cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

አዳኙ የየትምህርት እና የመረጃ ሚዲያ

መረጃ በፍጹም አይናቅም አይደንቅም

Більше
Рекламні дописи
800
Підписники
+824 години
+1327 днів
+12530 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

በአፍጋኒስታን በድጋሚ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የ68 ሰዎች ህይወት ማለፉን የታሊባን ባለስልጣናት አስታወቁ፡፡ በአፍጋኒስታን ከወትሮው የተለየ ከባድ ዝናብ እየጣለ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን፤ በዝናቡ ሳቢያ በሰሜናዊ እና ምዕራባዊ አፍጋኒስታን የጎርፍ አደጋ መከሰቱ ተሰምቷል፡፡ በአደጋው በምዕራብ አፍጋኒስታን በሚገኘው የጎሆር ግዛት 50 ሰዎች ሲሞቱ በሰሜናዊ አፍጋኒስታን ደግሞ 18 ሰዎች መሞታቸው ነው የተገለጸው፡፡ ከሰው ህይወት ማለፍ በተጨማሪ በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን፤ በአደጋው በሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች፣ ከ100 ሄክታር በላይ የእርሻ ማሳ እና 300 የቤት እንስሳት በጎርፍ መወሰዳቸው ተነግሯል፡፡ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ
Показати все...
እባካችሁ ፈጣሪን አትፈታተኑ ሰውንም ጨካኝ አታርጉት የአዲስ አበባ ፖሊስ እንዳስታወቀው እነዚህ በምስሉ ላይ የሚታዩት ግለሰቦች ጤናማና ያልታመመ ህፃን ልጅን ካንስር ይዞታል፣  የካንስር በሽተኛ ነው ፣ ሊሞትብን ነው ብለው ሲለምኑበት በቁጥጥር ስር ውለዋል።የድርጊቱ ፈፃሚዎች የህፃኑ አባትና አንድ ሌላ ግብረ አበሩ መሆኑንም ፖሊስ አስታውቋል። አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ ለሌሎች ሸር እናድርግ!! 👇👇👇👇👇👇👇👇 መረጃ በፍጥነት ለማግኘት በቴሌግራም 👇👇 https://t.me/AdanguMidia
Показати все...
👍 2
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ይፋ ሆኗል‼ የ2016 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) የበይነ መረብ (Online) ተፈታኞች መፈተኛ ይፋ ሆነ፡፡ ✔ ከዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በአድራሻው ተፈታኞች በሚገኙበት ክልል የተደለደሉ ስለሆነ ልምምድ ማድረግ ይችላሉ ተብሏል። ✔ተፈታኞች ልምምድ ለማድረግ ከዚህ በፊት ለክልል / ከተማ አስተዳደር ቀድሞ የተላከውን  የይለፍ ቃልና ስም (User Name and Password) ከየትምህርት ቤቶቻቸው ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል። ✔መጀመሪያ ወደ መፈተኛ ሲሰተሙ እንደገቡ የማይረሱትን የግላቸውን የይለፍ ቃል የሚቀይሩ ይሆናል፡፡ ✔ተፈታኞች ከተደለደሉበት ክለስተር ዉጪ ሲሰትሙን መጠቀም የማይችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። ✔የ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በወረቀትና በበይነ መረብ ይሰጣል። አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ
Показати все...
የሥልጠና ጥሪ
የህፃናት ማቆያ (ዴኬር)ለከፈቱ የመንግስት የመንግስት ትምህርት ቤቶች በሙሉ #የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት ከክፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት ጋር በመተባበር የህፃናት ማቆያ (ዴኬር)ለከፈቱ የመንግስት የመንግስት ትምህርት ቤቶች በህፃናት አያያዝና ማቆያ(ዴኬር) ስታንዳርድ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ስለሚሰጥ ሰኞ በቀን 12/09/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30(ሰዓት) የስልጠና ቦታ ቤተል በሚገኜው የክፍለ ከተማው ህንፃ 11ኛ ፎቅ ሁለገብ አዳራሽ በዚሁ መሰረት 1.የሰው ኃይል ቡድን መሪ ብዛት👉🏿 1 2.የዴኬር መግዚት ብዛት 👉🏿 1 #በአጠቃላይ እያንዳንዱ ትምህርት ቤት ሁለት(2)ተሳታፊዎች እንድገኙ ጥሪ ይተላለፍላቸው ተብሏል። አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ ለሌሎች ሸር እናድርግ!! 👇👇👇👇👇👇👇👇 መረጃ በፍጥነት ለማግኘት በቴሌግራም 👇👇 https://t.me/AdanguMidia
Показати все...
አዳኙ የየትምህርት እና የመረጃ ሚዲያ

መረጃ በፍጹም አይናቅም አይደንቅም

👍 3
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በታይላንድ ቅጥ ባጣ ዉፍረት ሲሰቃይ የነበረዉ ጎሬላ በስኳር በሽታ ህይወቱ ማለፉ ተነገረ በታይላንድ ባንኮክ ውስጥ ከአላፊ አግዳሚ በሚያቀርብለት ምግብ ሲኖር የነበረዉና በቅጥ ባጣ ዉፍረት የተሰቃየዉ ጎሬላ በስድስት አመቱ ከክብደት ጋር በተያያዙ በርካታ በሽታዎች ህይወቱ አልፏል፡፡ጎሬላዉ በባንኮክ በሚገኘው ክሪስታል ፔት ሆስፒታል የመጨረሻ እስትንፋሱ በህክምና ላይ እያለ አብቅቷል፡፡ ለጎሬላዉ ህልፈት ጣፋጭ የማብዛት ሱስ እና ሌሎች ክብደቱን የሚያደልቡ ምግብ መሰጠቱ ምክንያት ሆኗል፡፡ቱሪስቶች በርካታ ጣፋጭ ምግቦች ይሰጡት የነበረ ሲሆን በአማካይ ሊኖረዉ ከሚገባዉ ክብደት ከ19 ኪሎ ግራም በላይ እንዲደርስ አድርገዉታል መባሉን ዳጉ ጆርናል ከዘገባው ተመልክቷል። ጎሬላዎች በአማካይ እስከ 37 ዓመታት ሊኖሩ ቢችሉም ይህ ጉሬላ ግን በ 6 ዓመቱ ለሞት የተዳረገዉ በስኳር፣ በታይሮይድእና ኩሽንግ ሲንድሮም ተሠቃይቶ ነዉ፡፡ ጣፋጭ ምግቦች እና ስኳር የበዛበት መጠጦች በብዛት ይወስድ የነበረ ሲሆን ሰዎች ሲበላ ለእርሱም አብዝተዉ ይሰጡት ነበር ነገር ግን የሰዎች ደግነት ያለ እድሜዉ ገደሉት ሲሉ የእንስሳት ሀኪም ባለሙያዎች ተናግረዋል፡፡ ሁላችን በነገሮች ሁሉ አስተዋይ እንሁን አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ ለሌሎች ሸር እናድርግ!! 👇👇👇👇👇👇👇👇 መረጃ በፍጥነት ለማግኘት በቴሌግራም 👇👇 https://t.me/AdanguMidia
Показати все...
👍 2
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ከጠፋ ከ30 ዓመታት በኋላ በጎረቤቱ ቤት ታግቶ የተገኘው ግለሰብ ኦማር ቢን ዑምራን ከዘጠኝ ጓደኞቹ መካከል ተለይቶ ከ27 ዓመታት በፊት በአልጄሪያ በጄልፋ ከተማ ወደ ትምህርት ቤት ሲሄድ በድንገት መጥፋቱ ተሰማ። ፍለጋው ወዲያውኑ ነበር የተጀመረው። ይሁን እንጅ የውሃ ሽታ ሆነ። በ1990ዎቹ መጨረሻ እና በ2000ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ ለ10 ዓመታት በቆየው የሰሜን አፍሪካ ሀገራት መንግስታት እና በእስላማዊ አማፂ ቡድኖች መካከል በነበረው የእርስ በእርስ ጦርነት ምክንያት ኦማር ቢን ዑምራን ተገድሎ ሊሆን እንደሚችል ቤተሰቦቹ ገምተው ነበር። ግን ከመፈለግ ወደ ኋላ አላሉም። በዚህ መካከል የዑመር እናት ልጃቸውን እንደፈለጉ፣ በልጃቸው ላይ የደረሰውንም እውነት ሳይሰሙ ሁልጊዜ እንደናፈቁት ሕይወታቸው አልፏል። ይህንን መሪር ሀዘን ግን ዑመር አጠገቧ በሚገኝ አንድ የሰቆቃ ቦታ ሆኖ ሰምቶ እንደነበር ከተገኘ በኋላ ተናግሯል። በእግር በፈረስ ፈልገው አስፈልገው ያጡት ወላጆቹ በጦርነት ተገድሎ ሊሆን እንደሚችል ቢጠረጥሩም እውነቱ ግን ከዚያ የራቀ እና እዛው ቤታቸው አጠገብ እየተፈጠረ ያለ ነበር። የጠፋው ልጅ ከገዛ ቤተሰቦቹ ቤት 200 ሜትር ርቆ በሚገኝ ጎረቤቱ ቤት ውስጥ ታግቶ ሶስት አስርት ዓመታትን አስቆጥሯል።
Показати все...
                አስቸኳይ ማስታወቂያ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በመንግስት ት/ቤቶች በሞግዚትነት እያገለገላችሁ በአሠላ ፣ በኮተቤ እና በደ/ብርሃን ት/ኮሌጅ በKG መምህርነት በ2016ዓ.ም ተመርቃችሁ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ  ቅዳሜ በ10/9/16ዓ.ም ጠዋት 2:30 ላይ በሚኒሊክ አጠ/2ኛ ደ/ት/ቤት በመምህርነት ለመመደብ የመለያ ፈተና ስለሚሠጥ በሰዓቱ ተገኝታችሁ ፈተናውን እንድትወስዱ እያሳሰብን። 07/09/2016 አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ ለሌሎች ሸር እናድርግ!! 👇👇👇👇👇👇👇👇 መረጃ በፍጥነት ለማግኘት በቴሌግራም 👇👇 https://t.me/AdanguMidia
Показати все...
አዳኙ የየትምህርት እና የመረጃ ሚዲያ

መረጃ በፍጹም አይናቅም አይደንቅም

2
የሠራተኞች ደመወዝ… 👉 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ  የፌደራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1064/2010ን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ መክሯል። 👉የመንግስት ሰራተኞች የሰው ሀይል ምልመላና መረጣ ግልጽነት ባለው ውድድርና ብቃት ላይ የተመሰረተ ሆኖ ሁሉንም ባካተተና ብዝሀነትን በጠበቀ መልኩ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ስርአት መዘርጋት በማስፈለጉ ረቂቅ አዋጁ መዘጋጀቱ ተነግሯል። በረቂቅ አዋጁ ማሻሻያ ከተደረገባቸው ጉዳዮች ውስጥ ፦ ✔የደሞዝ ጭማሪ ✔የደሞዝ እርከን ✔ክፍያና ጥቅማጥቅሞች ማትጊያና ማበረታቻ ስርአት ✔ የሰራተኞች ብቃት  ምዘናና ማረጋገጫ ስልጠና አሰጣጥ ስራ ስምሪት እና ነጻ ገለልተኛ ስርአት መገንባት፣ ✔ የመንግስት ሰራተኛነት ውል ማቋረጥና ማራዘም የሚሉና ሌሎች እንደሚገኙበት ገልጸዋል፡፡ ✔ረቂቅ አዋጁ አዋጅ ቁጥር 13/2016 ሆኖ በሙሉ ደምጽ ለሰው ሀብት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርቷል፡፡ ስለዚህም የደመወዝ ስኬል ማስተካከያ በየአራት ዓመቱ እየተጠና፣ ይወሰናል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የፌደራል መንግስት ሰራተኞች ረቂቅ አዋጅ ከሚያስተዋውቃቸው ለውጦች ውስጥ አንዱ የደመወዝ ስኬል ማስተካከያ በምን ያህል ጊዜ እንደሚደረግ ማስቀመጡ ነው። በስራ ላይ ያለው አዋጅ የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ስኬል “የመንግስትን የፋይናንስ አቅም፣ የህዝቡን አጠቃላይ የኑሮ ሁኔታ፣ የዋጋ ደረጃዎች እና አግባብነት ያላቸውን ሌሎች ሁኔታዎች ባገናዘበ መንገድ” እየተጠና እንደሚወሰን ይደነግጋል። ይሁንና አዋጁ “በየጊዜው እየተጠና የሚወሰን ይሆናል” እንዲሁም “አስፈላጊ ሆኖ” ሲገኝ የደመወዝ ስኬል ተጠንቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ ከመደንገግ ውጪ ይህ ጥናት በምን ያህል ጊዜ እንደሚደረግ አያስቀምጥም። አዲሱ ረቂቅ አዋጅ በአንጻሩ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን “የሥራ ደረጃ መነሻ ዝቅተኛ ደመወዝ እና ከፍተኛ ደመወዝ ጣሪያ በየአራት አመቱ አጥንቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ” እንደሚያስወስን እንዲሁም አፈጻጸሙን እንደሚቆጣጠር ያስቀምጣል። ኮሚሽኑ የሚያደርገው የአበል ማስተካከያም በተመሳሳይ የጊዜ ገደብ ተቀምጦለታል። በረቂቅ አዋጁ፤ “የመንግስት ሠራተኛ ወጪን መሸፈን የሚያስችል ልዩ ልዩ የአበል አይነቶች እና የቀን ውሎ አበል ማስተካከያ በየሁለት አመት ኮሚሽኑ ይወስናል” ሲል በየስንት ጊዜው ማስተካከያ እንደሚደረግ ይወስናል። የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የደመወዝ ስኬልን ለማስተካከል በየአራት ዓመቱ የሚያደርገውን ጥናት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ከማቅረቡ አስቀድሞ ግን ማረጋገጫ የመስጠት ኃላፊነት ያለው አዲስ ቦርድ በረቂቅ አዋጁ ተዋውቋል። አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ ለሌሎች ሸር እናድርግ!! 👇👇👇👇👇👇👇👇 መረጃ በፍጥነት ለማግኘት በቴሌግራም 👇👇 https://t.me/AdanguMidia
Показати все...
አዳኙ የየትምህርት እና የመረጃ ሚዲያ

መረጃ በፍጹም አይናቅም አይደንቅም

👍 2 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
                አስቸኳይ ማስታወቂያ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽፈት ቤት ስር በመንግስት ት/ቤቶች በሞግዚትነት እያገለገላችሁ በአሠላ እና በደ/ብርሃን ት/ኮሌጅ በKG መምህርነት በ2016ዓ.ም ተመርቃችሁ፣ በወቅቱ ክ/ከተማ መጥታችሁ ያመለከታችሁ 27 ሞግዚቶች በሙሉ፦ ቅዳሜ በ10/9/16ዓ.ም ጠዋት 2:30 ላይ በሚኒሊክ አጠ/2ኛ ደ/ት/ቤት የመለያ ፈተና ስለሚሠጥ በሰዓቱ ተገኝታችሁ እንድትወስዱ እያሳሰብን፤ ስም ዝርዝራችሁን ከታች ባለው መሠረት አያይዘንላችኋል፡፡ 07/09/2016 አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ ለሌሎች ሸር እናድርግ!! 👇👇👇👇👇👇👇👇 መረጃ በፍጥነት ለማግኘት በቴሌግራም 👇👇 https://t.me/AdanguMidia
Показати все...
2👍 1👎 1
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣንና የአዲስ አበባ ከተማ  ት/ቢሮ በጋራ በመተባበር በሁሉም ደረጃ ለሚገኙ የግል ት/ቤቶች እና የመንግስት ቅድመ 1ኛ ፣እና 1ኛ እና መካከለኛ  ት/ቤቶች የትምህርት ስራ ቁጥጥር/Inspection/ ይካሄዳል። ስለዚህም ለሁሉም የመንግስትና የግል ት/ቤቶች በሙሉ ከ07/09/2016 ዓ.ም እስከ 08/09/2016 ዓ.ም ድረስ ከከተማ የተመደቡ ሱፐርቫይዘሮች በየተቋማችሁ ለክትትልና ድጋፍ ስለሚመጡ በአግባቡ እንድታስተናግዷቸው በአክብሮት እናሳውቃለን። አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ ለሌሎች ሸር እናድርግ!! 👇👇👇👇👇👇👇👇 መረጃ በፍጥነት ለማግኘት በቴሌግራም 👇👇 https://t.me/AdanguMidia
Показати все...
አዳኙ የየትምህርት እና የመረጃ ሚዲያ

መረጃ በፍጹም አይናቅም አይደንቅም

👍 2