uk
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Відкрити в Telegram
917
Підписники
+124 години
+57 днів
-330 днів
Архів дописів
ሚያዚያ 03/2018 ዓ.ም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የትንሳኤን በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ዋና አስተዳዳሪው በዓሉን ስናከብር የሀገራችን መለያ የሆነውን በመተጋገዝና በመደጋገፍ አብሮ የማሳለፍ ልማድን በማጠናከር አቅም ለሌላቸውና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ወገኖቻችንን በማሰብና ማዕድ በማጋራት ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል። የትንሳኤ በዓል በክርስትና ሀይማኖት ተከታዮች ዘንድ የዐብይ ጾም መጠናቀቅን ተከትሎ በድምቀት ከሚከበሩና ትልቅ ትርጉም ከሚሰጣቸው ዐበይት ክብረ በአላት መካከል ተጠቃሽ ነው። በየእምነቶቻችን አስተምህሮዎችና ድንጋጌዎች መሠረት የምናከናውናቸው ሃይማኖታዊ  ክንዋኔዎች ውስጣዊና ውጫዊ ሠላምን በማጎናፀፍ የእርስበርስ ትስስራችን በፍቅር፣ በመከባበርና በመቻቻል ላይ እንዲመሠረትና እንዲጠናከር ድልድይ ሆነው የሚያገለግሉ ናቸው ሲሉም አቶ ሚፍታ ሁሴን  በመልዕክታቸው ጠቁመዋል። በመጨረሻም ዋና አስተዳዳሪው በዓሉን ስናከብር በፍቅር በመተሳሰብ፣ በመቻቻል  በመደጋገፍና በመረዳዳት ባህላዊ እሴታችንን ባይበልጥ በማጠናከር  ለተቸገሩ ወገኖች ካለን ላይ በማካፈል ሊሆን  ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። በድጋሚ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የትንሳኤ በዓል የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል። መልካም በዓል!!!

ሚያዝያ 03/2018 ዓ ም በባለፉት 5 አመታት በህብረተሰቡ፣ በመንግስትና በባለሀብቶች ተሳትፎ 2 መቶ 45.6 ሚሊየን ብር ሀብት በመሰብሰብ በርካታ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎችን መከናወናቸውን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨፨ በወረዳው ባለፉት አምስት አመታት 271.84 ኪ.ሜ በላይ የጠጠር መንገድ መስራት መቻሉን ጽ/ቤቱ አክሎ ገልጿል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸብር ረጋ በባለፉት 5 አመታት በተቋሙ በመንገድ ልማት የተከናወኑ ተግባራት አስመልክቶ እንደገለጹት መንገድ ለአንድ ሀገርና አካባቢ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ብልጽግና የሚኖረው ፍይዳ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው የመንገድ ተደራሽነት በማሳደግ የምንፈልገውን ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እድገት ለማረጋገጥ የመንግስት፣ የህብረተሠቡና የባለሃብቱ ንቁ ተሳትፎ እንዲሁም የመንግስትና ቅንጅታዊ አሠራር በማጠናከር በርካታ ስራዎች መሰራተቸውን አስታውቀዋል። አቶ አሸብር አክለውም መንግስት ባለፉት 5 አመታት የህብረተሰቡን የመንገድ ተደራሽነት ችግር ለመቅረፍ በረካታ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን ገልፀው ፣ቀበሌን ከቀበሌ፣ ቀበሌን ከወረዳና ከሌሎች አጎራባች አካባቢዎች ጋር በማስተሳሰር ሰፊ ርብርብ መደረጉን የተናገሩት ኃላፊው ባለፉት 5 ዓመታት ብቻ በወረዳው መንግስት፣ ተወላጅ ባለሃብቶችና ህብረተሰቡን በማስተባበር ከ2 መቶ 45.6 ሚሊዮን  ብር በላይ በሆነ ወጪ 271.84 ኪ.ሜ የጠጠር ስራ እና 151.3 ኪ.ሜ የአፈር ስራ  በላይ የገጠር መንገድ ግንባታ፣ የተለያዩ ስትራክቸሮች ስራ፣ የድልድይ ግንባታ እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች በማከናወን አ/አደሩን ማስጠቀም ስለመቻሉ ገልጸዋል። በወረዳው በ2013 ዓ.ም በህብረተሰቡ በመንግስትና በባለሃብቶች ተሳትፎ 15 ሚሊዮን 950,000 ብር ተሰብስቦ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ በአምስት አመቱ ሁለት መቶ 45.6 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ ተችሏል። ይህም በ2013 ዓ/ም ከነበረው 89.1ኪ.ሜ በ2018 ዓ.ም 271.84 ኪ.ሜ የጠጠር መንገድ ማደጉን አመላክተው ከዚህም በተጨማሪ የአፈር ስራ በ2013 ዓ.ም 43 ኪ.ሜ ከነበረበት 151.3 ኪ.ሜ መስራትና መፈፀም የተቻለ ሲሆን የወረዳችን የመንገድ ሽፋን በ2013 ዓ.ም ከነበረበት 28.13% በ2018 ዓ/ም ወደ 75.3% ማደጉን ገልጸዋል። እንዲሁም በርካታ እስትራክቸሮች እና እጅግ ለመገናኘት አታካች የነበሩ ድልድዮች የመገንባት ስራ ተሰርቷል፡፡ በመንገድ ልማት ዘርፍ በህብረተሰብ ተሳትፎ ማደጉን ተከትሎ በተሰሩ ውጤታማ ስራዎች የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ ቀጣይ የመንገዶች ማስተዳደር ስራዎች እንደሚሰራ እንደዚሁም የተሰሩ የመንገድ ልማት ስራዎች የረጅም ጊዜ እንዲያገለግሉ የመጠበቅ የመንከባከብ የመጠገን ስራ በትኩረት ይሰራል ብለዋል ሲል የዘገበው  የወረዳው መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።

መጋቢት 30/2018 ዓ.ም የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባት እንዲሳካ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት እድሜያቸው ከ9-14 ዓመት ለሆኑ ልጃገረዶች የሚሰጠው የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ክትባት አስመልክቶ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና ሰጥቷል። የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አብራር በመድረኩ ተገኝተው እንዳሉት ሴቶችን ከማህጸን በር ጫፍ ካንሰር በሽታ ተጋለጭነት ለመታደግ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን በአግባቡ መወጣት እንዳለባቸው ጠቅሰው ዕድሜያቸው ከ9 እስከ 14 ዓመት ለሆናቸው ሴቶች የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባት በጤና ተቋማት፣በትምህርት ቤት አና በክትባት መስጫ ቦታዎች ለመስጠት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል። የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር በስፋት በወሊድ እድሜ ክልል የሚገኙ ሴቶችን የሚያጠቃና ለሞት የሚዳርግ በሽታ እንደሆነ የገለጹት አቶ ኢብራሂም ክትባቱ ምንም አይነት የጎንዮሽ ጉዳት የሌለው በመሆኑ ሁሉም ልጃገረዶች ያለምንም ፍራቻ በጤና ባለሙያ የሚሰጣቸውን ክትባት መውሰድ እንዳለባቸው ገልጸዋል። በማህጸን በር ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባቶች አጠቃቀም ላይ የግንዛቤ ስልጠና የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የእናቶችና ህጻናት ስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ሚፍታ መቻል ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን የመድረኩ ተሳታፊዎችም ዘመቻውን ስኬታማ ለማድረግ አስፈላጊው ርብርበብ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። በመድረኩም የወረዳው የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አብራር ፣ የጤና ጣብያ ኃላፊዎች፣ የቀበሌ ጤና ኤክስቴንሽን፣ የጽ/ቤቱ ባለሙያዎችና ባለድርሸሰ አካላት  ተገኝተዋል።

መጋቢት 29/2018 ዓ/ም "ሳይንስ ይመራናል ቴክኖሎጂ ያስቀድመናል " በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ለ5ኛ ዙር የሳይንስ ቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች አውደ ራዕይ መካሄድ ጀምሯል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የተማሪዎችና የመምህራን የቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይ እና ኤግዚብሽን ውድድር አየተካሄደ መሆኑን የወረዳው ሳይንስና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት አክሎ አስታውቋል። የፈጠራ ስራ ከሃሳብ በመነሳት በተግባር የሚረጋገጥ ጊዜው የሚፈልገው አስገዳጅ ሁኔታ በመሆኑ ተማሪዎችን በመደገፍ የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች ክህሎታቸውን ማዳበር እንደሚገባ ተመላክቷል። የሳይንስ ቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች አውደ ራዕይ ውድድር በነገው እለትም የሚቀጥል ይሆናል።

መጋቢት 28/2018 ዓ/ም በክልሉ ግብርናን በማዘመንና ማነቆዎችን በመፍታት የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት እያደገ መጥቷል-አቶ ኡስማን ሱሩር ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ በካልም ፒፎር አር ፕሮግራም ድጋፍ በተፈጥሮ ሀብት እና በገጠር መሬት አስተዳደር የሚተገበሩ ሥራዎች አፈፃፀም ዙሪያ የፕሮግራሙ ስትሪንግ ኮሚቴ ወይይት አካሂዷል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በዚሁ ወቅት፣ በክልሉ ግብርናን በማዘመንና ማነቆዎችን በመፍታት የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል። ለዚህም የግብርናው ሴክተር ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶች የላቀ አበርክቶ እንደሚኖራቸውም አመላክተዋል። በክልሉ ባለፉት አመታት በተከናወኑ ተግባራት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውንም ተናግረዋል። የግብርናን ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን ማሳያው የገበያና እሴት ጭመራ መሆኑንም አቶ ኡስማን አመላክተዋል። በግብርናው ሴክተር ያሉ ፕሮጀክቶችና ፕሮግራሞችን ሀብት በተገቢው ለታለመላቸው አላማ እንዲውሉ በማድረግ የሴክተሩን አቅም ለመገንባት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለመማጣት፣ ምርትና ምርታማነትን ለማደግ እንዲሁም የግብርና ምርቱ የተሟላ የእሴት ሰንሰለት ኖሮት እንዲፈፀም በመደረጉ በርካታ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸውንም አቶ ኡስማን አብራርተዋል። በዚህም ባለፉት ሁለት አመታት 8 የወተት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ተከፍተው፣ አርሶ አደሩ የወተት ኢንዱስትሪ ባለቤት ማድረግ መቻሉን ለአብነት ጠቅሰዋል። በክልሉ የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ መንደሮች ስራ መጀመሩን የጠቆሙት የቢሮው ኃላፊ፣ በመንግስት፣ ህብረተሰብ እና የአጋር አካላት ጥምረት መሆኑን አመላክተው፣ ይህም ወደ ህብረተሰብ ልማት የሚወስድ ስለመሆኑ ጠቁመዋል። ሀብቶች ለፍጆታ ብቻ ሳይሆን ወደ ላቀ የህዝብ ተጠቃሚነትና ወደ ቴክኖሎጂ ሽግግር መሄድ እንዳለባቸው እንደ ሀገርም የተቀመጠው አቅጣጫ በክልሉ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩን ተናግረዋል። ወደ ታች የሚወርዱ ሀብቶች እንዳይባክኑ በአግባቡ መጠበቅ ይገባል ያሉት ኃላፊው፣ ለስኬታማነቱ በቅንጅት መስራት እንደሚገባም አመላክተዋል። በውይይቱ የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥና በሴክተሩ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እንደሚጡ የስትሪንግ ኮሚቴው አባላት ተናግረዋል።

መጋቢት 28/2018 ዓ.ም የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ትምህርት ቢሮ የሙያ ፈቃድ ምዘና በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ለሚገኙ መምህራን እና ርዕሰ መምህራን በመሃል አምባ በዛሬው ዕለት ሰጥቷል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የመምህራን የሙያ ምዘና ፈተና ሚናው ከፍተኛ መሆኑን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት አስታወቀ። በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከ350 በላይ መምህራን የሙያ ምዘና ፈተና እንደወሰዱም ተመላክቷል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ የ2018 ዓ/ም አመታዊ አጠቃላይ የመመምህራን ምዘና በዛሬው እለት እየተሰጠ መሆኑን ገልጸው ይህም በተማሪዎች ውጤት መሻሻል ላይ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል። የትምህርት ጥራት ችግርን ለመፍታት በየደረጃው እና በየወቅቱ መምህራን እያበቁ፣ እየመዘኑ እና እያሰለጠኑ መሄድ አንዱ ቁልፍ ተግባር መሆኑ ገልፀዋል። አቶ አለማየው አክለውም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ አማካኝነት የምዘና ፈተናው የተዘጋጀ ሲሆን ከዝግጅት ጀምሮ አስፈላጊውን ጥንቃቄ መደረጉን ጠቅሰው በወረዳው ከ350 በላይ መምህራንና ርዕሰ መምህራኖች የሙያ ምዘና ፈተና እንደወሰዱ አስታውቀዋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የፕላን ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ዘይነብ ወራቄ፣ የወረዳው የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ባለሙያ፣የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት ባለሙያ አቶ ደስታ በሃጋ በጋራ በመሆን የመምህራንና ርዕሰ መምህራኖች የሙያ ምዘና ፈተና አስጀምረዋል።

መጋቢት 25/2018 ዓ/ም የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር የማህበረሰቡ እድገትና ስነ ልቦና በሚመጥን መልኩ በአዲስ ከተደራጀ ወዲህ ውጤታማና የሚቆጠር የባህልና የልማት ተግባራትን አከናውኗል፦ እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤው በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል!! የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የእለቱ የክብር እንግዳ (ዶ/ር) እንዳሻው ጣሰው እንዳሉት የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር በተለያዩ አደረጃጀት ለረዥም አመታት ተነጣጥሎ ሲመራ የቆየ ተቋም እንደነበር ጠቅሰው ጉልባማ የማህበረሰቡ እድገትና ስነ-ልቦና በሚመጥን አደረጃጀት በአዲስ እንዲመሰረት መደረጉን አስታውሰዋል። የልማት ማህበሩ የልማትና የባህል ስራዎችን በማጠናከር ከጊዜ ወደ ጊዜ እድገት እያሳየ መምጣቱንም ገልጸው እነዚህም ተግባራት በቀጣይም አጠናክሮ ሊያስቀጥል ይገባል ነው ያሉት። እንደ ማህበረሰብ የጀመርነው የጋራ ትርክትና የማህበረሰብ ግንባታ ስራ በሚታወቅና በተለዩ አጀንዳዎች ላይ መመስረት መቻል ይኖርበታል ብለዋል። የልማት ስራዎችን ለማጠናከርና የባህል ግንባታውን በትክክለኛ መስመር ለማስኬድ የተደራጁና ማህበረሰቡን ሊያሻግሩ የሚችሉ አጀንዳዎችን ቀርጾ መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል። እነዚህ የጋራ አጀንዳዎች የጉራጌ ማህበረሰብ የሚያውቃቸውና የሚጠቀምባቸው፣ ልማቱን የሚመራባቸው፣ ባህሉን የሚያሳድግባቸው፣ የተደራጀ አመራር የሚሰጥባቸውና ስለ እድገቱና ስለ ቤተሰቡ ብልጽግና የሚወያይባቸውና የሚደጋገፍባቸው ሊሆኑ እንደሚገባ አስረድተዋል። ከዚህም ባለፈ ከሌሎች ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች የተጠናከረ ግንኙነትና የጋራ እጣፈንታ የሚመለከትበትና በሀገር እድገት በኢኮኖሚያዊ፣ በፖለቲካዊና፣ በማህበራዊ ዘርፎች ያለውን ተሳትፎ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሳድግበት ሊሆን እንደሚገባም አመላክተዋል። የጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር የመንግስት ፖሊሲዎችን ተከትሎ በልማቱና በትውልድ ግንባታ ላይ ላቅ ያለ ተሳትፎ እንዲኖረው ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል። በዚህም በትውልድ ግንባታና በኢትዮጵያ በሚኖረን አጠቃላይ ተሳትፎ ላይ የድርሻውን መወጣት ይኖርበታል ብለዋል።