es
Feedback
Secrets of Truth - 𝘽𝙮 𝙍𝙚𝙨𝙝𝙖𝙙

Secrets of Truth - 𝘽𝙮 𝙍𝙚𝙨𝙝𝙖𝙙

Ir al canal en Telegram

● ዲናችንና በሚመለከት ወቅታዊ መረጃዎችን ➶ Current information about Muslims and Islam 🔗 ሌሎችንም አንገብጋቢ ጉዳዮችን የምንተዋወስበት Channel ነው‼️ ➞ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አጠር ያሉ ስንኞች (በተለይም ስለ ፈለስጢን 🇵🇸) 🎯 አላማዬ:- የእውነትን ሚስጥሮች ማጋለጥ ነው‼️ #Free_Palestine 🇵🇸

Mostrar más
213
Suscriptores
Sin datos24 horas
-17 días
-430 días
Archivo de publicaciones
የዘካህ ህግጋት አጭር ማብራሪያ‼ ======================== የተሻሻለ አዲስ እትም (ረመዿን 1445 ዓ.ሂ) 📖 የ pdf ፋይል በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ ♠ አሪፍ መረጃ ታገኙበታላችሁ፤ አንብቡት። || t.me/MuradTadesse

የ2 ፎቶዎች ወግ‼ ============= ✍ ፎቶ ①: የአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ናቸው የተባሉ ወጣቶች በታቦት ተሳልቀዋል ተብሎ ድርጊቱን ለማውገዝ የኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መግለጫ ሲሰጥ፤ ጉዳዩ በቀጥታ የማይመለከታቸው እንደ ሃሩን ሚዲያ ያሉ ኢስላማዊ ሚዲያዎች ተገኝተዋል። ፎቶ ②: የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ሰባኪ ነው የተባለ ግለሰብ፤ እንኳን ኃይማኖተኛ ነኝ ከሚል እልል ካለ ዱርዬ የማይጠበቁ ጸያፍ ቃላትን በመጠቀም ሙስሊሞችን ያስቆጣ ነውረኛ ስድብ በመሳደቡ የተነሳ ድርጊቱን ለማውገዝ በዛሬው ዕለት የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ መግለጫ ሲሰጥ የነበሩ ሚዲያዎችን ያሳያል። በደብዳቤው ላይ ጥሪ ከተደረገላቸውና በሃገሪቱ የሚያ ባለ ስልጣን ዕውቅና ካላቸው መካከል፤ የሃገሪቱ ቲቪ EBC በቦታው አልተገኘም። በተጨማሪም ከኢልያስ መሠረት የባሰችው አስመሳይ "ቅመሟ" አሐዱ ቲቪና ሬዲዮ እንዲሁም ናሁ ቲቪ አልተገኙም። ሁሉም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሚዲያዎች በቦታው የሉም። ይህ በተዘዋዋሪ ለልጁ የተደረገ አጋርነት (implicit backing)) ነው ማለት ይቻላል። ለልጁም የብልግና ስድብና የጥላቻ ቅስቀሳ ዕውቅና እንደመስጠት (endorsement) ሊቆጠር ይችላል። የሃገሪቱ ቲቪ በህዝበ ሙስሊሙም ግብር የሚተዳደር ሆኖ ሳለ በእንዲህ አይነት መድረክ ላይ አለመገኘቱ ግደለሽነቱንና ንቀቱን አለፍ ሲልም ጥላቻውን የሚያሳብቅ ከመሆኑ ባሻገር፤ ያልተገኘበትን መግለጫ አውዱን አጣሞና አንሻፎ መዘገቡ ለህዝበ ሙስሊሙ ግልፅ መልዕክትና ትዝብት አስተላልፎ አልፏል። ያም አለ ይህ… እንደስከዛሬው በብቸኝነት የሚዲያ የበላይነትን በመቆናጠጥ ለግል ቡድን ጥቅም በሚያስገኝ መልኩ አውዱን ቀይሮ መዘገብ ድሮ ቀርቷል። የእናንተን የሰዓታት ድስኩር በደቂቃዎች ገመናውን የሚያወጣ ትውልድና ዘመን ተከስቷል። ምስጋና ለአላህ… ከናንተ ቁጥጥር ውጭ የሆነ ማኅበራዊ ሚዲያ የሚባል አለ። ራሳችሁን ትዝብት ላይ ትጥላላችሁ እንጂ ከእንግዲህ እውነትን በማድበስበስ በብቸኝነት ሚዲያውን ሾፍሮ ህዝብን ማሳሳት አይሠራም። ኢንሻ አላህ እንታገላችኋለን። ©ሙራድ ታደሰ

አላህ ይብቃን! በዚህ በተከበረ ወር ከዒባዳችንም አዘናጉን! እነርሱን መታገልን አላህ ከዒባዳህ ይቁጠርልን! እነሆ ዛሬ የተከበረው ወርሃ ረመዿን 12ኛ ሌሊት ላይ እንገኛለን። የተራዊሕ ጀማዓህ እንዳትቀንሱ። እንዳማረብን እስከ መጨረሻው ኢንሻ አላህ። አላህ የሚረዳን በትክክል ስንገዛው ነው።

"የእስልምናን መልካም እሴቶችን የሚሸረሸር በጥላቻ የተመረዘ እና በእስልምና ሀይማኖት ተከታዮች ዘንድ ከፍተኛ  ክብር ያላቸውን ነቢዩ መሐመድን "ﷺ" መዝለፍ ከባድ ዋጋ እንደሚያስከፍል ሁሉም ወገን ሊያውቀው ይገባል" 🔖 በድር ኢትዮጵያ - ሀሩን ሚዲያ፣ መጋቢት 2/2017 መቀመጫውን በሀገረ ሰሜን አሜሪካ ያደረገው በድር ኢትዮጵያ አለም አቀፉ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ድርጅት ከሰሞኑ በነብያች ላይ ድንበር ያለፈ ግለሰብን አስመልክቶ ተከታዩን መግለጫ አውጥቷል፦ "ሰሞኑን አንድ ግለሰብ የታላቁ ነቢያችንን (ሰ.ዐ.ወ) ስም አንስቶ በመዝለፍ የረጨው መርዝ የታሰበበትና በዕቅድ የተከናወነ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ሀገሪቱ ከገባችበት የመከራ አዙሪት ሣትወጣ ሌላ የሐይማኖት ግጭት ለመፍጠር የተፈፀመውን ድርጊት በድር ዓለም-አቀፍ የኢትዮጵያ ሙሰሊሞች ድርጅት አጥብቆ ያወግዛል። የእስልምናን መልካም እሴቶችን የሚሸረሸር በጥላቻ የተመረዘ እና በእሰልምና ሀይማኖት ተከታዮች ዘንድከፍተኛ ክብር ያላቸውን ነቢዩ መሐመድን (ሰ.ዐ.ወ)መዝለፍ ከባድ ዋጋ እንደሚያሰከፍል ሁሉም ወገን ሊያውቀው ይገባል የእሰልምና ሀይማኖት በኢትዮጵያ የማህበረሰብ ታሪክ ውሰጥ ለ14 ምዕተ አመታት ጠንካራ ህዝባዊ መሠረት ያለው ከመሆኑም ባሻገር የሀገሪቱ ግማሸ ቁጥር የሚሆነው ህዝብ የሚከተለው በመሆኑ ጊዜ እየተጠበቀና በተለያየ ዘዴ የሚፈፀምበት የጥላቻ ዘመቻ ትዕግሰቱን ክፉኛ እየተፈታተነው ይገኛል በታላቁ ነቢያችን (ሰ.ዐ.ወ)ላይ ዘለፋ የፈፀመውም ሆነ ተከታዮቹ የሀገሪቱ ህግ በሚያዘው መሠረት ምንም እርምጃ ባለመወሰዱ በድር ኢትዮጵያ እያዘነ ለምጣዱ ደህንነት ሲባል አይጧ ትለፍ ብሎ የታገሰው ሙሰሊም ወደሌላ እርምጃ ከመሄዱ በፊት የሚመለከተው አካል ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠውና ሁሉም ወገን እንዲያወግዝ እየጠየቀ በድር ኢትዮጵያ የሚከተለውን መግለጫ አውጥቷል። 1ኛ- ሀሣብን በነፃነት በመግለፅ ሰም የተጀመረው ፀረ እሰልምና ዘመቻ በአሰቸኳይ እንዲቆም እንዲደረግ 2ኛ -መንግሰት የህዝብን እምነት በማንቋሸሸ ግጭት እንዲፈጠር የሚያነሣሡ ለሐገር ሰላም ጠንቅ ናቸዉና ቁጥጥር ሊያደርግባቸው ይገባል 3ኛ- የጥላቻ መርዝ ጠንሳሹና ነቢዩ ሙሀመድን(ሰአወ) የዘለፈው ግለሰብ ለህግ ቀርቦ አሰተማሪ ቅጣት እንዲያገኝ እንዲደረግ 4ኛ-"መሠል ድርጊቶች ከአሁን በኋላ እንዳይፈፀሙ መንግሰትና ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ እያሳሰበ ሀይማኖት የግለሰብና የቡድን ምርጫ ነፃነት በመሆኑ የእምነት ምርጫና ነፃነት ፀንቶ እንዲቆይ በድር ዓለም ዐቀፍ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ድርጅት የበኩሉን እንደሚወጣ ይገልፃል ሲል መግለጫውን ቋጭቷል። © ሀሩን ሚዲያ

አንድ ሰው ነብኑን (ሶለላሁ አለይሂ ወሰልም) አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ጌታዬን እንዴት አድርጌ ልጠይቀው (ልማፀነው)? ብሎ ሲጠይቃቸው እንዲህ በል አሉት፦ “አላህ ሆይ! ማረኝ፣ እዘንልኝ፣ ጤነ
አንድ ሰው ነብኑን (ሶለላሁ አለይሂ ወሰልም) አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ጌታዬን እንዴት አድርጌ ልጠይቀው (ልማፀነው)? ብሎ ሲጠይቃቸው እንዲህ በል አሉት፦ “አላህ ሆይ! ማረኝ፣ እዘንልኝ፣ ጤነኛ አድርገኝ፣ ሲሳይን ለግሰኝ”!! ▲ ይህ የዱንያና የአኺራ ጉዳዮችን ላንተ ጠቅልሎ ይዞልሃል። #ሙስሊም_ዘግበውታል ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ እናም ተማሪዎች አርአያችን የአላህን መልዕክተኛ (ሶለላሁ አለይሂ ወሰልም) ናቸውና እኛም ሁሌም ይህንን ዱዓ እናድርግ። ጌታችንን ተናንሰን እንማፀነው‼️ ልብ ልንል የሚገባን ነገር ቢኖር:- እኛ ጥረት እያደረግንም ሆነ ጥረት ካደረግን በኋላ መመካት ያለብን በጥረታችን ((በልፋታችን)) ሳይሆን በአላህ ነው። በአላህ በመመካት እሱ (አላህ) እንዲያሳካልን ሁሌም ልንለምነው ይገባል። «በአላህ ፍቃድ ይሳካልኛል፣ ጥሩ ውጤት አመጣለሁ» በማለት ንባባችንን አጠናክረን መቀጠል አለብን‼️ ⭕️ አደራችሁን መልዕክቱን ለሁሉም ተማሪዎች አድርሱልኝ። ✍️ በናተው ወንድም ረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል

"ሰላት ተራዊሕ ወይም ተሀጁድ ላይ ለወላጆችህ ዱዓ ማድረግህ ፤ አሥር ግመሎችን አርደህ ሰደቃ ከማውጣት ይበልጣል።" #ሸይኽ_ኡሰይሚን
"ሰላት ተራዊሕ ወይም ተሀጁድ ላይ ለወላጆችህ ዱዓ ማድረግህ ፤ አሥር ግመሎችን አርደህ ሰደቃ ከማውጣት ይበልጣል።" #ሸይኽ_ኡሰይሚን

report አደራረጉ በግልፅ የሚያሳይ በቪዲዮ ስክሪን ሪከርድ አድርጎ አንድ ሰው @Murad_Tadesse ላይ ይላክልኝ። ቪድዮው ከዚህ የተሻለ ይሁን። በያንዳንዱ ስቴፕ የሚነካውን አማራጭ በግልፅ ጸዳ ባለ መልኩ በምልክት የሚያሳይ ይሁን። እስከዛው ስቴፑ የገባችሁ ደጋግማችሁ ሪፖርት አድርጉ። https://t.me/MuradTadesse/40353?single ልብ በሉ! ሪፖርት ለማድረግ follow ማድረግ አይጠበቅባችሁም። ፎሎወሩ እየጨመረ ያለው፤ ሊያዘጉበት ነው ብለው ተጠራርተው ኮፒ ሊንክ እያስባሉ ስለሆነ ነው። ሳንቀደም እንቅደም። እነርሱም በጎድን ኮፒ ሊንክ በማድረግ ስለወጠሩ እናንተም በሪፖርት ወጥሩ! ልብ በሉ! ሪፖርት ለማድረግ የግድ የቲክቶክ አካውንት ሊኖራችሁ አይገባም።

ከአንድ በላይ ደጋግሞ ሪፖርት ማድረግ ስለሚቻል ወጥሩ። ውጤት የሚያመጣው ደጋግሞ ሲደረግና ብዛት ሲኖረው ነው። ጎን ለጎን ዚክርና ዱዓችሁን እያደረጋችሁ በእጃችሁ ሥራችሁን ሥሩ። ኒያችንን ካሳመርን ይ
ከአንድ በላይ ደጋግሞ ሪፖርት ማድረግ ስለሚቻል ወጥሩ። ውጤት የሚያመጣው ደጋግሞ ሲደረግና ብዛት ሲኖረው ነው። ጎን ለጎን ዚክርና ዱዓችሁን እያደረጋችሁ በእጃችሁ ሥራችሁን ሥሩ። ኒያችንን ካሳመርን ይህም አንድ ኸይር ሥራ ነው። በርቱ! (ማነህ ግራፊክ የምትችል፣ ከላይ ባሉት ፎቶዎች ያስቀመጥኳቸውን ስቴፖች፤ ቁጥር አጻጻፉንና በመክበብ ማሳያውን ጽድት አድርገህ ላክልኝ።)

ልብ በሉ! ተራ ቁጥር 3 ላይ እንዳከበብኩት፤ Report ማድረግ ያለባችሁ አካውንቱን እንጁ ኮንተንት አይደለም። ሲቀጥል ተሳስታችሁም ቢሆን follow እንዳታደርጉ። በዚህ ሊንክ እንደት ሪፖርት እንደ
ልብ በሉ! ተራ ቁጥር 3 ላይ እንዳከበብኩት፤ Report ማድረግ ያለባችሁ አካውንቱን እንጁ ኮንተንት አይደለም። ሲቀጥል ተሳስታችሁም ቢሆን follow እንዳታደርጉ። በዚህ ሊንክ እንደት ሪፖርት እንደሚደረግ ዝርዝሩን ታገኛላችሁ። https://t.me/MuradTadesse/40353?single ሳትሰለቹ ደጋግማችሁ ሪፖርት አድርጉ። መጨረሻ ላይ ስትደርሱ ያለውን ስክሪን ሹት አድርጉትና ኮመንት ላይ ላኩት። ወጥሩ! በዙሪያችሁ ያሉ ሰዎችንም አካውንት እየተጠቀማችሁ ደጋግማችሁ ሪፖርት አድርጉ። ሳናዘጋ ዘመቻው እንዳይቆም። አንድ እርምጃ ከዚህ እንጀምር። ልብ በሉ! ሪፖርት የሚደረገው አካውንት ከላይ ባለው ፖስት ያስቀመጥኩት የቲክቶክ ሊንክ ነው። ቲክቶክ ላይ ሰርጭ ብታደርጉ ብዙ ተመሳስሎ የተከፈተ አካውንት ስለሚመጣ፤ ከላይ ሊንኩ ላይ ያለውን ሪፖርት አድርጉ።

ረመዿን 10 🌙 تدبر القرآن 🌙 ቁርዓንን ማስተንተን ረመዿን ቢናገር ኑሮ ሰዎች የሐዲስ፣ የፊቅህ እንዲሁም የተውሂድን ኪታቦችን ትተው ቁርዓንን በማንበብ ሲጠመዱ አይቻለሁ ይል ነበር ታዲያ እኔ እና አንተን ምንድነው ከቁርዓን ያዘናጋን? ረመዿን ቢናገር ኑሮ እንዲህ ይል ነበር ፦ وَقَالَ الرَّسُولُ يَا رَبِّ إِنَّ قَوْمِي اتَّخَذُوا هَٰذَا الْقُرْآنَ مَهْجُورًا መልክተኛውም «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ ይህንን ቁርኣን የተተወ ነገር አድርገው ያዙት» አለ፡፡ ውድ ወንድሜ ፣ውድ እህቴ ከዚህ ቀደም በ ረጀብ ወይም ደግሞ በሸዕባን ቁርዓንን  ማንበብ የተው/ሽ ከነበር/ሽ አስተወይ ይህን شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ (እንድትጾሙ የተጻፈባችሁ) ያ በርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድና (እውነትን ከውሸት) ከሚለዩም ገላጮች (አንቀጾች) ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዿን ወር ነው፡፡ ታዲያ ቅኑን መንገድ መርቶሃልን? የእወነቱን መንገድን አመላክቶሃልን? ከወንጀል ወደ አላህ መሃርታን ከማግኘት የተቀየርክ ሰው አድርጎሃልን? الشيخ : عبدالمحسن الأحمد -حفظه الله-

فوالله كاد قلبي يطير!!!! ኢስላምን እንደሚገባው የበላይነት ለማድረግ መልፋት ሲገባን ስጋዊ ስሜታችንን ለማሟላት ስንሯሯጥ የበታችነታችን ተረጋግጧል! በይፋም መሞታችንም ተበስሯል....

" ከነፍሳችን በላይ አብልጠን በምንወዳቸው ውዱ ነብያችን ክብር የማንደራደር መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል።" የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት ሀላፊ ኡስታዝ አቡበከር
" ከነፍሳችን በላይ አብልጠን በምንወዳቸው ውዱ ነብያችን ክብር የማንደራደር መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል።" የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት ሀላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ከሰሞኑ በውዱ ነብያችን ላይ በተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች ድምበር የሚያልፉ ግለሰቦችን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል። የፉሪ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ከኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የዳዕዋ መድረክ በርካታ ሙስሊሞች በተገኙበት መልዕክት ያስተላለፉት ኡስታዝ አቡበከር አህመድ "ከነፍሳችን በላይ አብልጠን በምንወዳቸው ውዱ ነብያችን ክብር የማንደራደር መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል" ሲሉ ተናግረዋል። "እኛ እምነታችን በምናስተምርበት ወቅት ፈፅሞ የሰዎች እምነት ላይ ድንበር አናልፍም እስልምናም ያንን አያዘንም ያሉ ሲሆን ሌሎች የእምነት ተቋማትም ድንበር የሚያልፍ ግለሰቦችን ተው ሊሉ ይገባል" ብለዋል። "እንደ ተቋም በህግ መሄድ እስለብን ጥግ ድረስ እንሄዳለን ያሉ ሲሆን ሙስሊሙ ማህበረሰብ በተለይ ወጣቱ በሰላማዊ መንገድ እምነቱን ማስከበር አለበት" ሲሉ ገልፀዋል።

ما شاء الله تبارك الله. في لفتة أبوية حانية .. الشيخ عبدالرحمن السديس يستضيف الأبناء الأيتام وأسرهم المحتضنة على مائدة الإفطا
+1
ما شاء الله تبارك الله. في لفتة أبوية حانية .. الشيخ عبدالرحمن السديس يستضيف الأبناء الأيتام وأسرهم المحتضنة على مائدة الإفطار في الحرم المكي الشريف. In a kind fatherly gesture, Sheikh Abdul Rahman Al-Sudais hosts orphans and their foster families at the Iftar table in Masjid Al Haram, Makkah.

አርቲስቱ እያለቀሰ ይናገራል‼ || t.me/MuradTadesse

ፖሊስነት በናንተ በቃ!🫡

🌿🌿🌿🍃ጥቆማ🍃🌿🌿🌿 "የውሻ ጩኸት ደመናን አይጎዳም!" ~ በነብያችን ﷺ ላይ የሚሳለቅ ራሱን እንጂ እሳቸውን ምንም ሊያደርጋቸው አይችልም። የላካቸው አምላክ "መወሳትህን/ዝናህን ከፍ አደረግንልህ" ብሏቸዋል። ይሄው የዝናቸው ከፍ ማለትም ነው ዛሬ በርካታ ውሾችን እያስጮኻቸው ያለው። ትላንትም የዛሬዎቹ ውሾች አያቶች የመልእክተኛውን ክብር ሊያንቋሽሹ ሞክረው ነበር። አላህ ግን ራሱ ለመልእክተኛው ﷺ ተከላካይ ጠበቃ ይሆንና መልእክተኛው ግን ነገሩን ንቀው እንዲተውት እንዲህ ይጠቁማቸዋል፡- (فَٱصۡدَعۡ بِمَا تُؤۡمَرُ وَأَعۡرِضۡ عَنِ ٱلۡمُشۡرِكِینَ ۝  إِنَّا كَفَیۡنَـٰكَ ٱلۡمُسۡتَهۡزِءِینَ ۝  ٱلَّذِینَ یَجۡعَلُونَ مَعَ ٱللَّهِ إِلَـٰهًا ءَاخَرَۚ فَسَوۡفَ یَعۡلَمُونَ ۝  وَلَقَدۡ نَعۡلَمُ أَنَّكَ یَضِیقُ صَدۡرُكَ بِمَا یَقُولُونَ ۝  فَسَبِّحۡ بِحَمۡدِ رَبِّكَ وَكُن مِّنَ ٱلسَّـٰجِدِینَ ۝  وَٱعۡبُدۡ رَبَّكَ حَتَّىٰ یَأۡتِیَكَ ٱلۡیَقِینُ) "የታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለፅ፤ አጋሪዎችንም ተዋቸው። እኛ ተሳላቂዎችን ሁሉ በቅተነሃል። (እነሱም) እነዚያ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደረጉ ናቸው፤ በርግጥም (የስራቸውን ዋጋ) ወደፊት ያውቃሉ። አንተም በሚሉት ነገር ልብህ የሚጠብ መሆኑን በርግጥም እናውቃለን። ጌታህንም ከማመስገን ጋር አጥራው፤ ከሰጋጆቹም ሁን። እውነቱም (ሞት) እስከሚመጣህ ድረስ ጌታህን አምልክ።" [አልሒጅር፡ 94-99] ስለዚህ ተሳላቂዎቹ ውሾች ቢሳለቁም የነብያችን ﷺ ዝና የበለጠ ይገናል። የውሾቹ ስም ይከስማል። ውሻ ደግሞ ምን ታሪክ አለውና?! እስኪ የነብያችንና የትላንት ጠላቶቻቸውን ዝና አወዳድሩ። ሲጀመር መወዳደር ይችላሉ? በጭራሽ! “የሰማይና የመሬት ያክል ነው” ብንል እንኳ በትክክል አይገልፀውም። ግን የነብያችንን ﷺ ክብር ለማጉደፍ ተፍ ተፍ የሚሉ ሰዎች አላማቸው ምን ይሆን? መልሱ ግልፅ ነው። 1.  አንዳንዶቹ በነብዩ ﷺ እውቅና ሂሳብ እውቅና መሸመት የሚፈልጉ ናቸው። “አንዳንዶች ታዋቂዎችን በመተቸት ታዋቂ መሆን ይፈልጋሉ” ሲባል አልሰማችሁም? 2.  ሌሎቹ ደግሞ የኢስላም ውበቱና ሁለንተናዊነቱ የሚያስቀናቸው፤ ከፍተኛ ግስጋሴው የሚያስበረግጋቸው ናቸው። ስለሆነም ሙሐመድን ﷺ ሲያንቋሽሹ የኢስላም ውበቱ የሚደበዝዝ፣ ግስጋሴው የሚገታ ይመስላቸዋል። እውነታው ግን ተቃራኒው ነው። ኢስላም ዛሬ ጠላቶቹን እንቅልፍ በሚነሳ መልኩ በከፍተኛ ፍጥነት እየገሰገሰ ነው። ስለዚህ ውሾቹ አመል ሆኖባቸው ይጮሃሉ እንጂ የኢስላምን ግስጋሴ ሊገቱት አይችሉም! ውሾቹ ይጮሃሉ፣ ዋው! ዋው! እያሉ። ግመሉ ግን ጉዞውን ቀጥሏል። ውሻ ግመልን ማስቆም ከቻለች ትሞክር። ባይሆን ከእኛ አንድ ነገር ይጠበቃል። ከሃዲዎችን የነብያችንን ﷺ ስም ለመዘለፍ ያበቃቸው ለነብዩ አስተምሮ ያላቸው ጥላቻ መሆኑ ይታወቃል። አዎ የነቢዩ ﷺ ሱና እጅጉን ያስቆጫቸዋል! እውነቱ ይህ ከሆነ ከሃዲዎችን የበለጠ ለማስቆጨት የሚጓጓ፤ ለሙሐመድ ﷺ እውነተኛ ወዳጅነቱን ማንፀባረቅ የሚፈልግ፣ ብሎም የአላህን ውዴታ ማትረፍ የሚሻ የበለጠ ወደ መልእክተኛው ሱና ይቅረብ። ትእዛዛቸውንም ይፈፅም። ከከለከሉትም ይራቅ። ይህን የሚያደርግ ጠላቱን የበለጠ ያስቆጫል። የአላህንና የመልክተኛውንም ﷺ ውዴታ ያፍሳል። ያ ሱብሓላህ! የአላህና የመልክተኛውን ውዴታ ያገኘ ምን የቀረበት ነገር አለ?! ያ ወሃ፞ቡ አንተ ወፍቀን! ኣሚን ✍IbnuMunewor https://t.me/ibnukedir