uk
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Відкрити в Telegram
917
Підписники
+124 години
+57 днів
-330 днів
Архів дописів
ከመጋቢት እስከ መጋቢት የማትበገረው ኢትዮጵያ  ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ "ስለ አለፈ ዘመናችን ስንናገር ከሚሰማን ኩራት ጋር ሲነጻጸር፣ ነገ የሚጠብቀን ተስፋ ቢበልጥ እንጂ አያንስም። ዋናው ጥያቄ ተስፋውን አይተን እውን ለማድረግ ምን ያህል ቁርጠኞች ነን? የሚለው ነው። ኢትዮጵያ የምትበለጽገው እኛ ለመለወጥ በፈለግንበት መጠንና የጋራ ራዕይ በሰነቅንበት ልክ ብቻ ነው። ኢትዮጵያ ካዘመመችበት ቀና የምትልበት ጊዜው አሁን ነው፡፡ ይኼን ለማሳካት የዛሬ ህያው ኢትዮጵያውያን ታላቅ አደራ ተጥሎብናል።" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ.ም ከተናገሩት የተወሰደ

መጋቢት 22/2018 ዓ/ም የመሃል አምባ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት አሠጣጥን ማዘመን የሚያስችል ሶፍት ዌር በአንድ ሚሊየን 380 ሺህ ብር ውል ተፈረመ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የመሃል አምባ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት አሠጣጥ ማዘመን የሚያስችል ሶፍት ዌር አገልግሎት ለማስጀመር መሀመድ አሚን እና ጓደኞቻቸው የሶፍት ዌር ዲዛይን እና ዴቨሎፕመንት ከተሰኘ ድርጅት ውል ተፈራረመ። ሶፍት ዌሩ በዋናነት የግንባታ ፍቃድ አሠጣጥ ፣የመሬት ልማት ማኔጅመንት አገልግሎት እና የማዘጋጃ ቤታዊ የገቢ አሠባሰብ ስርዓት አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን የሚያስችል ነው። ከ10 ሺህ በላይ መረጃዎችን ስካን በማድረግ ወደ ፋይል የሚያስገባ እና የመሬት ልማት ማኔጅመንት ፣የግንባታ ፍቃድ እና የገቢ አሰባሰብን የአንድ መስኮት አገልግሎት ለመስጠትም ያስችላል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን በውል መፈራረሙ ወቅት ተገኝተው እንደገለጹት ለከተሞች ዕድገት የማዘጋጃ ቤት አገልግሎት አሠጣጥን ማዘመን ወሳኝ በመሆኑ ሰፊ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመው ከወረቀት ነፃ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችል ትልቅ ተግባር በመሆኑ የማዘመን ሂደቱ በብቃት መምራትና መፈፀም አስፈላጊ መሆኑን ገልፀው የማዘጋጃ ቤት አገልግሎት አሠጣጥን ማዘመን ስራ የመሃል አምባ ማዘጋጃ ቤት የፈርጅ 3 ጥያቄ ለመመለስ የሚያግዝ በመሆኑ በወረዳ ደረጃ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። የወረዳው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተማም አደም በበኩላቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ማዘመን ተገልጋዩን ማህበረሰብንና የተቋሙን ባለሙያዎች በሙሉ ከድካምና ከተጨማሪ ወጪ የሚታደግ በመሆኑ አገልግሎት ለማስጀመር ከወረዳው  መንግስት ጋር ጥረት በማድረግ ላይ ቆይቶ የተለያዩ ኮሚፒዩተርንና ቁሳቁስ መዘጋጀቱን ጠቁመው ቀሪ ግብዓቶች በአጭር ጊዜ የማሟላት ስራ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል። በውል ስምምነቱ ወቅት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴንና አመራሮች፣የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎትና ስታዳርዳላይዜሽን ዳይርክቶሬት ዳይሬክተር ተፈሪ ድሜ ዶ/ር፣የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ማዘመን ፎካል አቶ አብደላህ ሳሊህ እና የጉራጌ ዞን የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ክንፈ እንዲሁም መሀመድ አሚን እና ጓደኞቻቸው የሶፍት ዌር ዲዛይን እና ዴቨሎፕመንት ስራስኪያጆች ተገኝተዋል።

መጋቢት 21/2018ዓ.ም ህብረተሰቡን በማሳተፍ የወረዳችን ሰላም ናፀጥታ ዘላቂ እና አስተማማኝ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ፅህፈት ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህን ያስታወቀው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ፅህፈት ቤት የ2018 ዓ.ም የ2ኛ ሩብ አመት የህዝብ ክንፍና የዜጎች ቻርተር ከባለድርሻ አካላት በተገኙበት ውይይት ባካሄደበት ወቅት ነው። የፅ/ቤቱ የ2018 በጀት አመት የ6ወራት አፈጻጸም በተቋሙ የልማት ዕቅድ ባለሙያ በወ/ሪት ብሩክ ቦቤ ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጎበታል ። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይ ወ/ሮ አስቴር ዮሐንስ በውይይቱ የተሰጡ አስተያየቶች እንደ ግብዓት በመውሰድ የቀጣይ የእቅድ አካል ተደርገው እንደሚሰሩ ገልፀዋል። ወ/ሮ አስቴር ዮሐንስ አክለውም የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ በሁሉም የመንግስት እርከኖች ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠትና ወቅታዊ ብሎም ቀጣይነት ያለው የመረጃ ምንጭ በመሆን ለህዝብ አስተዳደር እና ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት ከማገዙም በተጨማሪ ለትምህርት ፣ ለጤናና ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች እቅድ ዝግጅትና ፖሊሲ ለመቅረፅ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች ለማመንጨት የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ወሳኝ ሚናን እንደሚጫወት አስታውቀው ሰላም የህይወት ዋስትና በመሆኑ ህብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባና በነጻነት ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ እንዲችል ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል እና የጸጥታ መዋቅሩ በጋራ ተቀናጅቶ መስራት እንዳለበት አስታውቀዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከወሳኝ ኩነት መረጃ አያያዝ እና አመዘጋገብ ላይ ክፍተት መኖሩ፣የተቋሙ ድጋፋና ክትትል ማድረግ እንደሚገባ፣ጠንካራ የሆነ ቅንጅታዊ አሰራር መኖር እንዳለበት እንዲሁም በወረዳው የሚገኙ የወሰን ግጭቶችን ዘላቂ መፍትሄ መስጠት  እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። በመድረኩ የሴክተሩ የህዝብ ክንፍና የዜጎች ቻርተር አባላትና ከባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

መጋቢት 21/2018 ዓ.ም የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ከወረዳዎችና ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽህፈት ቤት አመራሮች ጋር የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ 9 ወራት ተግባር አፈጻጸም ግምገማ እና የቀጣይ አቅጣጫ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ  እያካሄደ ይገኛል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዶ ሀሰን መድረኩን ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት ጤናማ የገንዘብና የበጀት አስተዳደር እንዲኖር የፋይናንስ ተቋም ሃላፊነት መወጣት ይጠበቅበታል። የሀብት ቁጥጥር ስርአት ፣ የኦዲት ግኝት ላይ ከመቼውም ጊዜ በላይ አጽንኦትት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበትም  አብራርተዋል። ሁሉም ተግባራት በስታንዳርዱ መሰረት ከመፈጸም አኖጻር ያሉ ውስንነቶች በተገቢው በመቅረፍ በፋንናንስ ዘርፍ የተያዙ ግቦች ስኬታማ ማድረግ እንደሚገባም ተናግረዋል። በመድረኩ  የጉራጌ ዞን ምክር ቤት የኢኮኖሚ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ጠጄ ደነቀ፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችና ምክትል ሀላፊዎች እንዲሁም የኦዲት አስተባባሪዎችና የመምሪያው የማኔጅመንት አካላቶች ተገኝተዋል።

የሳምንቱ አበይት ዜናዎች መጋቢት 20/2018 ዓ.ም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የኢንጌ ማዘጋጃ ቤት በአዋጅ በተሠጠው ተግባርና ሀላፊነት ለመኖሪያ የሚውሉ ቦታዎች ለ9ኛ ዙር በሊዝ ጨረታ አወዳድሮ ለማስተላለፍ ዝግጁቱ አጠናቆ ተወዳዳሪዎችን ማወዳደር ይፈልጋል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በሰባተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ (ኮኪር ምርጫ ክልል) የሚወዳደሩ እጩዎች በመሀል አምባ ከተማ ተገኝተው የመራጭነት ካርድ ወሰዱ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የ5ተኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከመጋቢት 18 እስከ 21/2018 ዓ.ም ለተከታታይ አራት ቀናት ቤት ለቤት እንደሚሰጥ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የማህበረሰቡን ንጹህ መጠጥ ውኅ ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ውኅና ማዕድንና ኢነርጂ ጽ/ቤትገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሂደት ተጠናክሮ ቀጥሏል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ለሚያስፈጽመው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ “ለምርጫው ቀን” በሁሉም ጣቢያዎች ላይ ተጨማሪ አስፈጻሚዎችን ገለልተኝነታቸውንና መሥፈርቱን ማማላታቸውን አረጋግጦ በጊዜያዊነት ለመቅጠር ይፈልጋል።  በመሆኑም መሥፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች የተያያዘውን ማስፈንጠሪያ https://url-shortener.me/IUTH በመጠቀም ከዛሬ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት እንድታመለክቱ ቦርዱ ያሳውቃል። የምልመላ መሥፈርት፡- • ዕድሜው/ዋ ከ18 ዓመት በላይ የሆነ/ች፣ • የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፣ • የትምህርት ዝግጅት፦ 12ኛ እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች፣ • የሥራ ቦታ፦ ቦርዱ ባቋቋማቸው የምርጫ ጣቢያዎች፣ • የክልሉን የሥራ ቋንቋ መናገር እና መጻፍ የሚችል/ምትችል፣ • የሥራ ቆይታ ፦ ለሰባት ቀን፣ (ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ) በምርጫዬ የሞባይል መተግበሪያ ባሉበት ሆነው ራስዎን ለመራጭነት ይመዝግቡ!

መጋቢት 20/2018 ዓ/ም መንግስት የቤተሰብ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የጀመራቸው ስራዎች በህብረተሰቡ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት አስችሏል:-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በስልጤ ዞን ስልጢ ወረዳ በበጋ መስኖ የለማ የበቆሎ ማሳ የመስክ ምልከታ አድርገዋል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )በስልጤ ዞን ስልጢ ወረዳ አሹቴ ቀበሌ በበጋ መስኖ የለማ የበቆሎ ማሳ ምልከታ ባደረጉበት ጊዜ እንደገለጹት መንግስት የቤተሰብ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የጀመራቸው ስራዎች በህብረተሰቡ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት አስችሏል። አካባቢዉ ለበርካታ አመታት በጓርፍ በመጠቃቱ ህዝቡም ለተረጂነት የተጋለጠ እንደነበር ርዕሰ መስተዳድሩ አስታውሰዋል። ህብረተሰቡ፣ዞኑ እና ክልሉ በጋራ ተቀናጅተው በመስራታቸው አመቱን ሙሉ ያልተቋረጠ ምርት እንዲገኝ ምክንያት መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል። አካባቢው የጎርፍ ምሳሌ ከመሆን አልፎ በአመት አምስት ጊዜ አምራች ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። በክልሉ ከስልጠ ዞን ባለፈ በሀዲያ፣በሀላባ፣በጉራጌ፣በከምባታ እና በሌሎችም አካባቢዎች አመቱን ሙሉ አምራች መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል። በክልሉ ውሃን፣መሬትን እና ጉልበትን አቀናጅቶ መስራት በመቻሉ የህብረተሰቡን ኑሮ ማሻሻል ስለመቻሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል። በክልሉ ከሰብል ልማት ባለፈ በሌማት ትሩፋት የተገኘው ውጤት ገበያውን ለማረጋጋት የላቀ ሚና እንዳለውም ጠቁመዋል። ህብረተሰቡ በሁሉም ዘርፍ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ርዕሰ መስተዳደሩዳድሩ አሳስበዋል።

ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚዲያ አጠቃቀም እና የድልድል ቀመር ይፋ ሆነ ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚውለውን የነፃ የሚዲያ አጠቃቀምና የድልድል ቀመር ይፋ አድርጓል። ድልድሉ ፍትሐዊነትንና አካታችነትን መሠረት ያደረገ ሲሆን፣ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች ያካትታል፦ ✅ የድልድል መመዘኛዎች፦ ድልድሉ 40% ለሁሉም እኩል፣ 25% እንደ እጩዎች ብዛት፣ 15% ለሴት እጩዎች፣ 15% ለአካል ጉዳተኛ እጩዎች እንዲሁም 5% ለሴት አካል ጉዳተኛ እጩዎች ትኩረት ሰጥቶ ተዘጋጅቷል። ✅ የተመደበ የሚዲያ መጠን፦ ለ47 የፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል እጩዎች በድምሩ፦ • 782.5 ሰዓታት በሬዲዮ፤ • 513 ሰዓታት በቴሌቪዥን፤ • 576 አምዶች በጋዜጣ ተመድቧል። ✅ የሚሳተፉ ተቋማት፦ በምርጫ ቅስቀሳው ወቅት 24 የሬዲዮ ጣቢያዎች፣ 20 የቴሌቪዥን ጣቢያዎች እና 6 የሕዝብ ጋዜጦች አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ ሆነዋል። ይህ አሠራር ሁሉም ተፎካካሪዎች አማራጭ ሐሳባቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበት የዴሞክራሲያዊ ምኅዳር ማሳያ ነው። Ethiopian Broadcasting Corporation

ከእርዳታ ጥገኝነት ወደ ምግብ ሉዓላዊነት የተደረገ ታሪካዊ ሽግግር በስንዴ ልማት ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ባለፉት ስምንት ዓመታት በኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ደማቅ ስኬቶች መካከል የስንዴ ልማት ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል። ኢትዮጵያ ለፍጆታ የሚሆን ስንዴን ከውጭ ለማስገባት በዓመት 1 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ታወጣ የነበረበትን ታሪክ በመቀየር፣ ዛሬ ላይ ራሷን ችላ ምርቷን ለዓለም ገበያ መላክ የጀመረችበት አዲስ የከፍታ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ለዚህ ተአምራዊ ስኬት ዋነኛው ምክንያት "የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት" ስትራቴጂ ሲሆን፣ ይህም የምርት መጠኑ ከእጥፍ በላይ እንዲያድግና መሬትን በዓመት እስከ ሦስት ጊዜ በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ አስችሏል። በ2015 ዓ.ም ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ መላክ መጀመሯ በምግብ ራሷን የመቻል ግቧን በተግባር ማሳካቷን ለዓለም ያበሰረችበት ታላቅ ክስተት ነበር። ይህ ስኬት በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት አይነት ዓለም አቀፍ ቀውሶች በሀገር ውስጥ የዳቦና የዱቄት አቅርቦት ላይ የከፋ ችግር እንዳያመጡ ትልቅ መከላከያ ሆኗል። በተጨማሪም ዓመታዊ የስንዴ ምርትን ወደ 231 ሚሊዮን ኩንታል በማድረስ የስንዴ ገቢ ምርትን ሙሉ በሙሉ በማስቀረት ወደ ውጭ የመላክ አቅም ተፈጥሯል። የኢትዮጵያ የስንዴ ልማት ስኬት እንደ ዓለም አቀፉ የግብርና እና የምግብ ድርጅት (FAO) ባሉ ተቋማት እውቅናን ያገኘ ሲሆን፣ አርሶ አደሩንም ከቤት ፍጆታ ባለፈ ወደ ገበያ መርና ዘመናዊ የሜካናይዜሽን ግብርና ተጠቃሚነት አሸጋግሮታል። የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ከኢኮኖሚ ባለፈ የሀገርን የፖለቲካ ነፃነትና የውሳኔ ሰጪነት አቅም የሚያሳድግ በመሆኑ፣ ይህ ውጤት ኢትዮጵያ በ2030 መካከለኛ ገቢ ያላት ሀገር ለመሆን ለያዘችው ራዕይ አንድ ስኬት ተደርጎ የሚጠቀስ የታሪክ ምዕራፍ ነው። ይህ ባለፉት ስምንት ዓመታት የተገኘ አስገራሚ ለውጥ ኢትዮጵያ እየገነባች ላለው የማይበገር ኢኮኖሚ አንዱ አበርክቶ ያለው ሲሆን በፈተናዎች አልፋ የጸናች ኢትዮጵያን የመፍጠር ህልም እየተሳካ እንደሆነ ማሳያ ሆኗል። Ethiopian Broadcasting Corporation #WheatProduction #FoodSovereignty #AgriculturalRevolution #IrrigationFarming