cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Mulugeta Anberber

ፈጣን መረጃ እንዲሁም ለዕለታዊ ክንውኖች ወዳጅ ይሁኑ❗️ ዜናው ጥሩም ይሁን፤ መጥፎ እነግራችኋለሁ፡፡ መረጃ ለመላክ @Mulugetaanberberrrr

Більше
Рекламні дописи
9 485
Підписники
-624 години
-177 днів
+1330 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Показати все...
የአማራ ፋኖ፤ የአጭርና የረዥም ጊዜ ዓላማዎች እንዴት ይተግበሩ…? | 251 Agenda | 251 Zare | Ethio 251 Media

👍 18
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የወልቂጤ ሞባይል ቤት ባለቤት የሆኑትን አቶ ስንታየሁ በማንነት አማራ ስለሆነ ብቻ በግል ችግር ያለባቸው ሁለት የቀቢናና ማረቆ ተወላጅ ፀረ አማራ ግለሰቦች ይህ ግለሰብ የጉራጌን ዘርማና ፋኖን ለማጠናከር ለመሳርያ መግዣ ብር ያሰባስባል በማለት ያልሆነ ታፔላ በመስጠት ልጁን አሳስረውታል !! ደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ የአማራንና ጉራጌን ተወላጆች ማሳደድ በቃ የተለመደ ነገር ሁኗል እናም ድምፅ ሁኑን:: ግፉዓን ወገኖቻችሁ ከደቡብ ኢትዮጵያ
Показати все...
👍 51😢 5
02:44
Відео недоступнеДивитись в Telegram
ይሄን ቪዲዮ ብዙ ነገር ይነግረናል‼️ አማራ ስለሆነች ፓስፓርቷን ወረወሩባት ይሄ አዲስ አበባ ላይ የሆነ እና አሁንም የቀጠለ ነወ። በሁሉም የመንግስት መዋቅር ውስጥ አማራ ላይ በስውር ይደረጉ የነበሩ መድሎዎች አሁን አይን አውጥተው በግልጽ ብሄር እየጠየቁ መሳደብ እና መሰል ነገር በcustomer sevice በሚሰጡ አካላት ጭምር እየተደረገ ነው። ለዚህም ነው ከአብይ አህመድ ጋር ድርድር ዘላቂ ፍትህ አያመጣም የምንለው! https://t.me/MulugetaAnberberEthio251
Показати все...
👍 93💔 16🔥 4😱 3😈 2👏 1
Показати все...
በአዲስ አበባ ሕጋዊ ትጥቅ የማስፈታት የአገዛዙ ድብቅ ኦፕሬሽን | 251 Zare | 251 Agenda | Ethio 251 Media

👍 23
ጋዜጠኛ ሳሙኤል አሰፋ ከአገር መሰደዱን ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገለጸ። ጋዜጠኛ ሳሙኤል በአዲስ አበባ ዙሪያ ሸገር ከተማ "ሕገ ወጥ ግንባታ" ናቸው ተብለው በፈረሱ ወደ 100 ሺህ የሚቆጠሩ ቤቶችና በተፈናቀሉ ወደ ግማሽ ሚሊየን የሚጠጉ ዜጎችን ጉዳይ ለኢትዮጵያ ሚዲያ ሰርቪስ EMS ለመዘገብ ጣፎ በተገኘበት ወቅት በፖሊስ ተይዞ ድብደባ ፣ እስርና ማዋከብ ደርሶበት ነበረ። በዋስ ከእስር ቤት ወጥቶ እንዲከራከር በፍርድ ቤት ተወስኖለት ቢወጣም ዛቻና ማስፈራሪ በየጊዜው ይደርስበት እንደነበረ ለኢትዮ 251 ገልጿል። በቅርቡም ለዋዜማ ሬድዮ እና ኢንተር ኒውስ ዘገባ ለመስራት ወደ አማራ ክልል ደሴና ሐይቅ ከተሞች በተጓዘ ወቅት በክልሉ ኮማንድ ፖስት ታስሮ እንደነበረ ይናገራል። አስቀድሞ በታሰረበት ጉዳይ ለዋስትና የተያዘውን ገንዘብ ለማስለቀቅ ሸገር ከተማ በተገኘ ወቅት ፖሊስ ይዞት እንደነበረ እና በተጨማሪም ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ከአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ VOA ጋር በነበረው ቃለ ምልልስ ጉዳይ ፌደራል ፖሊስ ለጥያቄ ትፈጋለህ ብለው አስገድደው ወስደውት እንደነበረ የገለጸው ጋዜጠኛው። በደረሰበት ተደጋጋሚ ጫና ምክኒያት አገር ለቆ መውጣቱን አስታውቋል። ሳሙኤል በበርካታ የመገናኛ ብዙሃን የሰራ የረጅም አመት ልምድ ያለው ጋዜጠኛ ሲሆን የሰራባቸው ሚዲያዎች ዋዜማ ሬድዮ ፣ ንስር ኢንተርናሽናል ብሮድካስት እና የኢትዮጵያ ሚዲያ ሰርቪስ ይገኙበታል። https://t.me/ethio251media
Показати все...
👍 64 7😢 3
Показати все...
በአማራ ላይ የትህነግና የአገዛዙ ጥምር ሴራ | 251 zare | 251 Agenda | Ethio 251 Media

👍 47🔥 3 2
ክብሩን የናቀ ማን ያከብረዋል...⁉️ ጥቃት አካላዊም፣ ስነልቦናዊም፣ ሞራላዊም ነው። በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማሕበራዊ እና ባህላዊ መስኮች ሁሉ የሚፈጠር ጥቃት፤ ክብር (Dignity) ላይ የሚመጣ ጥቃት ነው። ክብርን ማጣት ከሰውነት መውረድ ነው!! ክብር የሌለው ሰው ወይ ማሕበረሰብ በባርነት ውርስ ያለ ነው ወይም ባርነትን ለመቀበል የወሰነ ነው። ጥቃትን የሚለማመድ ማሕበረሰብ ክብር-ማጣትን የሚለማመድ ማህበረሰብ ነው። ተጠቂነት የሚወሰደው በግለሰብ ደረጃ አንተ ላይ፣ ቤትህና ቤተሰብህ ላይ ብቻ ጥቃት ሲፈፀም አይደለም። ጥቃት ከሌሎች ጋር በምትጋራው የትኛውም እሴት እና ማንነት ላይ የሚፈፀም ጥቃትም ነው!! ጥቃት ክብሩን አውርዶ ሕልውናውን ሲያንቀው የተኛ ማሕበረሰብ ውርደትን ብቻ ሳይሆን መጥፋትን ምርጫው ያደረገ ነው። ድል ለአማራ !! #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide https://t.me/MulugetaAnberberEthio251
Показати все...
👍 59👏 4 2
Repost from Ethio 251 Media
አርበኛ ተፈሪ መኮነን! ከ2008 ዓ/ም በፊት የአሚኮ ፕሮሞሽን ሀላፊ፣ የህዝባዊ ግንባሩ መስራች፣ የንስር ሚዲያም መስራች ፣በባህርዳር ከተማ ወጣቱን ማንቃት ጉልህ ሚና የተጫወተ ድንቅ አርበኛ ነበረ። ይህ አርበኛ በኮሎኔል ፈንታው ሙሀቤ የሚመራው የወሎ ዕዝ እና በዋርካው ምሬ ወዳጆ የሚመራው የምስራቅ አማራ ፋኖ ወደ አንድ እንዲመጣ የተቋቋመውን ኮሚቴ በመምራትና ሂደቱ እንዲፋጠን ወሳኝ ሚና የተጫወተ ነው። በተመሳሳይ ሻለቃ መከታው ማሞ የሚመራውን የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛትን እና በአርበኛ አሰግድ የሚመራውን የአማራ ፋኖ በሸዋ ወደ አንድ እንዲመጡ ለማድረግ እየሰራ ካለው ኮሚቴ አባል በመሆን ስራዎችን እየሰራ ይገኝ ነበር። አገዛዙ ከወራቶች በፊት በደብረ ኤልያስ ገዳም የሰነዘረውን ጥቃት ለመመከት ከጓዶቹ ጋር ተሰልፎ በርካታ ገድሎችን ፈፅሟል። አርበኛ ተፈሪ አገዛዙ በጥላቻ ተነሳስቶ በአማራነታቸው ብቻ ገሚሶችን በማሰር፡ መያዝ ያልቻላቸውን ደግሞ በሌሉበት በሽብር ወንጀል ከከሰሳቸው ውስጥ አንዱ ናቸው። ይህ ኩሩ ጀግና በአማራ ትግል ሂደት ውስጥ የሚስተዋሉ ውስብስብ ችግሮችንና እንቅፋኖችን በመበጣጠስ በጎጃም፣ በሸዋ፣ በወሎና በጎንደር ያሉ ፋኖዎች ወደ አንድ መጥተው የአማራ ፋኖ እንዲቋቋም ትልቅ ጥረት እያደረገ ባለበት ሰሞኑን በሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ ልዩ ስሙ ሸዋት በተባለ አከባቢ ላይ አገዛዙ በፈፀመው የድሮን ጥቃት በክብር ተሰውቷል። https://t.me/ethio251media
Показати все...
😢 58👍 13🔥 2 1
Repost from Ethio 251 Media
ከኢትዮ 251 ሚዲያ የቀረበ ጥሪ! ኢትዮ 251 ሚዲያ ላለፉት አራት ዓመታት የዐቢይ አህመድ አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ የሚያደርሰውን መጠነ ሰፊ ጭፍጨፋና ግፍ እየተከታተለ በመዘገብ የህዝብ ልሳን ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ሚዲያው በሚያቀርባቸው መረጃዎች አገዛዙን በማጋለጡ፤ አገዛዙ ሚዲያውን በመዝረፍ፣ ጋዜጠኞችን በማሳደድ እንዲሁም በተደጋጋሚ እና በተደራጀ መልኩ ቻናሎቹን እያዘጋበት ይገኛል፡፡ በዚህ የተነሳም የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን የዘር ማጥፋት ጦርነት ሰሚ እንዳያገኝ የአገዛዙ ፍላጎትና እቅድ ቢሆንም፤ ኢትዮ 251 ሚዲያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም ለህዝብ ድምጽ በመሆን የአገዛዙን ገመና ያለማቋረጥ እያጋለጠ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የአማራ ህዝብ የተጋረጠበትን ጦርነት ለመመከትና ህልውናውን ለማስጠበቅ የሚዲያው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ኢትዮ 251 ሚዲያም ይህንን ኃላፊነቱን በመረዳት ባለሙያዎች በመጠናከርና በሁሉም ቀጠናዎች ዘጋቢዎችን በመመደብ እየሠራ ይገኛል፡፡ ይህ ጥረቱም የአገዛዙን ገመና ከማጋለጥም በተጨማሪ፤ የፋኖን እያንዳንዱን የትግል ውሎና ጀብዱ በመዘገብና ሰንዶ በመያዝ ላይ ነው፡፡ ይህን ጥረቱን በተጠናከረ መልኩ እንዲያከናውን የፋይናንስ ድጋፍ አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል፡፡ ስለሆነም ኢትዮ 251 ሚዲያን በዚህ የጎፈንድሚ አካውንት በመደገፍ የአማራን ህዝብ ትግል ይደግፉ ስንል በአክብሮት ጥሪ እናቀርብለዎታለን፡፡ ኢትዮ 251 ሚዲያ!! https://gofund.me/a2d99937
Показати все...
ኢትዮ 251 ሚዲያን እንደግፍ! Support Exiled Ethio251 Media, organized by Ethio251 Zena-Tequam

ከኢትዮ 251 ሚዲያ የቀረበ ጥሪን እንደግፍ! ኢትዮ 251 ሚዲያ ላለፉት አራት ዓመታት የዐቢ… Ethio251 Zena-Tequam needs your support for ኢትዮ 251 ሚዲያን እንደግፍ! Support Exiled Ethio251 Media

👍 28🔥 1
09:23
Відео недоступнеДивитись в Telegram
አርበኛ ፋኖ ተፈሪ መኮንን የአብን ቅድመ መስራች እና በአማራ ሕልውና ተጋድሎ ዱር ቤቴ በማለት በተለያዩ አውደ ግንባሮች በመሳተፍ ላይ የነበረው በትግል ሜዳ ላይ ተሰውቷል። ዝርዝሩን እነሆ
Показати все...
👍 39 3😢 1