እንደዛ ይሻላል>>
<<በቃ መጣሁ ልብስ ላምጣ>>
ብሎኝ ሄደ እና ወዲያው ይዞ ተመለሰ ወጣን አንድ የበላሁት ነገር አይቀመጥም ግን ደግሞ መብላት እፈልጋለሁ በቃ ሆዳም ሆኛለሁ ነው የምላችሁ 4ኛ ወሬን ያዝኩ ግን የአራት ወር ፅንሰ አይመስልም በጣም ያስታውቃል እና ተያይዘን ወጣን ጎዳናው በጣም ተውቧል ስለመሸ ያልኩትን ባቅላባ ማግኘት አልቻልንም ስንፈልግ አንዱ ጋር አለቀ አንዱ ጋር ደግሞ ማዘጋጀት አቁመናል ይሉናል ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ አንድ beakery ስንሄድ
<<አሁን ለትንሽ በጣም ለትንሽ ጨረስን>> አለን እንባዬ መጣ
<<በቃ እኔ አልሄድም>> አልኩት እና ደረጃው ላይ ተቀመጥኩ
ይቀጥላል☆ ☆ ☆ . . .
1 125
☆Anahira☆
🎀 ክፍል 22
☆ወረቀቶቹን ሰብስቦ አነሳቸው እና ሄደ ዝም ብያለሁ በቃ ዝም ለአንድ ደቂቃም ቢሆን ደነዘዝኩ መልሼ ቦርሳዬን አንስቼ ወደ ክፍሌ ስገባ እሱም ወረቀቶቹን የያዘውን ፖስታ ቁም ሳጥን ውስጥ እየከተተ ነበር ሩጫ በሚመስል መልኩ ሄጄ አልጋው ላይ ተቀመጥኩ ከሳጥኑ አናት ላይ ሻንጣ ያወርዳል
<<ም……? ለማን ነው? የት ልትሄድ ነው?>> አልኩት
<<ልብሶችሽን በማስተካከል ልተባበርሽ ብዬ ነው እስከዛ ድረስ አንቺ አረፍ በይ>>
<<እ……? እኔኮ እንዳልናገር ስላስጠነቀቀቺኝ ነው ደግሞ………ደግሞ ለምን ቅድም እንደዛ ተናገርከኝ?? እኔ በመምጣቴ የተበላሸ የህይወትህ ክፍል አለ?……እኔን በማግባትህ እንዲፀፅትህ የሚያደርግ ነገር ምን ሰርቻለሁ?>>
<<አላውቅም ካንቺ ጋር መኖርም አለመኖርም ተመሳሳይ ናቸው በቃ ስትኖሪም ታሳምሚኛለሽ ሳጣሽም እታመማለሁ ከእኔ ጋር ነሽ ማለት አልችልም አንድ ጣሪያ ውስጥ እየኖርን ግን ሁለት አለም ውስጥ ተከፋፍለናል>>
<<ምን አይነት ፍልስፍና ነው ይሄ ደግሞ ፈልገህም ሆነ ሳትፈልግ አግብተኸኛል እና አሁን ሰለቸሺኝ እያልከኝ ነው?>>
<<እንደዛ መሰለኝ ስሜቴን መረዳት አልቻልኩም በዚህ ሰዓት ቢያንስ የሆንኩትን እስከ ምረዳ እና እስከማውቅ ድረስ አንቺ አቢ ጋር ብትቆዪ ብዬ አሰብኩ>>
<<ከዛስ ከራስህ ጋር አውርተህ እኔን ስለመፍታት ቢመጣልህስ? ትክክለኛ ውሳኔ ከሆነብህስ ትፈታኛለህ?>>
<<አዎ አንቺም ፍቺውን ከእኔ በላይ እንደምትፈልጊው ይሰማኛል>>እንባዬ ያለ ከልካይ ይፈሳል
<<አርግዤ ቢሆንስ?!>> ቀና ብሎ አየኝ እና እየሳቀ መልሶ አንድ አባያ ሻንጣው ውስጥ ከተተ
<<ሃ ሃ ሃ……በዚህ ፍጥነት እንደማሆን እኔም አንቺም እናውቃለን>>
<<ግን ቢሆንስ? እኮ ነው ያልኩህ ትፈታኝ ነበር?>>
<<ሚንሃ………በማይመስል ነገር አታባብዪኝ ልጅ እኔ እናቴን ባጣሁበት ቅፅበት እንዲኖረኝ የተመኘሁት ነገር ቢኖር ልጅ ነበር በቃ አንድ ነፍስ ወደ ጌታዋ ስትሄድ ሌላ ነፍስ ደግሞ ለእኔ እንደ አደራ ስትሰጥ ያሰብኩትን ህይወት አይደለም እየኖርኩ ያለሁት ያልኩሽም እሱን ነበር>>
<<ስለዚህ ልንገርህ ያንተ ሃሳብ ያንተ ነው እኔም ግን በዚህ ፍጥነት እናት መሆኔ ገርሞኛል አላህ ዱዓህን ሰምቶህም ሊሆን ይችላል ግን አሁን ላይ ነኝ>> አልኩት
ፊቱ በመምታታት ሲቀያየር ይስተዋላል
<<እኮ አንቺ…… ማለ…ት ልጅ እርጉዝ ነሽ? ኧ……አንቺ ነሽ?>>
<<ዛሬ በነገርኩህ ሰዓት ልመጣ ያልቻልኩት ለመከታተል ከአትሮን ጋር ሄጄ ነው ለዛሬ ሳምንት በድጋሚ ቀጥራኛለች የዛኔ አንተም መገኘት ሊኖርብህ ይችላል>>
<<ማለት?…… መጀመሪያ ያልሺኝ ሳይገባኝ ሆስፒታል ስለመገኘት ታወሪያለሽ?>>
<<እ……እና ምን ልበል? ሌላ አገላለፅ አለው እርጉዝ ነኝ ለማለት ከፈለግክ ቫይታሚኖቹን ወረቀቱን መመልከት ትችላለህ ማረጋገጫ መሳሪያው በራሱ አትሮን ቦርሳዬ ውስጥ ሳታደገው አትቀርም>> እያወራሁት አቀርቅሬ ቦርሳ መበርበር ተያያዝኩት በዚህ መሃል ነበር ኢርቫ ከቆመበት መጥቶ ግንባሬን የሳመኝ እኔ ግን እጄን ለፍለጋ ካሰማራሁበት የቦርሳ ውስጣዊ ክፍል አልተላቀቅኩም
<<የኔ ሁሉ ነገር የኔ የኔ ምን ልበልሽ?………ም…ምንም አላጣሁም ያጣሁት ራሴን ነበር ካንቺ ምንም አላጣሁም ምናልባት አሁን የተናገርኩሽን ነገር በራሱ ከምንም ነገር መቁጠርሽ ለእኔ ሞት መሆኑን ታውቂያለሽ? ቃሌ ከማንም በላይ ግብዝነት አለው በህመሜ ውስጥ ፍቅር አንቺ ብቻ ነሽ ያንን የምታዪው እንደ ህፃን ሁሌም ተመሳሳይ ጥያቄ ውስጤ አለ አትወደኝም ነፍሴን ገደልኳት ነፍሴን በደልኳት በቃ ስላንቺ ጥሩ እንዲሰማኝ እፈልጋለሁ ግን አልቻልኩም ነበር አሁን ግን ለእኔ ከዚህ በላይ ፍቅር የለም>> የዚህን ሰዓት የያዝኩትን አስቀምጬ አቀፍኩት
ዛሬ እንግዶቻችንን ማለትም አክስቱን ከእነ ልጆቿ ለመሸኘት 11:25 ላይ አየር መንገድ ነን ከመጡ አንድ ሳምንታቸውን አጠናቅቀዋል ኢርቫ አባቱ ከሄደበት እስከ ሚመለስ እንድትቆይ እና አውፍ እንዲያባብላቸው ቢጠይቃትም አሻፈረኝ በማለቷ ዝም ሊላት ችሏል አቢ እና አባቴ(መርዋንም) ከሄዱ አልተመለሱም እነሱም ሳምንታቸውን ይዘዋል በዚህ ምክንያት ኢነብ ጠዋት ማታ ጭንቀት ውስጥ ነው ኒሳዕን ሌላ ሰው እንዳይቀድመው ይንቆራጠጣል ቀኑ ረዘመበት
<<ሚንሃ?………! በእነዚህ ቀናት ውስጥ ምንም አይነት መጥፎ ነገር ላይብሽ አልቻልኩም ሰሊመት አንቺን የመረጠችበትን ነገር በዚሁ ተረዳሁት ኢርቫ እናቱን አላጣም ሁለተኛ እናት አገኘ እንጂ………ደግሞ ምንም እንኳን የአላህ ስራ ቢሆንም አሁን ላይ ሁለት ነፍስ ይዘሻል ይህ ደግሞ ኢርቫን ብቸኝነት እንዳይሰማው አድርጓል የሚወለደው ልጅ ልጅ ብቻ እንዳልሆነ ተገንዘቢ ከፍ ሲል አማካሪው እና ወንድሙም ጭምር ነው ስለዚህ እንደ ባል ዘመድ በምን አይነት መንገድ ልጠላሽ እንደምችል ምክንያት አጣሁ>>ሁለታችንም ከት ብለን ሳቅን ሁለተኛ ሰሊመት ኧረ እራሷን copy ናት ስትስቅ በራሱ እንደእሷ አይኖቿ ይጨፈናሉ ኢላሂ የአንዳንድ ሰዎች አንደበት ማማር……… መልሳ እንባ እየተናነቃት
<<ልጅሽን ወልደሽው ደግሞ አላህ በሰላም ያገናኘን በስልክ ደግሞ እንዘያየራለን እሺ?…… ሃቢብቲ>> እኔም እንባዬን እየዋጥኩ
<<መርሃባ አላህ በሰላም ያድርሳችሁ>> አልኳት አይመን እና ኢርቫም ከእኛ ብዙ ሳርቁ የሚባባሉትን ተባብለው ተቃቀፉ መንሱረት አማርኛ ትንሽ ቢቸግራትም እንደነገሩ ተሰነባበትን እና ከኢርቫ ጋር ወደ ቤታችን አቀናን የቦሌ ጎዳና በመብራት ማሸብረቁ
15🥰 ይቀጥላል☆ ☆ ☆. . . .
1 125
☞ እናቴን ማን ነው የሚገዛኝ???? ☜
አጂብ የሆነ ታሪክ
አንድ ወጣት በጣም ቆንጆ የሆነች ልጅ ይወድና ለጋብቻ ያጫታል ከተጫጩ በዃላ ግን ግልፅ በሆነ አረፍተነገር እናቱን እንደማትወዳት እና አብራቸው መኖር እንደማትፈልግ ትነግረዋለች ።
እሱን ብትወደውም እናቱን ግን ልትወድለት አልቻለችም እናቱም
በእድሜ የገፉ ስለነበሩ ልጂቷ ልጂቷ ብዙ ታስቸግራቸው ጀመር።
ከዛም ልጅ እንደማያገባትና እንደሚለቃት አስረግጦ ሲነግራት ልጂቱ ልጁን ስለምትወደው ደነገጠች እንደምታስተካክልና እናቱን እንደምታከብር እንዲያገባት ተማፀነችው።
ልጁም ካስተካከልሽ ብሎ እሽ አላት ከዛም የሰርጋቸው ቀን ደረሰ ምሽቱ ላይ ሠዎች በተሰበሰቡበት መሐል እናቱ ተጋባዥ እንግዶችን ለማስተናገድ በደስታ ሽር ጉድ ሲሉ
*ሙሽሪት በንዴት ይህቼን አሮጊት እናትክን ወዳ በልልኝ አታሳየኝ ከቻልክ እንደውም ሽጣት አለችው*
ልጁም ፈገግ ብሎ ተነሳና ሰዎች ከተሰበሰቡት መሐል
*"እናቴን ማን ነው የሚገዛኝ "ለ 3 ጊዜ በተከታታይ ማለት ጀመረ*
እናቱም ከልጃቸው አንደበት የሰሙትን ማመን አቃታቸው ማዘንና ማልቀስ ጀመሩ እንግዶቹን በጣም ተገረሙ አዘኑ ከዛም ሙሽራው ወደ ሙሽሪት ዘወር አለና
*"አየሽ እናቴን ማነም ሊገዛት አልቻለም
ለምን እንደሆነ ታቂያለሽ? ምክንያቱም እናት ውድ ነች እናቴ ከምንም በላይ ውድ ነች ዋጋ አይተምናትም እኔ ግን
እናቴን እገዛታለው አንችን ደግሞ ሺጨሻለው
* ፈትቸሻለው በማለት የሰርጉ ቀን ቀለበቱን ከፊቷ ላይ በመወርወር ትቶላት እናቱን ይዞ ሲወጣ ወዲያው ከእንግዶቹ አንዱ ተከተለውና እንዲክ አለው "
*ለሴት ለልጄ ከአንተ የተሻለ ጥሩ ልጅ
አላገኝም ፍቃደኛ ከሆንክ ልጄን ልዳርልክ*
ብሎት ልጁን ይዞ ወደ ቤቱ ወሰደው ልጁም የዛን ሰው ልጅ ሲመለከታት እጅግ ውብና አደበኛ ነበረች አገባትም ለባሏም ሆነ ለባሏ እናት ፍቅሯን ያለ ገደብ ትሰጣቸውና ትንከባከባቸው ጀመር።
የወለደቻት እናቷ እስክትመስላት ድረስ
የሚጠበቅባትን ሁሉ መወጣት ጀመረች።
መልካምና ደስተኛ የሆነ ህይወት ይኖሩ ጀመር።
*አንድን ነገር ለ አሏህ ብሎ የተወ አሏህ የተሻለውን ይወፍቀዋል*
እህቴ ከታሪኩ ብዙ ቁምነገሮችን ተማሪበት፣ ለጓደኞችሽም አጋሪው
1 125
☆Anahira☆
ክፍል 21
☆ተደስተዋል እኔ ብቻ ነኝ ከምንም ያልሆንኩት ወይ ከመደሰት ወይ ከመፀፀት አላውቅም ብቻ ኡሚ እና አትሮኖስ ሲንጫጩ
<<ቆይ ዛሬ ሌሊቱን ያለ እንቅልፍ ልታሳድሩኝ ነው እንዴ?>>
እያለች አያቴ ከክፍሏ ብቅ አለች አትሮኖስ የደስታ ሲቃ እየተናነቃት ሄዳ አቀፈቻት
<<አያቴ በድጋሚ ቅድመ አያት ልትሆኚ እኮ ነው>> አለቻት በተሸበሸበው ጉንጯ ፈገግ ብላ
<<የሃሩን ሚስት(ሃሩን ከኢነብ በፊት ታላቅ ወንድሜ ነው እና ሃላሉ እሷ ነፍሰ ጡር ናት) ወለደች?>>
<<አይ…… አይ ሳይሆን ሚንሃ እርጉዝ ናት>> አለቻት በጥልቀት አይኖቿ የቻሉትን ያህል አስፍታ አጥብባ አየቺኝ ሳያት ፈገግ ለማለት ሞከርኩ
<<ይህ እልህ ነው ……ሃ ሃ ሃ እንደዛ ካልኩ በኋላ ለመሆን መስራት ጀመርሽ? ግን እንደእኔ ቸኩለሻል የት ለመኬድ ሃ ሃ ሃ……>> ኡሚ፣ አትሮን፣ እና ኢነብ ሁኔታዋ ግራ እየገባቸው ነው እኔ ግን እንዴት እንደደነገጥኩ አታውቁም ደግሞ መናገሯ ሳያንስ ሳቋ አስፈራኝ ቆይ ሰው በዚህ ደረጃ እንዲህ ከነበረበት ሲወርድ ራሱን በምላሱ ሲያቀል እና ሲያዋርድ አያስጠላም?
ትቻቸው ወደ ክፍሌ ገባሁ እና አንሶላውን ተከናንቤ ተኛሁ እኔ ሰው ሲያናግረኝ ካልተጠነቀቀ በምንም መንገድ የሚከፋኝ አይነት ሰው ነኝ አያቴ ደግሞ እንድትናገር ከፈቀዱላት ሰውን በጣም ታሳዝናለች በቃ ታስከፋለች ማንም ምንም ሊላት አይችልም ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ ምንም እንኳን አትሮን ልታረጋጋኝ ልታባብለኝ ብትሞክርም አልቻለችም
በዛ ፍጥነት ቤቱን ትቼ ኢርቫ ጋር ብመለስ አልኩ ብቻ እሷን ላለማየት ግን ደግሞ ሰዓቱ 05:47 ይላል መንቀሳቀስ አይቻልም ተሸፋፍኜ እያለቀስኩ የሆነ ሰዓት ላይ እንቅልፍ ወሰደኝ ፈጅር አዛን አለ ፈጅርን ሰግጄ ትንሽ ተኛሁ ነግቶ ቁርስ እስከምንበላ ድረስ አትሮኖስ አስቀድማ ስትንከባከበኝ ነበር
<<አሁን ለኢርቫ ብትነግሪው አስበሽዋል?…… ውይይይ እንዴት እንደሚሆን ገና አሰብኩት>>
<<ምን ልጅ ያን ያህል ያጓጓል እንዴ? ማንም እንደሚወልደው ነው የምወልደው የተለየ ፍጥረት አይደለም>>
<<ይህቺ የ82 አመት አሮጊት ያንን አለቺኝ ብለሽ እንደዚህ አይነት ተስፋ አልባ ወሬ አታውሪ ሲቀጥል እናቱን ባጣበት ሰዓት ልጅ እንዳለው እንደማወቅ ደስ የሚል ነገር የለም እና ወደ ቤትሽ ከመሄድሽ እኔም ወደ ስራ ከመግባቴ በፊት ሆስፒታል እንሄዳለን>> አለቺኝ እሺ ነበር ያልኳት
እንዳሰብነውም ኡሚን ተሰናብተን ወደ ሆስፒታል ሄድን በጣም ደስ የሚል እንክብካቤ ነበር ከዶክተሯ ያገኘነው ከምርመራ በኋላ
<<6 ሳምንት ሆኖታል ከ14 ሳምንት በኋላ ማለትም ከ3 ወር በኋላ ፆታውን ማወቅ እንችላለን እንኳን ደስ አላችሁ…… የማዝልሽ መድሃኒቶች(ቫይታሚኖች) አሉ ስትወጡ ትገዛላችሁ>>
አለችን እንደነገረችን የቫይታሚኖቹን መውሰጃ ጊዜዬን አረጋግጠን እና ገዝተን ተለያየን
<<አብሬሽ ብሄድ ደስ ይለኝ ነበር ግን በቅርቡ እመጣለሁ እሺ? እጎበኝሻለሁ>> አለቺኝ አትሮንም እሷን ተሰናብቼ ወደ ቤት ስሄድ ሰዓቱ 05:10 ብሏል ኢርቫ ካለኝ ሰዓት እንዳረፈድኩ እያሰብኩ ነበር
ስለደረስኩ በሩን ከፍቼ ገባሁ ሳሎን ውስጥ የእይታ መነፀሩን አድርጎ ወረቀቶች ያገላብጣል አክስቱ ልጆቿን ይዛ አንዳንድ አካባቢዎችን ልታስጎበኛቸው ሄዳለች እንዲሁ ጥርሴን መክደን አቅቶኝ እያገጠጥኩ ነበር የገባሁት
<<አሰላሙ አለይክ?>> አልኩት ከጎኑ ሄጄ እየተቀመጥኩ አይኑን ከያዘው ወረቀት ላይ ሳይነቅል
<<ወአለይኪ ሰላም>> አለኝ ፍፁም ድክምክም እና ስልችት ባለ ድምፅ አሁንም ቀና ብሎ እንዳላየኝ ሳስብ
<<ቡና ይዤልህ ልምጣ? ማቀርቀሩ አድክሞሃል መሰለኝ>>
<<መርሃባ ደስ ይለኛል>> ወዲያው ቦርሳዬን አስቀምጬ ማዕድ ክፍል ገባሁ ውሃው እስከሚፈላ ትንሽ ቢቆይም ቡናውን አሳክቼው ነበር ስለሁኔታው እንዴት ልነግረው እንደምችል እያሰብኩ ነው
<<የምትወደው ይመስለኛል ለቡና ብዙም ፍላጐት ስለሌለህ ወተት ጨምሬበታለሁ>>
<<ጀዛኩሙላህ>> አንድ ወረቀት ላይ በትኩረት አፍጥጧል
<<ኢርቫ እ………ም እ?……>> ስግደረደር ቀደመኝ እና
<<እናቴ ህመምተኛ እንደነበረች ከመሞቷ በፊት ታውቂ ነበር እንዴ?>> አለኝ አሁን ዞሮ እያፈጠጠብኝ ነው አይኖቹ የአይኖቼ ውስጣዊ ክፍል ውስጥ ይንከራተታሉ
<<ንገሪኝ እንጂ ታውቂ ነበር?………>> ዝም አልኩት ምላሴን የዋጥኩት ይመስል አስተያየቱ ሲያስፈራ
<<ኧ?…… ለምን ዝም ትያለሽ? ታውቂ ነበር?>>
<<አይ አላውቅም አንተ ያላወቅከውን እኔ እንዴት ላውቅ እችላለሁ? አ…… አላውቅም ነበር>>
<<ደግሞ ውሸትሽ እንጂ ታዲያ ይሄ የማን ፊርማ ነው?>> ወረቀቱን እንደመወርወር አድርጎ ሰጠኝ ቀስ ብዬ አነሳሁት ወዲያው ትዝ አለኝ
[<ከቅርብ ሰዎች ወይም ከቤተሰቧ የሚያውቀው አንድ ሰው ቢኖር አንቺ ነሽ እዚህ ጋር ደግሞ ፊርማሽ ያስፈልጋል እና ሚንሃ እዚህ ጋር ፈርሚ>]
<<ንገሪኝ እንጂ የማየው ፊርማ የእኔን ነው?>> ሲል የኢርቫ ጩኸት አባነነኝ <<ንገሪኝ ያንተ ፊርማ ነው አትዪኝም አይደል?>> ስሩ ተገታትሯል በዛች ሰዓት አንድ ነገር ብናገር ጥሩ ነገር እንደማይመጣ ስለተረዳሁ ተጠግቼ አቀፍኩት እስከ ሆነ ደቂቃ ድረስ የንዴት ትንፋሽ ነበር የሚተነፍሰው ቆይቶ ግን ተንሰቀሰቀ
<<……ለምን አልነገርሺኝም? አ…… አሁን ያለሁበት ሁኔታ ጥሩ ይመስልሻል? ትክክለኛ ሷላት እንኳን ከሰገድኩ ዘመናት አለፉ ለምን ሚንሃ ለምን??>>
<<እንድታውቅ እና እንዲነገርህ ብዙ ነገር ብዬ ነበር ግን ………ግን እናቴ አ…… አትንገሪው ማወቅ የለበትም አለቺኝ እኔ እኮ እንዲህ ይሆናል አላልኩም ልነግርህ ብዙ ጊዜ አስብና ለእሷ የገባሁት ቃል ስላለ እተወዋለሁ እ……… ኢርቫ እኔ እንድታውቅ ፈልጌ ነበር ግን እሷም ላይ አትዘንባት ላንተ ብላ ነው እኮ እንጂ ትነግርህ ነበር አትዘንብኝ እሺሼንዳልነግርህ ስላስጠነቀቀቺኝ ነው እሷም ብትሆን ደግሞ ላንተ አስባ ነው እባክህ በመጥፎ ነገር አትዪብኝ እ……?>>
ለማሰብ ይሁን አላውቅም ረጅም ሰዓት ዝም አለ ለቀቅኩት እና ተስተካክዬ ተቀመጥኩ በረጅሙ እየተነፈሰ
<<ሚ……ሚንሃ>>
<<እ… ነዓም>>
<<አሁን ጥሩ ሁኔታ ላይ ስላልሆንኩ በቃ ሂጂ>>
ጆሮዬ ነው ወይስ እውነት ነው ሂጂ ማለት?
<<አ…… አል…ገባኝም ሂጂ ማ…ለት?>>
<<ከራሴ ጋር የማወራበት ጊዜ ፈለግኩ ወይ ልክ አልነበርኩም ነበር ተወኝ እንዳልሺኝ አንቺን መተው ነበረብኝ መሰለኝ ማለት ነው ማ……… ማለት አንቺን ማግባት አልነበረብኝም ነበር ይሁን? አላውቅም ግን ያለምኩትን ህይወት አይደለም እየኖርኩ ያለሁት………>>
አሁንም ጆሮዬ ነው እንጂ ከኢርቫ አፍ እንዲህ ያለ ከላም እሰማለሁ የሚል እምነት የለኝም ያወራል እኔ ግን የለሁም በቃ ተምታታብኝ ከዛ ከተቀመጠበት እየተነሳ
<<ምን አሰብሽ?>> ሲለኝ ድንግርግር እያልኩ
<<አ…… አንተ እንደፈለግክ>>
<<በቃ…… ገና መምጣትሽ ስለሆነ ትንሽ አረፍ በይ እና አደርስሻለሁ>> አለኝ እንባዬ የአይኖቼን ግድቦች ጥሰው ለመውረድ ይታገላሉ
<<የት?>> አልኩት ጉሮሮዬ እየተያያዘ
<<ቤተሰቦችሽ ጋር>>
15🥰ይቀጥላል ☆ ☆ ☆
ግን likeየለም 😔
1 125
☆Anahira☆
🎀 ክፍል 20
☆ ወዲያው ነበር ቤት የደረስነው ከኡሚ ጋር ወሬ ይዘን ስለነበር መድረሳችንን በራሱ አላወቅነውም መغሪብን ሰግደን መጨዋወት ጀመርን በተለይ ከአትሮኖስ ጋር ምሽቱን ሳሎን ስንጫወት ቆይተን ወደየ ክፍላችን ገባን እኔ እና አትሮኖስም እንደዛው ለአንዳንድ ነገሮች መፍትሄ ይሆናል ያለችውን ሃሳብ እየነገረቺኝ ነበር በሩ ድንገት ተንኳኳ ""(ግቡ"") አለች እሷም ተከፍቶ ሲገባ ኢነብ ነበር
<<ሴቶች በቃ ተገናኛችሁ እና ሌሊቱን ሙሉ ስታወሩ ነው የምታድሩት እባካችሁ ተኙ ሌላ ጊዜ ታወራላችሁ>> ሲል አትሮን
<<ቆይ ምን ይመለከትሃል?>> ረጅም ሳቋን ለቀቀችው ፈገግ እያለ
<<እኔማ ለእናንተ ብዬ ነው እሺ አሁን ስለመጣሁበት ጉዳይ ስነግራችሁ አትሮን የጠፋሽ እቃ አለ?>> አላት ቁልቁል እያያት አጭር ናት ሳቋን እየገታች
<<የለኝም ምነው?>>
<<አይ በቃ ተዪው ምንም አልጣልሽም?>>
<<እ…… እ… ምን ልጥል እችላለሁ ምንም አልጣልኩም>>
<<እና ልውሰደው?>>
<<ኢነብ እንደዛማ አይደረግም ቆይ ምንድነው?>>
<<በቃ ወሰድኩት ቻው>>
<<ኧረ ኢነብ አይደረግም ካልሆነ……>>
<<ካልሆነ ምን?>>
<<እጅህን እነካሃለሁ ሴት መንካት አይቻልም አይደል? በቃ ጌታህ ያረክስሃል>>
<<እንዲመሽልኝ ትንሽ እንኳን መቀለድ አልችልም?……… ለማንኛውም አንቺም አትነኪኝም እኔም ልወሰው የምችለው ነገር አልነበረም ስልክሽ>> አላት ፈገግ ብላ
<<ተመልከቺ ሚኑ የእህትሽን ልበ ቢስነት ስልኬን የሚያክል ነገር ጥዬ……… ለማንኛውም ሽኩረን ያ አኺ……>>
ወደ አልጋዋ መጥቶ ሰጣት
<<አየሻት በአረብኛ ለመድኩ ብላ ስትፈላሰፍብኝ ለማንኛውም ደህና…… እደሩ>>
<<አሜን ወንድሜ ደህና እደር!>>
እኔ ፍዝዝ ብዬ ቀረሁ ኢነብ እና አትሮን አልመስልሽ አሉኝ አሁን እኔም ስለሌለሁ ቤት ውስጥ ያሉት እነሱ ብቻ ናቸው ከመግባባት ውጪ አማራጭ የላቸውም ብዬ አሰብኩ በዚህ መልኩ ከቁም ነገር አልፈው ለቀልድ መቀራረባቸው እየደነቀኝ ያሰብኩትን ሁሉ ደግሞ የኒሳዕ ጉዳይ ደርሶ ያበላሸዋል አይ ኢነብ ኒሳዕን ሊያገባ አይደል እንዴ? አትሮኖስም ኢስላምን እንደማትቀበል አውቃለሁ ምንድነው የምዘባርቀው ብዬ ራሴን አደብ አስይዛለሁ በዚህ መሃል ነበር
<<ይሄ እብድ የሆነ ልጅ>> ስትል ከሃሳቤ ነቃሁ
<<ይገርማል በስተመጨረሻ አንቺና ኢነብ ተግባባችሁ?>> አልኳት ፈገግ ብላ
<<እ?/!………አሁን እሱም ሊያገባ ባለበት ሰዓት መስማማታችን ያስጠላል ግን ባለፈው ያ! ያቺ ታማሚዋ ከጎዳቺኝ ጊዜ ጀምሮ ታላቅ ወንድም የሚመስል ኢነብን ነው ያገኘሁት ወደ ስራ በራሱ ብቻዬን መሄድ አቁሜያለሁ ከእሱ ጋር ነው የምንሄደው ብቻ አንዳንድ ሰዎች ስትቀርቢያቸው ነው ደግነታቸውም በዪው የማታውቂው እና ደስ የሚለው የጓደኝነት ስሜታቸው የሚገለፀው>> ስልኳን እየጎረጎረች ነበር ይህን ያለቺኝ እኔም
<<ግን እኮ ማለት አውቃለሁ ሁለታችሁም ጋር ምንም እንደሌለ ግን ስራ አብረን ነው የምንሄደው እና የምንመጣው ስትዪ የሆነ ነገር አለ……>>
<<እንዳጨርሺው ሚንሃ ሁለት ባዕድ ወንድና ሴት በብቸኝነት አብረው ከሆኑ ሶስተኛው አካል ሰይጣን ነው የሚለውን አቢ ሲናገር ሰምቻለሁ ለማይሆን ነገር ሰይጣን ይገፋፋቸዋል ……… አሁን እሱን አይደለም የምናወራው ፊት እና ኋላ ሆነን ነው የምንሄደው እሱ እንደ ራይድ ሹፌር ያሽከረክራል እኔ እንደ ድንበኛ ከጀርባ ወንበር እቀመጣለሁ ገባሽ?……ሲቀጥል ደግሞ ልጁ ኢነብ ነው ለእንደዚህ አይነት ነገር ቦታ የለውም እኔም ብሆን ንፁህ ወንድሜ ነው ሚንሃ በዛ ላይ ሊያገባ ነው ኒሳዕ እና ወላጆቿ እሺ እንዲሉ ፀልዪለት እንዴት እንደሚወዳት ብታዪ ዪ ዪ ደግሞ እሷ ራሱ ኒቃቧን ስታወልቀው ውይይይይ እንዴት እንደምታምር እያልኩ ኢነብን እንዴት እንደማጓጓው ያው ሲፈቀድለት አይደል? ማየት የሚችለው? እና እንደዛ ነው እልሻለሁ>>
አለቺኝ ላነሳ የነበረውን ሃሳብ በሙሉ መንገዱን ስለዘጋችብኝ ዝም ማለት እንጂ ምርጫ አልነበረኝም የአትሮን የሆነ ነገር እንደተቀየረ በራሱ ያስታውቃል በዚህ መንገድ መቀራረባቸው ደስ አላለኝም መጥፎ ነገር አስቤ ሳይሆን አንዳቸው ጋር አንድ ነገር ቢኖር የሁለቱም አዘቅጥ መውረድ አሳዝኖኝ ነው
ትክዝ እንዳልኩ ድንገት የማቃር ነገር ተሰማኝ እና መታጠቢያ ክፍል ገባሁ አትሮንም ተጣድፌ መግባቴን ስላየች ተከተለቺኝ በጉጉት እነዛ ስፍስፍ ብዬ ኡሚ አምጥታ የሰጠቺኝ እና የበላሁት ምግብ የቀረ አለ ካልኳችሁ ውሸት ነው በሚጨንቅ ሁኔታ አስመለሰኝ ያለ ማቋረጥ አትሮንንም ሳላስጨንቃት አልቀረሁም ልብሴም ተበላሽቶ ነበር እና እንድቀይር አመጣችልኝ ደግሞ እራት ሲቀርብ አልበላም ብዬ ነበር መጀመሪያውንም ውስጤን ከብዶታል ቀዝቃዛ ውሃ በጭንቅላቴ ላይ እያፈሰሰች ካረጋጋቺኝ በኋላ
<<ሚኑ…… ምነው? ምን ሆንሽብኝ?>> አለቺኝ ፊቴን በፎጣ እያደራረቅኩ
<<ቅድም ያመጣችሁት ባቅላባ መሰለኝ ጣፋጩ በዝቷል ደግሞ ጓጉቼ ስለበላሁት ይሁን አላውቅም ኡፍፍፍፍፍ>> አልኩ እና ወደ አልጋዬ ሄድኩ ገና ቁጭ እንዳልኩ አሁንም ሊያመልሰኝ መሰለኝ እና ሩጫ ወደ መታጠቢያ ክፍል …… አሁንም ፊቴን እያደረቅኩ ስወጣ አትሮን ባለማመን እያየቺኝ
<<እ…… አንቺ አርግዘሻል እንዴ?>> አለቺኝ በመጠየቋም ደንግጣለች እኔም በጥያቄዋ ደንግጫለሁ መለስኩላት
<<ኧረረረረ……… ምን አመጣሽ ደግሞ አትሮን?>> አልጋዬ ላይ ዘፍ ብዬ ተቀመጥኩ እሷም ለመተኛት ትራሷን እያስተካከለች
<<ቅር ካለሽ ይቅርታ ግን እንደዛ ስለመሰለኝ ነው አሁን ስላስመለሰሽ ሳይሆን ቅድም ሳይሽ በራሱ የሆነ ሰውነትሽ ዝልፍልፍ ብሎብኛል ለዛ ነው የጠየቅኩሽ>> አለቺኝ ገብታ ተኛች እኔም ተኛሁ እንቅልፍ ሸለብ ሲያደርገኝ ብድግ ብላ
<<ግን እኮ መመርመሪያው በፋሻ ሳጥን ውስጥ አለ ለምን አናየውም?>>
<<ምኑን?>> እኔ እረስቼዋለሁ ስለምን እንደምታወራ በራሱ አልገባኝም ነበር
<<እንዳረገዝሽ ነዋ እንየው>>
<<አትሮን ምን ሆነሻል ገና እኮ ካገባሁ ሁለተኛ ወሬ ነው ምን ነክቶሻል? አሁን እንተኛ እንቅልፌ መጥቷል>> አልኳት ግን ሳትሰማኝ መሳሪያውን አውጥታዋለች ወደ አልጋዬ እየመጣች
<<እባክሽ እሺ በዪኝ እና የመሃል ጣትሽን እዚህ ላይ አስርፊ>>
<<ይኸው ደስ ይበልሽ ምን አይነቷ ናት ባካችሁ>>አልኩ ጣቴን እንዳነሳሁት አትሮን ማበድ ጀመረች ልምምድ የሌለው ጭፈራ በአልጋዋ ላይ ትጨፍራለች ሰው እንዲህ እንኳን ስትሆን አይጠረጠርም? ዝም አልኳት እና ጭንቅላቴን ትራስ ላይ አሳርፌ ለመተኛት ሞከርኩ የአትሮን ገጣሚ አልባ እንጉርጉሮዋ ማቆም ስላልቻለ ብቻ ውስጤን አንድ ፍርሃት ጠራኝ መልሼ"እውነት አርግዤ ቢሆንስ?"" በዛው ፍርሃት ውስጥ እንዳለሁ ተነሳሁ እና
like 🥰
1 125
<<አንዲትን ሴት በማርገዟ ባነውራት
እኔ እራሴ እንዳላረግዝ እፈራለው >> አብደሏህ ኢብኑ መስዑድ
የሰዎችን አይብ ምንከከታተል ከሆነ አሏህ በነሱ አይተን የጠላነውን ነገር በራሳችን ያሳየናል ።
የሰዎችን አይብ ከመከታተል አሏህ ይጠብቀን
1 125
☆Anahira☆
🎀 ክፍል 19
☆<<ታውቃለህ ግን ኢርቫ እንዳገባህ ስላልነገርከኝ ትንሽ ቅር ብሎኛል አባትህ እንደማይነግረኝ ታውቃለህ ለምን አልነገርከኝም??¿>>
ፊቷ ጥያቄ ምልክት ሰርቶ ነበር በመጅሊሱ ዙሪያ ተቀምጠናል
<<አፍወን አክስቴ በጣም የተጣበበ ስለነበር ሰፊ ሰርግ አላዘጋጀንም ያው ኡሚ እንደምትሞት አስቀድማ ታውቅ ስለነበር ቶሎ እንዲሆን ፈለገች……… ሚንሃም አልተቀበለቺኝም ነበር>>
ብሎ ዞሮ ሲያየኝ መጀመሪያውኑ እያየሁት ስለነበር ተገጣጠምን እና ወዲያው አይኔን ሰበርኩ
<<እ…… እንደዛ ከሆነ ይሁን ኧምምም ሌላው ደግሞ እኛ አንድ ነን ያው ሰሊመትን መሆን ባልችልም ከዚህ በኋላ በሁሉም ነገር ከአላህ በታች አብሬህ እንደሆንኩ እወቅልኝ አይመንም ሆነ መንሱራ እህት እና ወንድምህ ናቸው እ…… አውቃለሁ በጣም ያሳዝናል ከእንግዲህ ስልክህ ላይ እማዬ የሚል ጥሪ አይኖርም ኡሚ ብለህ የምትጠራትም እውነተኛ እናት የለችህም ግን አላህን የምታመሰግንበት አንድ ነገር ቢኖር ሚስት አለህ ነገ ያንተ አባቴ የሚሉህ ልጆች ይኖሩሃል ምምምም…… እሱን ስታስብ ከማንም በላይ አላህን ታመሰግናለህ አልሃምዱሊላህ>>
<<እ…… አዎ ተጫወቱ በቃ አንድ ጊዜ መጣሁ>>
ብሎ ከመካከላችን ተነሳ የጤናው እንዳልነበር ያስታውቃል
<<ሚንሃዬ አንቺስ ቤታችሁ ውስጥ ስንት ቤተሰቦች ናችሁ?>>
<<6 ነን ልጆች ማለት ነው እ…… እና ወላጆቼ አሉ ከአንድ ወንድሜ እና ከእህቴ በቀር ሁላችንም አግብተናል>>
<<ማሻአላህ ደስ ይላል ታናሾችሽ ናቸው?>>
<<ኧረ ሁለቱም ታላላቆቼ ናቸው እኩያ ናቸው>>
<<ኦ መንታ?>> ስትለኝ ምን እንዳልኩ ግራ ገባኝ አትሮኖስ እና ኢነብን ለማለት ነው ያሰብኩት የነበረው ግልፅ ላድርግላት ብዬ
<<ሳይሆን እሷ አብራን ነው ያደገችው ያው እህቴ ማለት ናት>>
<<ስለዚህ ደፍረው ያላወጡት ነገር ይኖር ይሆናላ ለዛ ነው እንጂ አንዳቸው ያገቡ ነበር>>
<<ኧረ አክስቴ እንደዛ አይደለም እሷ ክርስቲያን ናት እሱ ደግሞ በቅርቡ ላሰባት ሴት ሽማግሌ ሊልክ ነው>>
አልኳት የአስተሳሰቧ ርቀት እየገረመኝ አስባችሁታል ኧረ እንደውም አታስቡት ኢነብ እና አትሮኖስ ጭራሽ አይሆኑም በዛው መሃል ኢርቫ ትዝ ሲለኝ
<<እ… አክስቴ ቆይ እመለሳለሁ አንድ ጊዜ>> ብያቸው ሄድኩ ቀጥታ ወደ መኝታ ክፍል ነበር የሄድኩት ክፍሉ ደህና ሆኖ እንዲጠብቀኝ ዱዐ ሳደርግ ነበር ስገባ ግን ምንም ነገር አልተበላሸም በቦታው ነው አልጋው ግርጌ ጋር ቁጭ ብሏል በሩን ቀስ ብዬ ከፈትኩት እና ገባሁ ቀና ብሎ አይቶኝ አንገቱን ደፋ
<<ምነው? ለመቀመጥ ነው እንዴ የመጣኸው?>>
<<ኡሚ ላትመለስ ነው ለካ የሄደችው እውነትም ከዚህ በኋላ በኡሚ ስም save የተደረገ ጥሪ አይኖርም>>
<<ውይይይ ኢርቫ በቃ በቃ……>>
<<ግን………ግ…ን አል……አልቻልኩም>>
እንደ ሴት ስቅስቅ ብሎ ነበር ያለቀሰው አዎ የበፊቱ ኢርቫ የለም እናቱ የገነባችው ኢርቫ የለም በትንሹ በትልቁ አልቅስ አልቅስ ይለዋል እንደ ህፃን አቅፌ አባበልኩት
ዛሬ ጁሙዓ ነው ከመስጂድ መልስ አንድ በጣም ደስ የሚል ነገር ተፈጠረ ኡሚ ፣ አትሮኖስ ፣ ኢነብ እና አያቴ መጥተዋል ያው አያቴን አልጠላትም ብቻ ከስህተቷ እንድትመለስ ዱዓ አደርግላታለሁ እንጂ ኡሚን ግን ሳያት በቃ በጣም ደስ አለኝ ከእናቴ(ከሰሊመት) ሞት በኋላ ተገናኝተን አናውቅም ለመሄድ አስባለሁ ግን ኢርቫ ቤት ስለሚሆን እንሂድም ስለው ደስተኛ አይሆንም እናቱን ካጣ በኋላ ከሰው ጋር መገናኘቱን ቀንሶታል ይህን ስለማውቅ እኔም ጫና አላበዛበትም ዓላ ኩሊ ሃል የኢርቫም አክስት ወላጆቼን ማየት ፈልጋ ስለነበር ጥሩ አጋጣሚ ሆነልኝ ኡሚ አቢ እና አባቴ(መርዋን) ከከተማ ውጪ በቅርቡ የተገነባ መስጂድ ሊያስመርቁ እንደሄዱ ነገረቺኝ
የኢነብም ሽማግሌ የመላክ ጉዳይ ከሄዱበት ጉዳይ መልስ እንደሚደረግ አያይዛ አያቴም አቢ እንቢ እንዳላት እና እሷም ጥሩ ለመሆን እየሞከረች እንደሆነ ግን ደግሞ ያለምክንያት ጥሩ ለመሆን እንደማትሞክር እና ከፀባዪዋ መቀየር ጀርባ አንድ ነገር እንዳለ እንደጠረጠረች ጭምር አጫወተቺኝ
ይህን የምትነግረኝ ኢነብ፣አትሮኖስን፣ እና አያቴን ሳሎን ከኢርቫ አክስት ጋር አጋትረን ምግብ እናዘጋጅ በሚል ሰበብ ነው ግን ቀን በቀን የምታገኟትን እናታችሁን አግብታችሁ ስታገኟት ልክ ጓደኛዋ ነው የምትሆኑት ስንሳሳቅ ነበር ስለራሷ የማላውቃቸውን ብዙ ነገሮች አጫወተቺኝ እና የማብሰሉን ነገር ጨርሰን ምግቡን አቀረብን አያቴ እና የኢርቫ አክስት የሆነ ጊዜ ግንኙነት ኖሯቸው የተለያዩ እስከሚመስሉ ድረስ ተግባብተው መነጋገራቸው ይደንቅ ነበር
መንሱረት እና አትሮኖስም እንደዛው ኢነብ እና አይመን ግን መግባባት ያቃታቸው ይመስላል ኢርቫን ከመሃከላቸው አስገብተው ከዳር እና ዳር ያወራሉ እና እኔ እና እናቴ ሰፊ ሰዓት አገኘን እላችኋለሁ የማናወራው ነገር አልነበረም አሱርን እኛው ቤት ሰግደው ለመሄድ ተነሱ እስከ ኢነብ መኪና ድረስ ልሸኛቸው ብዬ ልብስ ለመደረብ ወደ ክፍሌ ገባሁ መለስ ብዬ አብሬያቸው ብሄድ አልኩ ከእነሱ ከተለየሁ 2ኛ ወር እየተጠጋ ነው
<<ኢርቫ ዛሬ እነ ኡሚ ጋር ልደር ትፈቅድልኛለህ? ሌላ ጊዜ ማንም ስለማይኖር አብረን እንሄዳለን ዛሬን ግን አክስቴም ስላለች አይደብርህም ልሂድ እ…?…እሺ አትለኝም?>> አልኩት ትንሽ እንደማሰብ ካለ በኋላ
<<መርሃባ ነገ ግን በጊዜ ነይ>>
<<ኡፍፍፍ የኔ ውድ እንዴት እንደምወድህ እኮ ቻው በቃ>> ከቁም ሳጥኑ ጫማ አውጥቼ ከክፍሉ ልወጣ ስል
<<እቀፊኛ>>
<<ቻው>>አቀፍኩትና ደረጃውን እየተንደረደርኩ ወረድኩ
10 🥰 and
share
ይቀጥላል ☆ ☆ ☆. . . . . .
