1 085
Підписники
+924 години
+207 днів
+1530 день
Архів дописів
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠናን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ለአገር ኢኮኖሚ እድገት ያለው ድርሻ የማይተካ ነው
****
(ኢ.ፕ.ድ)
ቴክኒክና ሙያን በአግባቡ መጠቀም ተግዳሮቶቹንም መፍታት ከተቻለ ለአገር ኢኮኖሚ እድገት ያለው ድርሻ የማይተካ መሆኑን የዘርፉ ምሁራን አስገነዘቡ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እያከበረ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አካል የሆነው የፓናል ውይይት "ቴክኒክና ሙያ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ በዘርፉ ለረጅም አመታት የሥራ እና የትምህርት ልምድ ያላቸው ምሁራን የመወያያ ጽሁፎችን አቅርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል።
በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት የአመራርና ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ሃላፊና የዘርፉ ባለሙያ የሆኑት አቶ አበባው ለማ ባቀረቡት ጽሁፍ፣ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ምቹ የስራ እድልን በመፍጠር የሀገርን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑን አመላክተዋል።
በዚህ መነሻነት ዘርፉ ላይ የሚሰጠው ስልጠና ውጤት ተኮር ስራን የተከተለና ከገበያና ኢንዱስትሪ ፍላጐት የሚመነጭ ሊሆን እንደሚገባው ገልጸዋል።
ለዚህ ደግሞ የግሉን ዘርፍ አሁን ካለውም በላይ በስፋት ማሳተፍ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
የኢንዱስትሪና የከተማ መሰረተ ልማት ፖሊሲ ጥናት ማእከል ሃላፊ አማረ ባህተቡ (ዶ/ር) በኩላቸው፣ ቴክኖሎጂ እንዲያድግ ቴክኒክና ሙያ ላይ ተጨባጭ ስራዎችን መስራት ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ አራተኛው የኢንዱስትሪ አብዮት ቴክኖሎጂ ላይ እንድትደርስ እንደ አውቶሜሽንና መሰል የክህሎት ማበልጸጊያ ስራዎች ላይ መስራት እንዳለባትም ዶክተር አማረ ገልጸዋል።
ከፍተኛ የፖሊሲ አማካሪ አንቶኒዮስ ፍሊቼ፣ "ስልጠና ከሌለ ኢኮኖሚ የለም። የአንድ ሀገር ኢኮኖሚ የሚጐለብተው የሰው ሀይል ልማት ላይ ከተሰራ ነው። ሰራተኛን ማልማት ካልተቻለ ኢኮኖሚን ማሰብ አአፕቻልም፤ ቴክኒክና ሙያ ከሌለ ኢኮኖሚ የለም" ብለዋል።
እንደ ጀርመን፣ ጃፓንና አንድ አንድ የምእራብ አፍሪካ አገራት በዚህ ረገድ በዘርፉ ያላቸው ተሞክሮ አመርቂ መሆኑና ኢትዮጵያም በተለይ ኢንዱስትሪ ላይ የሚሰጡ ስልጠናዎችን በማዳበር ከቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ የሚገኘውን ዘርፈ ብዙ ጥቅም ልታገኝ ይገባል ነው ያሉት።
በፓናል ውይይቱ ላይ በበቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ በቂ ክህሎትና ስብእና ያለውን ባለሙያ ለማፍራት ባለፉት አመታት በርካታ ስራዎች መከናወናቸው ተገልጿል።
የቴክኒክና ሙያ ስትራቴጂ መከለሱም ዘርፉን ብቃት ባለው የሰው ሀይል ማነቃቃት ተችሏል ነው የተባለው።
እስካሁን በዘርፉ ከተመዘገቡት ውጤቶች ባሻገር በተለይ ከትምህርት ጋር ተያይዞ ተግዳሮቶች ማጋጠማቸው የተነሳ ሲሆን፤ የፓናል ውይይቱ መሰል ችግሮችን ለመፍታት አንኳር ሀሳቦች የሚነሱበትና ወደ ፊት ዘርፉን ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ ግብአቶች እንደሚገኝበት ተብራርቷል።
በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ተማሪዎች በትምህርት ቤት በቂ ክህሎት ይዘው መውጣት ላይ ከፍተኛ ክፍተት መኖሩና ለዚህ ደግሞ የግሉን ዘርፍ ተሳታፊ ያደረገ ትኩረት እንደሚሻ፣ የወጡ ፖሊሲዎችን በአግባቡ ተግባራዊ የማድረግ ሃላፊነት ከመንግስትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እንደሚጠበቅ ተነስቷል።
©️ ኢ.ፕ.ድ
የኢንተርፕሩነርሺፕና የንግድ ሥራ ክህሎት ስልጠና በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መደበኛ ስልጠናቸውን ለሚያጠናቅቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በዛሬው እለት መሰጠት ተጀመረ፡፡
በስልጠናው መክፈቻ እለት በመገኘት ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግግራቸውም ሰልጣኝ ተማሪዎች በኮሌጅ ውስጥ የነበራቸውን ትምህርታቸውና ስልጠና አጠናቀው ሲወጡ የግላቸውን ስራ ፈጥረው ራሳቸውን፣ ቤተሰባቸውንና ብሎም አገራቸውን እንዲጠቅሙ ከመደበኛው ስልጠና በዘለለ እንዲህ አይነት ስልጠናዎችን መስጠት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን ። አቶ ሳሊም አያይዘውም ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ሰልጣኝ ተማሪዎች ከቅጥር ይልቅ ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ማስቻል ዋና አላማቸው ስለሆነ ሁሉም አካላት ለዚህ ስራ ተረባርቦ መስራት ይገባቸዋል ብለዋል፡፡
በዛሬው እለት እየተሰጠ የሚገኘው የኢንተርፕሩነርሺፕና የንግድ ሥራ ክህሎት ስልጠና በኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት (EDI) እና በኮሌጁ የተዘጋጀ ነው። የስልጠናውም ለ4 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ እንደሆነ በስልጠናው ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሰኔ 17/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
#ዜና | የድሬዳዋ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች፥ የምረቃ እና የሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ።
የአስተዳደሩ ስራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ባዘጋጀው መርሀ ግብር ላይ ሽግግር ያደረጉት ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ፣ ከኢ- መደበኛ ወደ መደበኛ፣ ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ፣ ከጥቃቅን ወደ አነስተኛ ማኑፋክቸሪንግ እንዲሁም ከኢንተርፕራይዝ ወደ ሞዴል ኢንተርፕራይዝ መሆኑ ተገልጿል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ ከንቲባ ተወካይ እና የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሙሉካ መሀመድ ባደረጉት ንግግር፥ ካፒታል ቆጥባችሁ ስራ ፈጥራችሁ ላሳያችሁት እድገት ምስጋና እና እውቅና ይገባችኋል ብለዋል።
ወ/ሮ ሙሉካ አክለውም፥ በተለያየ የስራ መስክ የተሰማሩት እነዚህ ግለሰቦች ከራስ አልፎ ለሌሎች የስራ እድል በመፍጠር እንደ አስተዳደር ያለውን የስራ አጥ ቁጥር ከመቀነስ አኳያ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታሉ ብለዋል።
የድሬዳዋ ስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው፥ ካለፉት 10 አመታት ጀምሮ በአነስተኛና ጥቃቅን ዘርፍ ተሰማርተው የተለያየ ድጋፍ ሲደረግላቸው ለቆዩ 93 አንቀሳቃሾች ሽግግር እና እውቅና መሰጠቱን ተናግረዋል።
በኢንተርፕራይዞች ሽግግር መርሀ ግብሩ ማብቂያ ላይ የእውቅና ሰርተፊኬት፣ የገንዘብ እና የዋንጫ ሽልማት ተሰጥቷል።
©️ DireTVአማርኛ
+1
ለድሬዳዋ ልማት ማህበር የሚደረገው ድጋፍ ቀጥሎ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ለማህበሩ የበኩላቸውን ድጋፍ አድርገዋል።
የሥራና ክህሎት ምክርቤት ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱ ለአስተዳደሩ ክህሎትን መሠረት ያደረገ የስራ ዕድል ለዜጎች ለማመቻቸት መደላድል መፍጠሩ ተገለጸ።
እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር አስፈጻሚና ባለድርሻ አካላትን በማቀናጀት በአስተዳደር ደረጃ ባልተቀናጀ መልኩ ሲፈጸም የነበረውን የሥራ ዕድል ፈጠራና የቴክኒክና ሙያ የሰው ኃይል ልማት ሥራን የአስፈጻሚና ባለድርሻ አካላትን ተሳትፎና ቅንጅት ባረጋገጠ መልኩ እንዲመራ ለማድረግ አዲስ የአደረጃጀትና የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት የአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ምክርቤት መቋቋሙ ይታወሳል።
በዛሬው ዕለትም የአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ምክርቤት የ2016 መደበኛ ጉባኤውን የአስተዳደሩ ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሃር በተገኙበት ሲያካሂድ በዋናነት ከዚህ በፊት ይታይ የነበረውን የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ክፍተት የሚደፍንና ለተሻለ መተባበር የሚያነቃቃ እንዲሁም ሁሉም የድርሻውን ኃላፊነት የሚወጣበት ስልታዊ አቅጣጫዎች የተመላከቱበት ሆኗል።
እንደ አስተዳደር የተቋቋመው ምክርቤት በየደረጃው የተቋቋሙ የሥራና ክህሎት ምክርቤቶችን በበላይነት የሚመራና የሚከታተል ሲሆን በዋናነት ከሥራ ገበያው ወይም ከኢንዱስትሪው የሰው ኃይል ፍላጎት እና ከሥራ ፈላጊዎች የሥራና የሙያ ምርጫ ጋር የተስማማ መካከለኛና መለስተኛ ክህሎት ያለው የሰው ኃይል በማዘጋጀትና በማቅረብ የሥራ እድል ፈጠራ ሥራዎችን ጊዜንና ሀብትን በሚቆጥብ አግባብ በአንድ መዋቅር የሚመራና የሚፈጸም ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 13/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
#ዜና በክህሎት ላይ የተመሰረተ የስራ እድል መፍጠር እንደሚገባ ተገለፀ
#DGC ሰኔ 13/2016
የድሬደዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የ2016 የስራና ክህሎት ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ተካሂዷል።
በመድረኩ የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ የተከበሩ ከድር ጁሃር መንግስት በተለያዩ ደረጃዎች የሚኖሩ የስራ ፍላጎቶችን ብቻውን የማሟላት አቅም እንደማይኖረው ገልፀው የግል ተቋማትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በዘርፈ ተገቢውን እርብርብ በማድረግ የዜጎችን የስራ ፈጠራ ጥረት ማገዝ እንደሚገባቸው አስረድተዋል።
ምንም እንኳን ከወጣቶች የስራ ባህልና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች አንፃር እጅግ በጣም መሰራት የሚገባቸው የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎች ቢኖሩም በዛው ልክ አርአያ መሆን የሚችሉ ከዩንቨርስቲም ተመርቀውም ሆነ በተለያዩ ሁኔታዎች ስራን ፈጥረው በመንቀሳቀስ ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የስራ እድል መፍጠር የቻሉ ወጣቶች መኖራቸውን ከንቲባው አመላክተዋል።የእነዚህን ወጣቶች ተሞክሮ ወደ ሌሎች ማስፋትም እንደሚገባ ገልፀዋል።
የድሬደዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮበል ጌታቸው የስራ እድል ፈጠራ ዘርፍ እንደ አስተዳደር ትኩረት የተሰጠው ዘርፍ ነው ብለዋል።
በዘርፉ ከጊዚያዊ የስራ እድል ፈጠራ በዘለለ መደበኛ የስራ እድል በመፍጠር ዜጎች ስራን አግኝተው ምቹ ህይወት እንዲመሩ ስራ እድል ፈጠራው ክህሎት መር እንዲሆን እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመዋል።
በድሬደዋ በየአመቱ ከ30 ሺ በላይ የስራ እድል ፈላጊ እንደሚኖር የገለፁት አቶ ሮቤል ከመንግስት ባለፈ የግሉ ዘርፍ እንዲሁም በቤተሰብ ደረጃ ስራን የመፍጠር ዝንባሌ በማሳደግ የስራ አጡን ቁጥር ትርጉም ባለው መልኩ መቀነስ የሚያስችሉ አስራርሮች ተግባራዊ እንደሚደረጉ አቶ ሮቤል ገልፀዋል።
54 አባላት ያሉት ይህ ምክር ቤት በአመት ሁለት ጊዜ በመሰብሰብ ለዜጎች ሊፈጠሩ የሚችሉ የስራ እድሎችን አሟጦ ከመጠቀም እንፃር የተሰሩ ስራዎችን የሚገመግም ሲሆን በ2016 ዓ.ም ባለፉት 11 ወራት የተከናወኑ ስራዎችን በጥልቅ በመፈተሽ ገምግሟል።
በዘርፈ የመንግስት አስፈፃሚ አካላትን መካከል የተቀናጀ አሰራር እንዲፈጠር ማስችል ፣የሚወጡ ፓሊሲና ስትራቴጂ ስራ እድልን ያማከለ እንዲሆኑ ማድረግ፣
የስራ ባህል ተቀይሮ የስራ ፈጣሪነት እንዲሁም የቁጠባ ባህል እንዲዳብር ማስቻል ስራ መከናወኑን በጉባኤው ተመላክቷል።
በ2016ዓም በ11 ወራት በስራ እድል ፈጠራ 13743 ዜጎች ስራ ለመፍጠር ታቅዶ ለ12015 ለመፍጠር መቻሉ የከተማ ግብርና ፣ የኢንዱስትሪ በአገልግሎት/ሆቴልና ቱሪዝም/ ዘርፍ ለዜጎች ስራ የተፈጠረባቸው ዋና ዋና መስኮች መሆናቸው ታይቷል።
በተቋማት መካከል ቅንጅታዊ አሰራር ፣የማምረቻና የመሸጫ ቦታ ፣የፋይናንስ አቅርቦት ፣የቤተሰብ ንግድ ፅንሰ ሃሳብ አለማደግ፣የሚፈጠሩ የስራ እድል ፈጠራዎች ክህሎት መር አለመሆን፣የስራ ባህል ደካማ መሆን በዘርፉ እንደ ችግር የተነሱ ጉዳዮች ሲሆኑ ፣የመረጃ ቅብብሎሽን ማዘመን፣ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር፣የሚሰጡ ድጋፎቸን ማጠናከር፣ ማምረቻና የመሸጫ ቦታን ጉደይ ልዩ ትኩረት በመስጠት በዘርፉ የሚዳሰስ ለውጥ ለማምጣት መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።
©️ የድሬዳዋ መንግሥት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
#ዜና በክህሎት ላይ የተመሰረተ የስራ እድል መፍጠር እንደሚገባ ተገለፀ
#DGC ሰኔ 13/2016
የድሬደዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የ2016 የስራና ክህሎት ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ተካሂዷል።
በመድረኩ የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ የተከበሩ ከድር ጁሃር መንግስት በተለያዩ ደረጃዎች የሚኖሩ የስራ ፍላጎቶችን ብቻውን የማሟላት አቅም እንደማይኖረው ገልፀው የግል ተቋማትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በዘርፈ ተገቢውን እርብርብ በማድረግ የዜጎችን የስራ ፈጠራ ጥረት ማገዝ እንደሚገባቸው አስረድተዋል።
ምንም እንኳን ከወጣቶች የስራ ባህልና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች አንፃር እጅግ በጣም መሰራት የሚገባቸው የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎች ቢኖሩም በዛው ልክ አርአያ መሆን የሚችሉ ከዩንቨርስቲም ተመርቀውም ሆነ በተለያዩ ሁኔታዎች ስራን ፈጥረው በመንቀሳቀስ ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የስራ እድል መፍጠር የቻሉ ወጣቶች መኖራቸውን ከንቲባው አመላክተዋል።የእነዚህን ወጣቶች ተሞክሮ ወደ ሌሎች ማስፋትም እንደሚገባ ገልፀዋል።
የድሬደዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮበል ጌታቸው የስራ እድል ፈጠራ ዘርፍ እንደ አስተዳደር ትኩረት የተሰጠው ዘርፍ ነው ብለዋል።
በዘርፉ ከጊዚያዊ የስራ እድል ፈጠራ በዘለለ መደበኛ የስራ እድል በመፍጠር ዜጎች ስራን አግኝተው ምቹ ህይወት እንዲመሩ ስራ እድል ፈጠራው ክህሎት መር እንዲሆን እየተሰራ እንደሆነ ጠቁመዋል።
በድሬደዋ በየአመቱ ከ30 ሺ በላይ የስራ እድል ፈላጊ እንደሚኖር የገለፁት አቶ ሮቤል ከመንግስት ባለፈ የግሉ ዘርፍ እንዲሁም በቤተሰብ ደረጃ ስራን የመፍጠር ዝንባሌ በማሳደግ የስራ አጡን ቁጥር ትርጉም ባለው መልኩ መቀነስ የሚያስችሉ አስራርሮች ተግባራዊ እንደሚደረጉ አቶ ሮቤል ገልፀዋል።
54 አባላት ያሉት ይህ ምክር ቤት በአመት ሁለት ጊዜ በመሰብሰብ ለዜጎች ሊፈጠሩ የሚችሉ የስራ እድሎችን አሟጦ ከመጠቀም እንፃር የተሰሩ ስራዎችን የሚገመግም ሲሆን በ2016 ዓ.ም ባለፉት 11 ወራት የተከናወኑ ስራዎችን በጥልቅ በመፈተሽ ገምግሟል።
በዘርፈ የመንግስት አስፈፃሚ አካላትን መካከል የተቀናጀ አሰራር እንዲፈጠር ማስችል ፣የሚወጡ ፓሊሲና ስትራቴጂ ስራ እድልን ያማከለ እንዲሆኑ ማድረግ፣
የስራ ባህል ተቀይሮ የስራ ፈጣሪነት እንዲሁም የቁጠባ ባህል እንዲዳብር ማስቻል ስራ መከናወኑን በጉባኤው ተመላክቷል።
በ2016ዓም በ11 ወራት በስራ እድል ፈጠራ 13743 ዜጎች ስራ ለመፍጠር ታቅዶ ለ12015 ለመፍጠር መቻሉ የከተማ ግብርና ፣ የኢንዱስትሪ በአገልግሎት/ሆቴልና ቱሪዝም/ ዘርፍ ለዜጎች ስራ የተፈጠረባቸው ዋና ዋና መስኮች መሆናቸው ታይቷል።
በተቋማት መካከል ቅንጅታዊ አሰራር ፣የማምረቻና የመሸጫ ቦታ ፣የፋይናንስ አቅርቦት ፣የቤተሰብ ንግድ ፅንሰ ሃሳብ አለማደግ፣የሚፈጠሩ የስራ እድል ፈጠራዎች ክህሎት መር አለመሆን፣የስራ ባህል ደካማ መሆን በዘርፉ እንደ ችግር የተነሱ ጉዳዮች ሲሆኑ ፣የመረጃ ቅብብሎሽን ማዘመን፣ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር፣የሚሰጡ ድጋፎቸን ማጠናከር፣ ማምረቻና የመሸጫ ቦታን ጉደይ ልዩ ትኩረት በመስጠት በዘርፉ የሚዳሰስ ለውጥ ለማምጣት መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።
©️ የድሬዳዋ መንግሥት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ፑል አመራር አባላት ስለ ኤች አይ ቪ/ኤድስ ሜንስትሪምንግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከጤና ቢሮ በመጡ ባለሙያዎች አማካኝነት የአስተዳደሩን ወቅታዊ የኤች አይ ቪ/ኤድስ ሁኔታ ግንዛቤ ለመስጠት የሚረዳ እንዲሁም በተቋሙ የኤድስ ፈንድ ለማስጀመር የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለኮሌጁ ፑል አመራር አባላት አካሂዷል።
በመድረኩ ለኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭት መንስኤም ሆነ የሚያስከትለው ተፅዕኖ ዘርፈ-ብዙ ከመሆኑ አንፃር ቫይረሱን ለመከላከልና ኤድስ የሚያስከትላቸውን አሉታዊ ተጽዕኖዎች የመቀነሱና የመከላከሉ ሥራ የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ የኮሌጁ ማህበረሰብም የበኩሉን መውጣት እንደሚገባው በመድረኩ ተግልፇል::
በቀጣይም ስለ ኤድስ ፈንድ ለኮሌጁ ማህበረሰብ በቂ ግንዛቤን በመፍጠር የኤድስ ፈንድ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ መገባት እንዳለበት በመድረኩ የተገለፀ ሲሆን ከኤድስ ፈንድ ጋር ተያያዥ የሆኑ ሥራዎች በቶሎ እንዲከናወኑ የሚያስችሉ ውሳኔዎች እንዲሰጡም በውይይቱ ወቅት ተጠቁሟል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ሰኔ 12/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
“በመደበኛ ዕቅዶቻችን አቅደን ከምንፈጽመው አክለን በተጨማሪ ቁርጠኝነትና ዝግጀት በክረምት በንቅናቄ የሚተገበሩ ተግባራትን ለማከናወን በቢሮው ማህበረሰብ ዘንድ መግባባትን ፈጥረን ውጤት ለማምጣት እየሰራን እንገኛለን”
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
በክረምት በንቅናቄ የሚሰሩ ስራዎች ዕቅድ እንደ ቢሮ ተዘጋጅቶ ላይ በቢሮውና በስሩ ከሚገኙ ኮሌጆችና የወረዳ የሥራና ክህሎት ማስተባበሪያዎች ጋር ውይይት መካሄዱ ይታወቃል ይህን ተከትሎ ወደ ተግባር ለመግባት የሚያስችል በወረዳ አንድ ማዕከላት የሚሰሩ ስራዎችን ዕቅድ በዛሬው ዕለት ወደታች በማውረድ ውጤት የሚያስገኝ ተግባር ለማከናወን በሚቻልበት አግባብ ዙሪያ ውይይት ተደረገ፤
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 11/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
