1 088
Підписники
Немає даних24 години
+227 днів
+1330 день
Архів дописів
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በኦፊስ ካይዘን ትግበራ ዙሪያ ለቢሮው ሰራተኞች ስልጠና አዘጋጀ።
በዚህም ስልጠናውን ከአስተዳደሩ የካይዘን ኢንስቲትዩት በመጡ ባለሙያ የተሰጠ ሲሆን በቢሮው የሚገኙ ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች በቀጣይ የሚኖረውን ትግበራ ውጤት ሊያስገኝ በሚችል መልኩ እንዲከውኑ የሚያግዝ ይሆናል።
ቢሮው ለሪፎርም ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን እነዚህም ስራዎች የሆነ ጊዜ ብቻ ተግባር አለመሆኑ በሚያሳይ መልኩ የዚህ ትግበራ አካል የሆነው ኦፊስ ካይዘንን በሁሉም የቢሮው ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች ላይ ተግባራዊ ማድረግ በተለየ መልኩ ቦታ ተሰጥቶታል።
በመሆኑም መጀመር ብቻ ሳይሆን ማዝለቅ እንደሚገባና ጥሩ አፈጻጸም የሚያስመዘገቡ ዳይሬክቶሬቶች፣ ክፍሎችና ሰራተኞችን ቢሮው እንደሚያበረታ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 11/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
41 የማምረቻና መሸጫ ክፍሎች ያሉት G+2 ህንጻ ግንባታው ተጠናቆ የርክክብ ስነስርዓት ተካሄደ።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በ48 ሚሊየን ብር ወጪ ግንባታው የተከናወነውን ጀርባ ሰፈር የሚገኝ ህንጻ የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ለአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንደስትሪ ክላስተር ልማት ኮርፖሬሽን ስራ አስኪያጅ ለሆኑት አቶ ኡስማን አህመድ የቁልፍ ርክክብ አድርገዋል።
በቢሮው የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም እንደገለጹት ከዚህ ቀደም ጎሮ፣ ዲፖ፣ ኮኔል፣ ጫትተራ፣ ለገሃሬ(oxfam) እና ገንደገበሬ ሳይቶች በተመሳሳይ መልኩ ተሰርተው ለተጠቃሚዎች የተላለፉ መሆኑን አስታውሰው አሁን ላይ ርክክቡ የተካሄደው ይህም የጀርባ ሳይት በአስተዳደሩ ለሚገኙ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች የሚደረገውን የቦታ ምችችት ድጋፍ በተሻለ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 11/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
“ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ” የመጀመሪያ ዙር ማጠቃለያ እና ሁለተኛ ዙር ማስጀመሪያ መርኃግብር በደማቁ በዛሬው ዕለት ከመካሄዱ ጎን ለጎን በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ አንቀሳቃሾችና እና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እንቅስቃሴ ተጎበኘ፡፡
በሥራና ክህሎት ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ የልዑክ ቡድን በጉብኝቱ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በዋናነት የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማዕከል ግንባታ ሂደትን ተዟዙረው የተመለከቱ ሲሆን ከዚህ ጎን ለጎን በትምህርትና ስልጠናው፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በኢንዱስትሪ አታችመንት የተከናወኑ ውጤታማ ስራዎችን አድንቀው በቀጣይ ያለውን እምቅ አቅም አጉልተው የሚያሳዩ ተግባራት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፤
በተያያዘ በኢንተርፕራይዝ ልማት ረገድ ሥራ ፈጣሪዎችን በአካል የሚሰሩበት መስሪያ ቦታ በአካል በመገኘትና በመመልከት በማበረታታት ከድጋፍ አኳያ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቦታ ምችችት ፍላጎት ምላሽ የሚሰጡ ግንባታዎችን በተለይም ጀርባ ሰፈር የሚገኘውን ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነውን ህንጻ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 9/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ቢሮ የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በጀመረው እራሱን በቴክኖሎጂ የማስታጠቅ ስራ የሚውል ዘመናዊ ኮምፒዩተሮች ድጋፍ አደረገ፡፡
===================================
ይሄው ድጋፍ ተቋሙ ለጀመረው ስራዎችን በቴክኖሎጂ የማከናወን ተግባር እጅግ ከፍተኛ የሆነ እገዛ እንደሚኖረው በርክክቡ ወቅት ተገልጿል።
የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ እያከናወነ ባለው ዘርፈ ብዙ ስራዎች መደነቃቸውን የገለጹት የድሬደዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሁን በያዘው የከተማውን ሰላም እና ጸጥታ የማረጋገጥ ስራ በቴክኖሎጂ ተደግፎ እና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ለማስቻል ድጋፉን ማድረግ መቻላቸውን ጠቅሰው ይሄው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጨምረው ተናግረዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክቡር ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ በበኩላቸው ለተደረገው ድጋፍ የድሬደዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ለአቶ ሮቤል ጌታቸው ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በለውጥ ጎዳና ላይ መሆኑን የገለጹት ክቡር ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ተቋሙ እራሱን በቴክኖሎጂ ለማስታጠቅ እያደረገ ላለው ስራ የተደረገው ድጋፍ ከፍተኛ እገዛ እንዳለው ጠቅሰው የከተማችንን ሰላም አስተማማኝ ለማድረግ ከህብረተሰቡ ፤ከጸጥታ አካላት፤ ከባለሃብቱ ጋር በጋራ እያከናወኑ ያሉትን ስራዎች አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጨምረው ተናግረዋል፡፡
©️ ድሬ ፖሊስ
“ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ” ሁለተኛ ዙር ፕሮግራምን ዛሬ በምስራቋ ፈርጥ ድሬዳዋ ከተማ ከክቡር አቶ ከድር ጁዋር እና የሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር በይፋ አስጀምረናል፡፡
ፕሮግራሙ በአንድ በኩል ትምህርታቸውን በተለያየ ምክንያት ያቋረጡ ወጣቶች ብቁ፣ ተወዳዳሪና አምራች እንዲሆኑ በሥራ ላይ ልምምድ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ልምምድ በሚያደርጉበት ተቋም ቋሚ ሥራ የሚያገኙበትን ዕድል ከመፍጠሩም በላይ በመንግስትና በግል ተቋማት መካከል ያለውን ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ ማሻሻል የሚያስችል ነው፡፡
ከማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ጎን ለጎን የድሬ ዳዋ ከተማ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን እና ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር ያስገነባውን የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ ያስመረቅን ሲሆን በከተማው ውስጥ የተሻለ ተሞክሮ ያላቸውን አንቀሳቃሾችን እና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅን ጎብኝተናል፡፡
ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ
የሥራና ክህሎት ሚንስትር ዴኤታ
“ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ” ሁለተኛ ዙር ፕሮግራምን ዛሬ በምስራቋ ፈርጥ ድሬዳዋ ከተማ ከክቡር አቶ ከድር ጁዋር እና የሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር በይፋ አስጀምረናል፡፡
ፕሮግራሙ በአንድ በኩል ትምህርታቸውን በተለያየ ምክንያት ያቋረጡ ወጣቶች ብቁ፣ ተወዳዳሪና አምራች እንዲሆኑ በሥራ ላይ ልምምድ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ልምምድ በሚያደርጉበት ተቋም ቋሚ ሥራ የሚያገኙበትን ዕድል ከመፍጠሩም በላይ በመንግስትና በግል ተቋማት መካከል ያለውን ግንኙነት በከፍተኛ ደረጃ ማሻሻል የሚያስችል ነው፡፡
ከማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ጎን ለጎን የድሬ ዳዋ ከተማ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን እና ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር ያስገነባውን የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ ያስመረቅን ሲሆን በከተማው ውስጥ የተሻለ ተሞክሮ ያላቸውን አንቀሳቃሾችን እና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅን ጎብኝተናል፡፡
አቶ ሰለሞን ሶካ
የሥራና ክህሎት ሚንስትር ዴኤታ
ዛሬን ለነገ እንስራ!!
"ብቃት" የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም የመጀመሪያ ዙር በዛሬው እለት በደማቅ ስነስርዓት ተጠናቋል። በፕሮግራሙ ትግበራ ምን አሳካን?
#ስኬት -1
በዚህ ፕሮግራም ለስድስት ወራት የስራ ላይ ልምምድ ያደረጉ 931 ወጣቶች ሙሉ በሙሉ በአስተዳደራችን በሚገኙ የግል ድርጅቶች ውስጥ ተቀጣሪ ሆነዋል።
#ስኬት - 2
በወረዳ 03 ለስራ ፈላጊዎች ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ አንድ ማዕከል በአራት ወራት ተገንብቶና አስፈላጊ የቢሮ ግብዓቶች ተሟልተውለት በዛሬው እለት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
#ስኬት - 3 ፕሮግራሙ ተግባራዊ ከተደረገባቸው 10 ትላልቅ የሀገራችን ከተሞች ጋር በ3 ዘርፍ ተወዳድረን በሁለት ዘርፎች አንደኛ በመውጣት እውቅናና ሽልማት አግኝተናል።
ሌላም ሌላም ሌላም.........
ዛሬ የመጀመሪያ ዙርን በዚህ ደረጃ በላቀ አፈፃፀም ማጠናቀቃችን ለሁለተኛ ዙር መሳካት ታላቅ መነሳሳትን ይፈጥራልና የቢሯችን አመራሮች እና ባለሙያዎች እንዲሁም የወረዳ አመራሮችና ፈፃሚዎች እንኳን ደስ አላችሁ እያልኩ ለቀጣይ ስኬት ራሳችንን እናዘጋጅ እላለው።
ለስኬት ዝግጁ!!
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
# ዜና ባለፍት አመታት በስራ እድል ፈጠራ ዙሪያ በርካታ ስራዎች መሰራታቸው ተገለፀ ።
" ብቃት " የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የመጀመሪያ ዙር ማጠቃለያ እና የሁለተኛ ዙር ማስጀመሪያ መርሀ-ግብር በዛሬው እለት ተካሂዷል ። በዚሁ መርሀ-ግብር ላይም በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ከቲባ የተከበሩ ከድር ጁሀር ወጣቶች በወጣትነት እድሜያቸው ጠንክረው በመስራት ከራሳቸው አልፈው ቤተሰባቸውን እንዲሁም ከተማቸውን እና ሀገራቸውን ማገዝ እንዲሁም ማገልገል እንዳለባቸው ተናግረው ለዚህ ስራ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፆ ላበረከቱ ሁሉ ክቡር ከንቲባው በእለቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
" ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት " በአስተዳደሩ ላይ የፈጠረውን የስራ ተነሳሽነት እና ፕሮጀክትን ከመንግስት የትኩረት አቅጣጫ ከመተግበር አንፃር እጅግ ውጤታማ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ ተናግረው ፕሮጀክቱ በስራ እድል ፈጠራ ላይ እያሳደረ የመጣውን በጎ ተፅእኖ በመረዳት በቀጣይነት ጠንክረን በመስራት በመደበኛ ስራችንም ባህል እና ልምድ በማድረግ ማስቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሀገራዊ ሪፎርሙን ተከትሎ የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራው ክህሎት መር እንዲሆን አቅጣጫ አስቀምጦ በዘርፉ ሰፊ ርብርብ በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን በዚህም በመደበኛ የሥራ ዕድል ፈጠራ ከሚያከናውናቸው ተግባራት ጎን ለጎንም ከዓለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የተለያዩ ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶች ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሚኒስቴር ዲኤታ የሆኑት አቶ ሰለሞን ሶካ ተናግረዋል ።
በዚሁ ፕሮግራም የታቀፍ ወጣቶች በአፍላ እድሜ ላይ የሚገኙ እና በትምህርትም ብዙም ያልገፍ በመሆናቸው ከስራ ላይ ልምምዱ በተጨማሪ ሶስት የተለያዩ ስልጠናዎች የህይወት ክህሎት ፣ መሰረታዊ የኮምፒዩተር ክህሎት እና የስራ አፈላለግ ክህሎት እንዲያገኙ መደረጉን የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረው በዚህም ለራሳቸው ያላቸው ግምት ከመሻሻሉም በላይ በራስ መተማመናቸው በመጨመር ሰልጣኞች ያላቸውን መረጃ እና ልምድ በመለዋወጥ እርስ በእርሳቸው የሚኖራቸው አዎንታዊ ትስስር ያሳደገ የአቻ ለአቻ ውይይቶችን እንዲያካሄዱ መደረጉንም ነው የተናገሩት ።
ይህ በእንዲህ እንዳለም የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ከስራ ክህሎት ሚኒስቴር እና ከአለም ባንክ ጋር በመተባበር ያስገነባው የወረዳ 03 የአንድ ማእከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያም በዛሬው እለት በይፋ ተመርቋል ።
©️ የድሬዳዋ መንግስት ኮምንኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
ላለፉት 2 ቀናት “ከዕዳ ወደ ምንዳ” በሚል ርዕስ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና ሁለቱ የመንግስት ኮሌጅ አስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኝ መምህራን ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቅቋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ስልጠናው በተለያዩ ሀገራዊ እና አስተዳደራዊ የመንግስት ነባራዊ ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ በተዘጋጁ የስልጠና ሰነዶች ዙሪያ ላይ ያተኮረ ሲሆን የመንግስት ሠራተኛውን አቅም በማጎልበት ኢትዮጵያ ብሎም አስተዳደሩ ለጀመሩት የእድገትና ለውጥ ጉዞ ወሳኝ ሚናቸውን እንዲወጡ የሚያስችላቸው ግንዛቤ እንዲይዙ የሚያስችል አቅም የተፈጠረበት ስልጠና ነው ብለዋል።
በተመሳሳይ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የቢሮው የመንግሥት ሠራተኞች በአጠቃላይ ስልጠናው ሠራተኛው ራስን ከመምራት ጀምሮ ህዝብን በሚገባ ማገልገል እንዲችልና በሠራተኛው ዘንድ የተግባርና የሀሳብ አንድነት በማምጣት ቀጣይነቱ የተረጋገጠ ጥራት ያለውና ፍትሀዊ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችልና የሚያስረዳ ግንዘቤ መፍጠሩን ተናግረዋል።
በስልጠናው ማጠናቀቂያ ሰልጣኝ የቢሮውና የኮሌጆች አስተዳደር ሠራተኞች እና አሰልጣኝ መምህራን በስልጠናው የቀረቡ ሰነዶች ላይ ግልጽነት የሚያስፈልጋቸውን ነጥቦች በማንሳትና በመጠየቅ ከመድረክ ሰፊ ማብራሪያ እና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል በመጨረሻም ሰልጣኞች በተሰጣቸው የግንዛቤ ማጎልበቻ ስልጠና መደሰታቸውን ገልጸው መንግስት የጀመረውን እድገትና ለውጥ እንዲያስቀጥል በማሳሰብ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 7/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
''ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የአቅም ግንባታ ስልጠና በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ስር ለሚገኙ የአስተዳደር ሰራተኞችና አሰልጣኝ መምህራን መሰጠት ጀመረ፤
በአቅም ግንባታ ስልጠናው ላይ በክብር እንግድነት በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የድሬዳዋ ብልጽግና ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ እንደተናገሩት ይህ ስልጠና የመንግስት ሰራተኛው የመንግስትን አቅጣጫ በመረዳትና መግባባትን በመፍጠር የአስተዳደራችንን አልፎም የሀገራችንን ብልጽግና በማረጋገጥ ሂደት ላይ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል፤
የቢሮው አስተዳደር ሰራተኞች እና አሰልጣኝ መምህራን ዛሬን ጨምሮ ለሚቀጥሉት 2 ተከታታይ ቀናት "ሀብት እና ብልፅግናን መፍጠር እና ማስተዳደር እንዲሁም አገልጋይና ስልጡን ሲቪል ሰርቪስን መገንባት" በሚሉ ርዕሶች በቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ስልጠናው ለተከታታይ ሁለት ቀናት ከየካቲት 6-7/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 6/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
እንኳን ደስ አላችሁ!!
እንኳን ደስ አለን!!
በሰመራ ከተማ "ሥራ በክህሎት ይመራ!" በሚል መሪ ሃሳብ ሲካሄድ የቆየውና የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ እና የምክክር መድረክ ሲጠናቀቅ "ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር አፈጻጸምን አስመልክቶ በሶስት ዘርፎች በተካሄደ ውድድር የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በሁለት ዘርፎች በማሸነፍ ከዕለቱ የክብር እንግዳ ክቡር አቶ ንጉሡ ጥላሁን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ እጅ የዋንጫ እና የተለያዩ ቁሳቁስ ሽልማት ተበርክቶልናል።
የቢሯችን አመራሮችና ሰራተኞች፣ የአንድ ማዕከላት፣ ፖሊቴክኒክ ኮሌጆቻችን እንዲሁም ኢንተርፕራይዞችና ኢንዱስትሪዎች ያለእናንተ ትጋትና ተናቦ መስራት የተገኘው ውጤት የማይታሰብ ነውና እንደ አገር ላገኘነው እውቅናና ሽልማት እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን እያልኩ እንደ አስተዳደር በከተማና በገጠር የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎችን አጠናክረንና በተነቃቃ መልኩ ለመተግበር ትልቅ መነሳሳትንና ብዙ እድሎችን የሚፈጥርልን በመሆኑ በድጋሚ መላው የአስተዳደራችንን ነዋሪ እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን ለማለት እወዳለሁ፡፡
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
የ2016 ዓ.ም የሥራ ዕድል ፈጠራ እንዲሁም "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም የመጀመሪያ ዙር አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በውስጡ ከሚገኙ ዘርፎች የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አንዱ ሲሆን ለዜጎች የሥራ ዕድልን በመፍጠር አሁን ያለውን የሥራ አጥ ቁጥር ለመቀነስና የሥራ ባህልን በማጎልበት የሚያስፈልጓቸውን የሙያና የክህሎት ስልጠናዎች ወስደውና ወደ ሥራ እንዲሰማሩ በማመቻቸትና ራሳቸውን ከሥራ አጥነት እንዲያላቅቁ በማድረግና በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡
በዚህም የሚመለከታቸው የቢሮው አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁም የወረዳ ሥራ ክህሎት ማስተባበሪያዎች በተገኙበት በ2016 በጀት አመት አጠቃላይ የሥራ ዕድል ፈጠራ በተለይም በብቃት ፕሮግራም የመጀመሪያ ዙር የተሰሩ ስራዎች አፈጻጸም ላይ ሁሉም የወረዳ አንድ ማዕከላት አፈጻጸማቸው ቀርቦ ሰፊ ውይይት በማድረግ በቀጣይ ሁለተኛ ዙር የፕሮግራሙ ትግበራ በአጭር እና በረጅም ጊዜ መሰራት በሚገባቸው ሥራዎች ላይ መወያየትና መግባባት መፍጠር ተችሏል፡፡
በማጠቃለያው ባለፉት ስድስት ወራት በሥራ እድል ፈጠራ ዘርፍ በርካታ ስራዎች የተሰሩ መሆናቸውንና በዋናነትም የተመዘገቡ ሥራ ፈላጊዎች ወንድ 5620 ሴት 9734 ድምር 15,354 ሲሆን በአጠቃላይ በቋሚ እና በጊዚያዊ 9,004 የሥራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ ወንድ 4,957 ሴት 3,664 ድምር 8,621 የሥራ እድሎችን መፍጠር መቻሉን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 3/2016 ዓ.ም
ሐረር
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
