Bashewam Primary & Junior School 1-8
Відкрити в Telegram
2 748
Підписники
-224 години
+207 днів
+4230 день
Архів дописів
የተከበራችሁ፡ወላጆች የልጆች ወርሃዊ፡የት/ት እና የትራንስፖርት ክፍያ፡በወቅቱ ባለመከፈሉ በጣም የተቸገርን ስለሆነ በዚህ ዓመት፡ጥቅምት ወር ጀምሮ፡የቅጣት መጠን የጨመረ መሆኑን፡ተገንዝባችሁ፡በወቅቱ እንድትከፍሉ እያሳሰብን በዚህም መሠረት ወር በገባ 1-10=ያለቅጣት
ከ11-15=250ብር
ከ16-20=300ብር
ከ21-30=500ብር ቅጣት የምናስከፍል ፡መሆኑን በጥብቅ እያሳሰብን፡የትራንስፖርት
ከቀን11-20=200ብር
ከ21-30=250ብር ይሆናል።
Repost from Bashewam Primary & Junior School 1-8
ውድ ወላጆች ሁለተኛ ዙር መፅሐፍ የከፈላችሁ በሙሉ ከ28/01/2018ዓም ጀምሮ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
Repost from Bashewam Primary & Junior School 1-8
ውድ የባሸዋም ት/ቤት የተማሪ ወላጆች፡አራት እና ከዚያ በላይ፡ተማሪ ለምታስተምሩ ብቻ፡የቅናሽ ክፍያ(discountpay)የምንመዘግበው ፡ከመስከረም 28-30/01/18ዓ.ም ብቻ መሆኑን፡አውቃችሁ በአካል በመገኘት፡ፎርም እንድትሞሉ እያሳወቅን፡ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውጪ፡የማናስተናግድ መሆኑን፡በጥብቅ እናሳስባለን።ማመልከቻ መፃፋችሁን አትርሱ።
ቀን 28/01/18 ዓ.ም
ባሸዋም ቅድመ አንደኛ አንደኛና መካከለኛ እና አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
ለውድ ወላጅ/አሳዳጊ ከ1ኛ- 4ኛ የትምህርት እርከን የተላለፈ መልዕክት
ተማሪዎች በማንኛውም ጊዜ ወደ ትምህርት ቤት ማምጣት የሌለባቸው ነገሮች
1. ብስኩት፣ ከረሜላ ፣ሰን ቺፕስ እና
ሌሎችም
2. የመጫወቻ ቁሳቁሶች
3.ያለ ወላጅ አውቅና ብር/ገንዘብ/
4.የአንገት እና የ እጅ ጌጣጌጥ
5.ብረታብረት እና ማንኛውም ስለታማ
ነገሮች
6. ስልክ እና ማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ
ቁሳቁሶች
7.ማንኛውም ከመማሪያ ውጪ የሆነ
ቁሳቁስ፡፡
ማሳሰቢያ
- ወላጆች የተማሪዎችን ምግብና ዉሀ ንፅህናው የተጠበቀ መሆኑን እንዲያረጋግጡ
ወላጆች የላክነውን መልዕክት ተግባራዊ እንድታደርጉ እናሳስባለን ::
School Administrator Checked by Bashewamy
ውድ ወላጆች ሁለተኛ ዙር መፅሐፍ የከፈላችሁ በሙሉ ከ28/01/2018ዓም ጀምሮ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
ውድ የባሸዋም ት/ቤት የተማሪ ወላጆች፡አራት እና ከዚያ በላይ፡ተማሪ ለምታስተምሩ ብቻ፡የቅናሽ ክፍያ(discountpay)የምንመዘግበው ፡ከመስከረም 27-29/01/18ዓ.ም ብቻ መሆኑን፡አውቃችሁ በአካል በመገኘት፡ፎርም እንድትሞሉ እያሳወቅን፡ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውጪ፡የማናስተናግድ መሆኑን፡በጥብቅ እናሳስባለን።
#SocialMedia
የ2018 ትምህርት ዘመን ሰኞ መስከረም 05 ቀን 2018 ዓ/ም እንደተጀመር ይታወቃል፡፡
በዲጂታል ዘመን በተማሪ ህይወት ላይ ትልቅ ተፅእኖ ከሚያሳድረው አንዱ ማህበራዊ ሚድያ ሲሆን እንደ ፦
- ቲክቶክ
- ኢንስታግራም
- ፌስቡክ
- X
- ቴሌግራም እና መሰል መተግበሪያዎችን ያለ አግባብ መጠቀም ትኩረትን ይቀንሳል ፣ የአካዳሚክ አፈጻጸምን ያዳክማል ፣ ጭንቀትና መሰል አሉታዊ የሆኑ ውጤቶችን ያመጣል።
ተማሪዎች ማህበራዊ ሚድያን ያለ አግባብ ሲጠቀሙ የሚገጥሟቸው ዋና ዋና ፈተናዎች ምንድን ናቸው ?
➡️ በኦንላይን የሚጠፋው ከልክ ያለፈ ጊዜ የተማሪዎችን ትኩረት እና ምርታማነትን ስለሚቀንስ ተማሪዎችን ወደ ደካማ የአካዳሚክ አፈፃፀም ያመራል፡፡
➡️ ከፍተኛ መጠን ያለው የስክሪን ጊዜ በተማሪዎች ላይ የስነ ልቦና ጫናን ያስከትላል።
➡️ በምሽት ማህበራዊ ሚዲያን አብዝቶ መጠቀም እንቅልፍ ለመተኛት እና ጤናማ እረፍትን ለማድረግ ከባድ ስለሚሆን የማስታወስ ችግርን ያስከትላል እንዲሁም የመማር ችሎታን ይቀንሳል፡፡
➡️ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የአካባቢ እና የትምህርት ቤት ስሞችን ወይም ስልክ ቁጥሮች እና መሰል የግል መረጃዎችን ማጋራት ለመጭበርበር እና ለሳይበር ጥቃት በቀላሉ ተጋላጭ ያደርጋል።
ተማሪዎች አዲሱን የትምህርት ዘመን ሲጀምሩ ማህበራዊ ሚዲያን አግባብ ባለው መልክ እንዲጠቀሙ መውሰድ ያለባቸው መፍትሄዎች ምንድን ናቸው ?
📇 የስክሪን ጊዜን መገደብ እና ማህበራዊ ሚዲያን ከመጠቀማቸው በፊት ለትምህርት ቤት ስራ ቅድሚያ በመስጠት ትኩረትን የሚከፋፍሉ ነገሮችን መቀነስ።
📇 ማህበራዊ ሚዲያን እንደ መዝናኛ ብቻ ከመመልከት ይልቅ የትምህርት መሳሪያ በማድረግ የጥናት ቡድኖችን በመቀላቀል፣ የአካዳሚክ ገጾችን በመከተልና አዳዲስ ክህሎቶችን በመማር የትምህርት ጊዜን የተሳካ ማድረግ።
📇 ከቤተሰብ ጋር ጊዜ ማሳለፍ ፣ መጽሐፍ ማንበብ ወይም የስፖርት እንቅስቃሴን በማድረግ የተሻለ ማህበራዊ ህይወት ልምምድ ማዳበር።
#ማስታወሻ ፦ ትምህርት ሚኒስቴር መስከረም 05/2018 ዓ/ም ከተጀምረው የትምህርት ዘመን ጋር በተያያዘ ተማሪዎች ስልክን ጨምሮ ማንኛውም አይነት ኤሌክትሮኒክስ ቁሶችን ወደ ትምህርት ቤት ይዘው መምጣት እንደማይችሉ አስጠንቅቋል።
ማሳሰቢያ:- አርብ መስከረም 23/01/2018 የእሬቻ በዓል ዋዜማ እንግዶች በብዛት የሚገቡበት ቀን በመሆኑ ምክንያት መንገድ ሊዘጋጋ ስለሚችል ትምህርት የማይኖር መሆኑን እናሳዉቃለን::
ማሳሰቢያ:- ለተከበራችሁ የት/ቤታችን ዉድ ወላጆች በሙሉ::
ጉዳዩ:-የተማሪ መማሪያ መፅሐፍትን ይመለከታል::
በመማር ላይ ላሉ ልጆቻችሁ የመማሪያ መፅሐፍት እንድታሟሉ በተደጋጋሚ መልእክት መላካችን የታወቃል:: በመሆኑም እስካሁን ክፍያ ያልፈፀማችሁ ወላጆች ተማሪው ያለመፅሐፍ መማር የማይቻል ስለሆነ እስከ ቀን 23/01/2018ዓ. ም ድረስ በአካል በመቅረብ ክፍያ ፈፅማችሁ እንድታሟሉ በአክብሮት እያሳወቅን ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚፈጠረዉ ችግር ት/ቤቱ ኃላፊነቱን የማይወስድ መሆንኑን እናሳውቃለን
ማሳሰቢያ :-ለተከበራችሁ የት/ቤታችን ወላጆች የመጀመሪያ ዙር የመፅሐፍ ክፍያ የፈፀማችሁ መፅሐፍት የመጣ ስለሆነ ነገ በቀን 14/01/2018 ዓ.ም ከ 2:30-10:00 ባለዉ ጊዜ ት/ቤት በመምጣት እንድትወስዱ ስንል በአክብሮት እናሳዉቃለን::
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
