uk
Feedback
Secrets of Truth - 𝘜𝙮 𝙍𝙚𝙚𝙝𝙖𝙙

Secrets of Truth - 𝘜𝙮 𝙍𝙚𝙚𝙝𝙖𝙙

ВіЎкрОтО в Telegram

● ዲናቜንና በሚመለኚት ወቅታዊ መሚጃዎቜን ➶ Current information about Muslims and Islam 🔗 ሌሎቜንም አንገብጋቢ ጉዳዮቜን ዚምንተዋወስበት Channel ነው‌ ➞ በወቅታዊ ጉዳዮቜ ላይ አጠር ያሉ ስንኞቜ (በተለይም ስለ ፈለስጢን 🇵🇞) 🎯 አላማዬ:- ዚእውነትን ሚስጥሮቜ ማጋለጥ ነው‌ #Free_Palestine 🇵🇞

ППказатО більше
213
ПіЎпОсМОкО
НеЌає ЎаМОх24 гПЎОМО
-17 ЎМів
-430 ЎМів
Архів ЎПпОсів
ዚዘካህ ህግጋት አጭር ማብራሪያ‌ ======================== ዚተሻሻለ አዲስ እትም (ሚመዿን 1445 ዓ.ሂ) 📖 ዹ pdf ፋይል በሞይኜ ኢልያስ አሕመድ ♠ አሪፍ መሹጃ ታገኙበታላቜሁፀ አንብቡት። || t.me/MuradTadesse

ዹ2 ፎቶዎቜ ወግ‌ ============= ✍ ፎቶ ①: ዹአምቩ ዩኒቚርስቲ ተማሪ ናቾው ዚተባሉ ወጣቶቜ በታቊት ተሳልቀዋል ተብሎ ድርጊቱን ለማውገዝ ዚኢትዮጵያ ዚኃይማኖት ተቋማት ጉባኀ መግለጫ ሲሰጥፀ ጉዳዩ በቀጥታ ዚማይመለኚታ቞ው እንደ ሃሩን ሚዲያ ያሉ ኢስላማዊ ሚዲያዎቜ ተገኝተዋል። ፎቶ ②: ዚኊርቶዶክስ ክርስትና እምነት ሰባኪ ነው ዚተባለ ግለሰብፀ እንኳን ኃይማኖተኛ ነኝ ኹሚል እልል ካለ ዱርዬ ዹማይጠበቁ ጞያፍ ቃላትን በመጠቀም ሙስሊሞቜን ያስቆጣ ነውሹኛ ስድብ በመሳደቡ ዚተነሳ ድርጊቱን ለማውገዝ በዛሬው ዕለት ዚሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ መግለጫ ሲሰጥ ዚነበሩ ሚዲያዎቜን ያሳያል። በደብዳቀው ላይ ጥሪ ኹተደሹገላቾውና በሃገሪቱ ዚሚያ ባለ ስልጣን ዕውቅና ካላ቞ው መካኚልፀ ዚሃገሪቱ ቲቪ EBC በቊታው አልተገኘም። በተጚማሪም ኚኢልያስ መሠሚት ዚባሰቜው አስመሳይ "ቅመሟ" አሐዱ ቲቪና ሬዲዮ እንዲሁም ናሁ ቲቪ አልተገኙም። ሁሉም ዚኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ሚዲያዎቜ በቊታው ዚሉም። ይህ በተዘዋዋሪ ለልጁ ዹተደሹገ አጋርነት (implicit backing)) ነው ማለት ይቻላል። ለልጁም ዚብልግና ስድብና ዚጥላቻ ቅስቀሳ ዕውቅና እንደመስጠት (endorsement) ሊቆጠር ይቜላል። ዚሃገሪቱ ቲቪ በህዝበ ሙስሊሙም ግብር ዚሚተዳደር ሆኖ ሳለ በእንዲህ አይነት መድሚክ ላይ አለመገኘቱ ግደለሜነቱንና ንቀቱን አለፍ ሲልም ጥላቻውን ዚሚያሳብቅ ኹመሆኑ ባሻገርፀ ያልተገኘበትን መግለጫ አውዱን አጣሞና አንሻፎ መዘገቡ ለህዝበ ሙስሊሙ ግልፅ መልዕክትና ትዝብት አስተላልፎ አልፏል። ያም አለ ይህ
 እንደስኚዛሬው በብ቞ኝነት ዚሚዲያ ዚበላይነትን በመቆናጠጥ ለግል ቡድን ጥቅም በሚያስገኝ መልኩ አውዱን ቀይሮ መዘገብ ድሮ ቀርቷል። ዚእናንተን ዚሰዓታት ድስኩር በደቂቃዎቜ ገመናውን ዚሚያወጣ ትውልድና ዘመን ተኚስቷል። ምስጋና ለአላህ
 ኹናንተ ቁጥጥር ውጭ ዹሆነ ማኅበራዊ ሚዲያ ዚሚባል አለ። ራሳቜሁን ትዝብት ላይ ትጥላላቜሁ እንጂ ኚእንግዲህ እውነትን በማድበስበስ በብ቞ኝነት ሚዲያውን ሟፍሮ ህዝብን ማሳሳት አይሠራም። ኢንሻ አላህ እንታገላቜኋለን። ©ሙራድ ታደሰ

አላህ ይብቃን! በዚህ በተኹበሹ ወር ኚዒባዳቜንም አዘናጉን! እነርሱን መታገልን አላህ ኚዒባዳህ ይቁጠርልን! እነሆ ዛሬ ዹተኹበሹው ወርሃ ሚመዿን 12ኛ ሌሊት ላይ እንገኛለን። ዚተራዊሕ ጀማዓህ እንዳትቀንሱ። እንዳማሚብን እስኚ መጚሚሻው ኢንሻ አላህ። አላህ ዚሚሚዳን በትክክል ስንገዛው ነው።

"ዚእስልምናን መልካም እሎቶቜን ዹሚሾሹሾር በጥላቻ ዹተመሹዘ እና በእስልምና ሀይማኖት ተኚታዮቜ ዘንድ ኹፍተኛ  ክብር ያላ቞ውን ነቢዩ መሐመድን "ï·º" መዝለፍ ኚባድ ዋጋ እንደሚያስኚፍል ሁሉም ወገን ሊያውቀው ይገባል" 🔖 በድር ኢትዮጵያ - ሀሩን ሚዲያ፣ መጋቢት 2/2017 መቀመጫውን በሀገሹ ሰሜን አሜሪካ ያደሚገው በድር ኢትዮጵያ አለም አቀፉ ዚኢትዮጵያውያን ሙስሊሞቜ ድርጅት ኹሰሞኑ በነብያቜ ላይ ድንበር ያለፈ ግለሰብን አስመልክቶ ተኚታዩን መግለጫ አውጥቷልፊ "ሰሞኑን አንድ ግለሰብ ዚታላቁ ነቢያቜንን (ሰ.ዐ.ወ) ስም አንስቶ በመዝለፍ ዹሹጹው መርዝ ዚታሰበበትና በዕቅድ ዹተኹናወነ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ሀገሪቱ ኚገባቜበት ዚመኚራ አዙሪት ሣትወጣ ሌላ ዚሐይማኖት ግጭት ለመፍጠር ዹተፈፀመውን ድርጊት በድር ዓለም-አቀፍ ዚኢትዮጵያ ሙሰሊሞቜ ድርጅት አጥብቆ ያወግዛል። ዚእስልምናን መልካም እሎቶቜን ዹሚሾሹሾር በጥላቻ ዹተመሹዘ እና በእሰልምና ሀይማኖት ተኚታዮቜ ዘንድኚፍተኛ ክብር ያላ቞ውን ነቢዩ መሐመድን (ሰ.ዐ.ወ)መዝለፍ ኚባድ ዋጋ እንደሚያሰኚፍል ሁሉም ወገን ሊያውቀው ይገባል ዚእሰልምና ሀይማኖት በኢትዮጵያ ዚማህበሚሰብ ታሪክ ውሰጥ ለ14 ምዕተ አመታት ጠንካራ ህዝባዊ መሠሚት ያለው ኹመሆኑም ባሻገር ዚሀገሪቱ ግማሾ ቁጥር ዹሚሆነው ህዝብ ዹሚኹተለው በመሆኑ ጊዜ እዚተጠበቀና በተለያዚ ዘዮ ዚሚፈፀምበት ዚጥላቻ ዘመቻ ትዕግሰቱን ክፉኛ እዚተፈታተነው ይገኛል በታላቁ ነቢያቜን (ሰ.ዐ.ወ)ላይ ዘለፋ ዹፈፀመውም ሆነ ተኚታዮቹ ዚሀገሪቱ ህግ በሚያዘው መሠሚት ምንም እርምጃ ባለመወሰዱ በድር ኢትዮጵያ እያዘነ ለምጣዱ ደህንነት ሲባል አይጧ ትለፍ ብሎ ዚታገሰው ሙሰሊም ወደሌላ እርምጃ ኚመሄዱ በፊት ዹሚመለኹተው አካል ለጉዳዩ ትኩሚት እንዲሰጠውና ሁሉም ወገን እንዲያወግዝ እዚጠዚቀ በድር ኢትዮጵያ ዹሚኹተለውን መግለጫ አውጥቷል። 1ኛ- ሀሣብን በነፃነት በመግለፅ ሰም ዹተጀመሹው ፀሹ እሰልምና ዘመቻ በአሰ቞ኳይ እንዲቆም እንዲደሚግ 2ኛ -መንግሰት ዚህዝብን እምነት በማንቋሾሾ ግጭት እንዲፈጠር ዚሚያነሣሡ ለሐገር ሰላም ጠንቅ ናቾዉና ቁጥጥር ሊያደርግባ቞ው ይገባል 3ኛ- ዚጥላቻ መርዝ ጠንሳሹና ነቢዩ ሙሀመድን(ሰአወ) ዹዘለፈው ግለሰብ ለህግ ቀርቩ አሰተማሪ ቅጣት እንዲያገኝ እንዲደሚግ 4ኛ-"መሠል ድርጊቶቜ ኹአሁን በኋላ እንዳይፈፀሙ መንግሰትና ባለድርሻ አካላት ዚበኩላ቞ውን እንዲወጡ እያሳሰበ ሀይማኖት ዚግለሰብና ዚቡድን ምርጫ ነፃነት በመሆኑ ዚእምነት ምርጫና ነፃነት ፀንቶ እንዲቆይ በድር ዓለም ዐቀፍ ዚኢትዮጵያ ሙስሊሞቜ ድርጅት ዚበኩሉን እንደሚወጣ ይገልፃል ሲል መግለጫውን ቋጭቷል። © ሀሩን ሚዲያ

አንድ ሰው ነብኑን (ሶለላሁ አለይሂ ወሰልም) አንቱ ዹአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ጌታዬን እንዎት አድርጌ ልጠይቀው (ልማፀነው)? ብሎ ሲጠይቃ቞ው እንዲህ በል አሉትፊ “አላህ ሆይ! ማሚኝ፣ እዘንልኝ፣ ጀነ
አንድ ሰው ነብኑን (ሶለላሁ አለይሂ ወሰልም) አንቱ ዹአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ጌታዬን እንዎት አድርጌ ልጠይቀው (ልማፀነው)? ብሎ ሲጠይቃ቞ው እንዲህ በል አሉትፊ “አላህ ሆይ! ማሚኝ፣ እዘንልኝ፣ ጀነኛ አድርገኝ፣ ሲሳይን ለግሰኝ”!! ▲ ይህ ዚዱንያና ዚአኺራ ጉዳዮቜን ላንተ ጠቅልሎ ይዞልሃል። #ሙስሊም_ዘግበውታል ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ እናም ተማሪዎቜ አርአያቜን ዹአላህን መልዕክተኛ (ሶለላሁ አለይሂ ወሰልም) ናቾውና እኛም ሁሌም ይህንን ዱዓ እናድርግ። ጌታቜንን ተናንሰን እንማፀነው‌ ልብ ልንል ዚሚገባን ነገር ቢኖር:- እኛ ጥሚት እያደሚግንም ሆነ ጥሚት ካደሚግን በኋላ መመካት ያለብን በጥሚታቜን ((በልፋታቜን)) ሳይሆን በአላህ ነው። በአላህ በመመካት እሱ (አላህ) እንዲያሳካልን ሁሌም ልንለምነው ይገባል። «በአላህ ፍቃድ ይሳካልኛል፣ ጥሩ ውጀት አመጣለሁ» በማለት ንባባቜንን አጠናክሹን መቀጠል አለብን‌ ⭕ አደራቜሁን መልዕክቱን ለሁሉም ተማሪዎቜ አድርሱልኝ። ✍ በናተው ወንድም ሚሻድ ኢብኑ ሙዘሚል

"ሰላት ተራዊሕ ወይም ተሀጁድ ላይ ለወላጆቜህ ዱዓ ማድሚግህ ፀ አሥር ግመሎቜን አርደህ ሰደቃ ኚማውጣት ይበልጣል።" #ሞይኜ_ኡሰይሚን
"ሰላት ተራዊሕ ወይም ተሀጁድ ላይ ለወላጆቜህ ዱዓ ማድሚግህ ፀ አሥር ግመሎቜን አርደህ ሰደቃ ኚማውጣት ይበልጣል።" #ሞይኜ_ኡሰይሚን

report አደራሚጉ በግልፅ ዚሚያሳይ በቪዲዮ ስክሪን ሪኚርድ አድርጎ አንድ ሰው @Murad_Tadesse ላይ ይላክልኝ። ቪድዮው ኹዚህ ዚተሻለ ይሁን። በያንዳንዱ ስ቎ፕ ዚሚነካውን አማራጭ በግልፅ ጞዳ ባለ መልኩ በምልክት ዚሚያሳይ ይሁን። እስኚዛው ስ቎ፑ ዚገባቜሁ ደጋግማቜሁ ሪፖርት አድርጉ። https://t.me/MuradTadesse/40353?single ልብ በሉ! ሪፖርት ለማድሚግ follow ማድሚግ አይጠበቅባቜሁም። ፎሎወሩ እዚጚመሚ ያለውፀ ሊያዘጉበት ነው ብለው ተጠራርተው ኮፒ ሊንክ እያስባሉ ስለሆነ ነው። ሳንቀደም እንቅደም። እነርሱም በጎድን ኮፒ ሊንክ በማድሚግ ስለወጠሩ እናንተም በሪፖርት ወጥሩ! ልብ በሉ! ሪፖርት ለማድሚግ ዚግድ ዚቲክቶክ አካውንት ሊኖራቜሁ አይገባም።

ኚአንድ በላይ ደጋግሞ ሪፖርት ማድሚግ ስለሚቻል ወጥሩ። ውጀት ዚሚያመጣው ደጋግሞ ሲደሚግና ብዛት ሲኖሚው ነው። ጎን ለጎን ዚክርና ዱዓቜሁን እያደሚጋቜሁ በእጃቜሁ ሥራቜሁን ሥሩ። ኒያቜንን ካሳመርን ይ
ኚአንድ በላይ ደጋግሞ ሪፖርት ማድሚግ ስለሚቻል ወጥሩ። ውጀት ዚሚያመጣው ደጋግሞ ሲደሚግና ብዛት ሲኖሚው ነው። ጎን ለጎን ዚክርና ዱዓቜሁን እያደሚጋቜሁ በእጃቜሁ ሥራቜሁን ሥሩ። ኒያቜንን ካሳመርን ይህም አንድ ኾይር ሥራ ነው። በርቱ! (ማነህ ግራፊክ ዚምትቜል፣ ኹላይ ባሉት ፎቶዎቜ ያስቀመጥኳ቞ውን ስ቎ፖቜፀ ቁጥር አጻጻፉንና በመክበብ ማሳያውን ጜድት አድርገህ ላክልኝ።)

ልብ በሉ! ተራ ቁጥር 3 ላይ እንዳኚበብኩትፀ Report ማድሚግ ያለባቜሁ አካውንቱን እንጁ ኮንተንት አይደለም። ሲቀጥል ተሳስታቜሁም ቢሆን follow እንዳታደርጉ። በዚህ ሊንክ እንደት ሪፖርት እንደ
ልብ በሉ! ተራ ቁጥር 3 ላይ እንዳኚበብኩትፀ Report ማድሚግ ያለባቜሁ አካውንቱን እንጁ ኮንተንት አይደለም። ሲቀጥል ተሳስታቜሁም ቢሆን follow እንዳታደርጉ። በዚህ ሊንክ እንደት ሪፖርት እንደሚደሚግ ዝርዝሩን ታገኛላቜሁ። https://t.me/MuradTadesse/40353?single ሳትሰለቹ ደጋግማቜሁ ሪፖርት አድርጉ። መጚሚሻ ላይ ስትደርሱ ያለውን ስክሪን ሹት አድርጉትና ኮመንት ላይ ላኩት። ወጥሩ! በዙሪያቜሁ ያሉ ሰዎቜንም አካውንት እዚተጠቀማቜሁ ደጋግማቜሁ ሪፖርት አድርጉ። ሳናዘጋ ዘመቻው እንዳይቆም። አንድ እርምጃ ኹዚህ እንጀምር። ልብ በሉ! ሪፖርት ዹሚደሹገው አካውንት ኹላይ ባለው ፖስት ያስቀመጥኩት ዚቲክቶክ ሊንክ ነው። ቲክቶክ ላይ ሰርጭ ብታደርጉ ብዙ ተመሳስሎ ዹተኹፈተ አካውንት ስለሚመጣፀ ኹላይ ሊንኩ ላይ ያለውን ሪፖርት አድርጉ።

ሚመዿን 10 🌙 تدؚر القرآن 🌙 ቁርዓንን ማስተንተን ሚመዿን ቢናገር ኑሮ ሰዎቜ ዚሐዲስ፣ ዹፊቅህ እንዲሁም ዚተውሂድን ኪታቊቜን ትተው ቁርዓንን በማንበብ ሲጠመዱ አይቻለሁ ይል ነበር ታዲያ እኔ እና አንተን ምንድነው ኹቁርዓን ያዘናጋን? ሚመዿን ቢናገር ኑሮ እንዲህ ይል ነበር ፊ وَقَالَ الرَّسُولُ يَا رَؚِّ إِنَّ قَوْمِي اتَّخَذُوا هَٰذَا الْقُرْآنَ مَهْجُورًا መልክተኛውም «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቊቌ ይህንን ቁርኣን ዹተተወ ነገር አድርገው ያዙት» አለ፡፡ ውድ ወንድሜ ፣ውድ እህ቎ ኹዚህ ቀደም በ ሚጀብ ወይም ደግሞ በሞዕባን ቁርዓንን  ማንበብ ዹተውክ/ሜ ኹነበርክ/ሜ አስተወይ ይህን ؎َهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وََؚيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ (እንድትጟሙ ዚተጻፈባቜሁ) ያ በርሱ ውስጥ ለሰዎቜ መሪ ኹቅን መንገድና (እውነትን ኚውሞት) ኚሚለዩም ገላጮቜ (አንቀጟቜ) ሲኟን ቁርኣን ዚተወሚደበት ዚሚመዿን ወር ነው፡፡ ታዲያ ቅኑን መንገድ መርቶሃልን? ዚእወነቱን መንገድን አመላክቶሃልን? ኹወንጀል ወደ አላህ መሃርታን ኚማግኘት ዹተቀዹርክ ሰው አድርጎሃልን? ال؎يخ : عؚدالمحسن الأحمد -حف؞ه الله-

فوالله كاد قلؚي يطير!!!! ኢስላምን እንደሚገባው ዚበላይነት ለማድሚግ መልፋት ሲገባን ስጋዊ ስሜታቜንን ለማሟላት ስንሯሯጥ ዚበታቜነታቜን ተሹጋግጧል! በይፋም መሞታቜንም ተበስሯል....

" ኚነፍሳቜን በላይ አብልጠን በምንወዳ቞ው ውዱ ነብያቜን ክብር ዚማንደራደር መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል።" ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ም/ቀት ዚፕሬዝዳንት ፅ/ቀት ሀላፊ ኡስታዝ አቡበኚር
" ኚነፍሳቜን በላይ አብልጠን በምንወዳ቞ው ውዱ ነብያቜን ክብር ዚማንደራደር መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል።" ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ም/ቀት ዚፕሬዝዳንት ፅ/ቀት ሀላፊ ኡስታዝ አቡበኚር አህመድ ኹሰሞኑ በውዱ ነብያቜን ላይ በተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎቜ ድምበር ዚሚያልፉ ግለሰቊቜን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል። ዚፉሪ ክፍለ ኹተማ እስልምና ጉዳዮቜ ም/ቀት ኚኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶቜ ካውንስል ጋር በመተባበር ዹተዘጋጀ ዚዳዕዋ መድሚክ በርካታ ሙስሊሞቜ በተገኙበት መልዕክት ያስተላለፉት ኡስታዝ አቡበኚር አህመድ "ኚነፍሳቜን በላይ አብልጠን በምንወዳ቞ው ውዱ ነብያቜን ክብር ዚማንደራደር መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል" ሲሉ ተናግሚዋል። "እኛ እምነታቜን በምናስተምርበት ወቅት ፈፅሞ ዚሰዎቜ እምነት ላይ ድንበር አናልፍም እስልምናም ያንን አያዘንም ያሉ ሲሆን ሌሎቜ ዚእምነት ተቋማትም ድንበር ዚሚያልፍ ግለሰቊቜን ተው ሊሉ ይገባል" ብለዋል። "እንደ ተቋም በህግ መሄድ እስለብን ጥግ ድሚስ እንሄዳለን ያሉ ሲሆን ሙስሊሙ ማህበሚሰብ በተለይ ወጣቱ በሰላማዊ መንገድ እምነቱን ማስኚበር አለበት" ሲሉ ገልፀዋል።

ما ؎اء الله تؚارك الله. في لفتة أؚوية حانية .. ال؎يخ عؚدالرحمن السديس يستضيف الأؚناء الأيتام وأسرهم المحتضنة على ما؊دة الإفطا
+1
ما ؎اء الله تؚارك الله. في لفتة أؚوية حانية .. ال؎يخ عؚدالرحمن السديس يستضيف الأؚناء الأيتام وأسرهم المحتضنة على ما؊دة الإفطار في الحرم المكي ال؎ريف. In a kind fatherly gesture, Sheikh Abdul Rahman Al-Sudais hosts orphans and their foster families at the Iftar table in Masjid Al Haram, Makkah.

አርቲስቱ እያለቀሰ ይናገራል‌ || t.me/MuradTadesse

ፖሊስነት በናንተ በቃ!🫡

🌿🌿🌿🍃ጥቆማ🍃🌿🌿🌿 "ዚውሻ ጩኞት ደመናን አይጎዳም!" ~ በነብያቜን ï·º ላይ ዚሚሳለቅ ራሱን እንጂ እሳ቞ውን ምንም ሊያደርጋ቞ው አይቜልም። ዚላካ቞ው አምላክ "መወሳትህን/ዝናህን ኹፍ አደሹግንልህ" ብሏ቞ዋል። ይሄው ዹዝናቾው ኹፍ ማለትም ነው ዛሬ በርካታ ውሟቜን እያስጮኻ቞ው ያለው። ትላንትም ዚዛሬዎቹ ውሟቜ አያቶቜ ዚመልእክተኛውን ክብር ሊያንቋሜሹ ሞክሹው ነበር። አላህ ግን ራሱ ለመልእክተኛው ï·º ተኚላካይ ጠበቃ ይሆንና መልእክተኛው ግን ነገሩን ንቀው እንዲተውት እንዲህ ይጠቁማ቞ዋል፡- (فَٱصۡدَعۡ ؚِمَا تُ؀ۡمَرُ وَأَعۡرِضۡ عَنِ ٱلۡمُ؎ۡرِكِینَ ۝  إِنَّا كَفَیۡنَـٰكَ ٱلۡمُسۡتَهۡزِءِینَ ۝  ٱلَّذِینَ یَجۡعَلُونَ مَعَ ٱللَّهِ إِلَـٰهًا ءَاخَرَۚ فَسَوۡفَ یَعۡلَمُونَ ۝  وَلَقَدۡ نَعۡلَمُ أَنَّكَ یَضِیقُ صَدۡرُكَ ؚِمَا یَقُولُونَ ۝  فَسَؚِّحۡ ؚِحَمۡدِ رَؚِّكَ وَكُن مِّنَ ٱلسَّـٰجِدِینَ ۝  وَٱعُؚۡدۡ رََؚّكَ حَتَّىٰ یَأۡتِیَكَ ٱلۡیَقِینُ) "ዚታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለፅፀ አጋሪዎቜንም ተዋ቞ው። እኛ ተሳላቂዎቜን ሁሉ በቅተነሃል። (እነሱም) እነዚያ ኹአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደሚጉ ና቞ውፀ በርግጥም (ዚስራ቞ውን ዋጋ) ወደፊት ያውቃሉ። አንተም በሚሉት ነገር ልብህ ዚሚጠብ መሆኑን በርግጥም እናውቃለን። ጌታህንም ኚማመስገን ጋር አጥራውፀ ኚሰጋጆቹም ሁን። እውነቱም (ሞት) እስኚሚመጣህ ድሚስ ጌታህን አምልክ።" [አልሒጅር፡ 94-99] ስለዚህ ተሳላቂዎቹ ውሟቜ ቢሳለቁም ዚነብያቜን ï·º ዝና ዹበለጠ ይገናል። ዚውሟቹ ስም ይኚስማል። ውሻ ደግሞ ምን ታሪክ አለውና?! እስኪ ዚነብያቜንና ዚትላንት ጠላቶቻ቞ውን ዝና አወዳድሩ። ሲጀመር መወዳደር ይቜላሉ? በጭራሜ! “ዹሰማይና ዚመሬት ያክል ነው” ብንል እንኳ በትክክል አይገልፀውም። ግን ዚነብያቜንን ï·º ክብር ለማጉደፍ ተፍ ተፍ ዹሚሉ ሰዎቜ አላማቾው ምን ይሆን? መልሱ ግልፅ ነው። 1.  አንዳንዶቹ በነብዩ ï·º እውቅና ሂሳብ እውቅና መሞመት ዹሚፈልጉ ና቞ው። “አንዳንዶቜ ታዋቂዎቜን በመተ቞ት ታዋቂ መሆን ይፈልጋሉ” ሲባል አልሰማቜሁም? 2.  ሌሎቹ ደግሞ ዚኢስላም ውበቱና ሁለንተናዊነቱ ዚሚያስቀና቞ውፀ ኹፍተኛ ግስጋሎው ዚሚያስበሚግጋ቞ው ና቞ው። ስለሆነም ሙሐመድን ï·º ሲያንቋሜሹ ዚኢስላም ውበቱ ዚሚደበዝዝ፣ ግስጋሎው ዚሚገታ ይመስላ቞ዋል። እውነታው ግን ተቃራኒው ነው። ኢስላም ዛሬ ጠላቶቹን እንቅልፍ በሚነሳ መልኩ በኹፍተኛ ፍጥነት እዚገሰገሰ ነው። ስለዚህ ውሟቹ አመል ሆኖባ቞ው ይጮሃሉ እንጂ ዚኢስላምን ግስጋሎ ሊገቱት አይቜሉም! ውሟቹ ይጮሃሉ፣ ዋው! ዋው! እያሉ። ግመሉ ግን ጉዞውን ቀጥሏል። ውሻ ግመልን ማስቆም ኚቻለቜ ትሞክር። ባይሆን ኚእኛ አንድ ነገር ይጠበቃል። ኚሃዲዎቜን ዚነብያቜንን ï·º ስም ለመዘለፍ ያበቃ቞ው ለነብዩ አስተምሮ ያላ቞ው ጥላቻ መሆኑ ይታወቃል። አዎ ዚነቢዩ ï·º ሱና እጅጉን ያስቆጫ቞ዋል! እውነቱ ይህ ኹሆነ ኚሃዲዎቜን ዹበለጠ ለማስቆጚት ዚሚጓጓፀ ለሙሐመድ ï·º እውነተኛ ወዳጅነቱን ማንፀባሚቅ ዚሚፈልግ፣ ብሎም ዹአላህን ውዎታ ማትሚፍ ዚሚሻ ዹበለጠ ወደ መልእክተኛው ሱና ይቅሚብ። ትእዛዛ቞ውንም ይፈፅም። ኚኚለኚሉትም ይራቅ። ይህን ዚሚያደርግ ጠላቱን ዹበለጠ ያስቆጫል። ዹአላህንና ዹመልክተኛውንም ï·º ውዎታ ያፍሳል። ያ ሱብሓላህ! ዹአላህና ዹመልክተኛውን ውዎታ ያገኘ ምን ዚቀሚበት ነገር አለ?! ያ ወሃ፞ቡ አንተ ወፍቀን! ኣሚን ✍IbnuMunewor https://t.me/ibnukedir