1 097
Підписники
+424 години
+267 днів
+2530 день
Архів дописів
“በድሬዳዋ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ትምህርትና ስልጠና ተከታትላችሁ ያጠናቀቃችሁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በምትሰማሩበት በአመለካከት፣ በዕውቀት እና በክህሎት የታነጻችሁ ብቁ ዜጋ ሆናችሁ እንደማያችሁ ሙሉ እምነት አለኝ፤ በዚህም የሀገር እድገት ላይ የድርሻ ሚናችሁን ለተወጣችሁ አሰልጣኞች፣ የዘርፉ አመራሮች እና ባለሙያዎች በሙሉ በቢሮው ስም ምስጋናዬን እያቀረብኩ ስልጠና አጠናቃቂዎች ለተገባችሁ ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ!”
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
እንደሚታወቀው በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር ካሉት ዘርፎች አንዱ የቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ዘርፍ እንደመሆኑ የዘርፉን ግብ እና ዓላማ፤ ለማሳካት በሚደረገው ትግል ውስጥ የማይተካ ሚና ያላቸውና ባለራዕይ የሆኑ ከዘርፉ የሚፈሩ ሰልጣኝ ተማሪዎች እንደሆኑ እሙን ነው፡፡
የድሬዳዋ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጆችም ዘርፉን በአመለካከት፣ በእውቀት እና በክህሎት የበቁ ዜጎችን በማፍራት ላይ ሲገኙ በተለይ በአሁኑ ወቅት እንደ ቢሮ በተፈጠረው ተቀራርቦ የመስራትና የመደጋገፍ ሁኔታዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድነት ሰልጣኝ ተማሪዎችን በጋራ መስከረም 26/2016 ዓ.ም በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ትልቁ አዳራሽ በድምቀት የሚያስመርቁ ይሆናል፤
በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!!!
የድሬዳዋ አስተዳደር በስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ዙሪያ ከቀበሌ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በደንብ ማሻሻያ ሃሳቦች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አዘጋጀ፡፡
በመድረኩም በድሬዳዋ አስተዳደር ከብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን መድፈን እንዲያስችል ከድሬዳዋ ማይክሮ ፋይናንስ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን፤ ከተሳታፊዎችም ከብድር ተጠቃሚዎች ምልመላ አንስቶ እስከ አመላለስ ድረስ የታዩ እና እየታዩ ያሉ ችግሮችና ተግዳሮቶችን በተለይም በብድር ተጠቃሚዎች ዘንድ ያለው ለሚያገኙት ብድር ያላቸው አመለካከት እና ተከታትሎ እንዲመለስ በማድረጉ ረገድ የሚመለከታቸው አካላት ቁርጠኝነት አለመኖር የሚታዩ ክፍተቶች በደንቡ ማሻሻያ ትኩረት እንዲሰጣቸው ተነስቷል፡፡
የዳይሬክቶሬቱ ኬዝቲም የሆኑት ወ/ሮ መቅደስ ከፈለኝ እንደተናገሩት ከብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ያለውን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ወሳኝ የሆነው የአሰራር ስርዓቱ ላይ የተስተዋሉ ክፍተቶችንና ችግሮች ለመቅረፍ የሚያስችሉ ገንቢ ሃሳቦቸን ከመድረኩ መገኘቱን ጠቅሰው በቀጣይ ደንቡ ሂደቱን ጠብቆ ሊያሰራና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ የሚሻሻል እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡
የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 24/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለወጣቶች በተከታታይ ለአራት ዙር መሠረታዊ የኮምፕዩተር ስልጠና ተሰጠ፤
እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር በ2015 ዓ.ም ከ1700 በላይ ሰልጣኞች ተመዝግበው 1500 በላይ የሚሆኑት የ10 ቀን የህይወት ክህሎት ሰልጠና ወስደው 972 የሚሆኑ ወጣቶች ተግባራዊ የሥራ ላይ ልምምድን የተቀላቀሉ ሲሆን በተለያዩ በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንደስትሪዎች ላይ ስድስት ወራት የሚፈጀውን ውጤታማ ቆይታ እያደረጉ ሲገኝ ከዚሁ ጎን ለጎን የአቻ ለአቻ ውይይቶችንና መሰረታዊ የኮምፕዩተር ስልጠና መስጠት ተችሏል፡፡
በዚህ ስልጠና ላይ ተሳታፊ የሆኑ ወጣቶች በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ተጠቃሚነታቸው በአመለካከት፣ በክህሎት እንዲሁም በዕውቀት ከዚህ በፊት ከነበሩበት የተሻለ ነገሮችን የመረዳትና የማድረግ አቅም ማዳበራቸውን የተናገሩ ሲሆን በተለይ በመሠረታዊ የኮምፕዩተር ስልጠና በሁለቱ የመንግስት ኮሌጅ መምህራን የተሻለ ዕውቀት የቀሰሙበት እንደነበር ተናግረዋል፤
በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በበኩላቸው ብቃት የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለአምስት ዓመት የሚተገበር መሆኑና ከ70 ሺ በላይ ወጣቶችን ቋሚ የስራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን አስታውሰው እንደ አስተዳደር በመጀመሪያው ዓመት የፕሮግራሙ አፈጻጸም በተሰራው ስራ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነት በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተገኙ ውጤቶችን አስጠብቆና አስፍቶ በመስራት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኑነት
መስከረም 24/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የቴክኖሎጂ እሴት ሰንሰለት ትንተና እና ሰነድ ዝግጅት ላይ ያኮረ ስልጠና ከየዘርፍ መስሪያ ቤቶች ለተወጣጡ ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠት ጀመረ፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከትኩረት ዘርፍ መ/ቤት ለተውጣጡ ባለሞያዎች፤ ለኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራንና ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለተውጣጡ መምህራኖች የእሴት ሰንሰለት ትንተና ስልጠና ከመስከረም 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ መስጠት ጀመረ፡፡
በስልጠናው ማስጀመሪያ መድረክ ላይ የተገኙት በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ እደገለጹት ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ተልዕኮዎች ውስጥ አንዱ ተወዳዳሪነትን የሚያረጋግጥ አዋጭ ቴክኖሎጂ ለኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መሆኑን ጠቅሰው የምርት ወይም የአገልግሎት የአመራት ሂደት በመተንተን ክፍተቶችን በመለየት እና ለክፍተቶቹም የቴክኖሎጂዎችን መፍትሄ ለማስቀመጥ የእሴት ሰንሰለት ትንተና ማከናወን አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም የዚህ ስልጠና ዋና አላማ ከትኩረት መ/ቤት የተውጣጡ የተለያዩ ባለሞያዎች የዘርፋቸውን እሴት ሰንሰለት መስራት እንዲችሉና ዘርፉን ተወዳዳሪ በማድረግ የስራ ዕድል እንዲፈጥር ለማድረግ ታሳቢ ያደረገ ሲሆን በሚለዩት ቴክኖሎጅዎች የኢንተርፕራይዞችን፣ የተቋማትን እና የኢንዱስትሪዎችን ምርታማነትና ተወዳዳሪነት በመጨመር ለበርካታ ዜጎች የሥራ-ዕድል ለመፍጠርና እና የገቢ መጠን ለመጨመር እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 22/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
“ብቃት” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የድጋፍና ክትትል ስርዓት ግምገማ ተደረገ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት በስሩ ከምገኙ የወረዳ አንድ ማዕከላት ከሚያስተባብሩ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በአጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም በተለይ በድጋፍና ክትትል ስርዓቱ ላይ የተመላከቱ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመንቀስ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ማድረግ ተችሏል፡፡
በዚህም መድረክ ላይ ፕሮጀክቱ እንደ አስተዳደር ያስገኘውን ጠቀሜታ ከጅምሩ ሰልጣኞች በስልጠና ላይ ሆነው ከአመለካከት አንስቶ በኢንደስትሪዎች ተመድበው በሥራ ላይ ልምምድ እያደረጉ እስከሚገኝበት አሁናዊ ሁኔታ ወጣቶቹ እያሳዩ የሚገኙትን ለውጥ ቤተሰብ የመሰከረለት በሚሰሩበት ኢንደስትሪም ሰማንያ ዘጠኝ የሚሆኑት የሥራ ላይ ልምምዱ ሶስት ወር ሳይሞላው ቋሚ ቅጥር የፈጸሙ መሆኑ የሚያበረታታ መሆኑን በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሰኢድ አሊ ገልጸዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ወጣቶቹ የአቻ ለአቻ ውይይቶችንና መሰረታዊ የአይ.ሲ.ቲ ስልጠና እንዲያገኙ የተደረገ መሆኑን አስታውሰው ጥቂት የታዩ የመጠነ ማቋረጥ አዝማሚያዎችን ከኢንደስትሪዎቹ ጋር ተናቦና ተቀራርቦ ከፌደራል በተዘረጋው የድጋፍና ክትትል ስርዓት የፕሮጀክቱን ውጤታማነት ከዚህ በላይ ለማሳደግ አቅጣጫዎች ተቀምጠው ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 22/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ሼር በማድረግ መረጃውን ያድርሱ!!
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው የስራ ማስታወቂያ ላይ ከድሬዳዋ የተመዘገባችሁ ስራ ፈላጊዎች በሙሉ የፅሁፍ ፈተና ጥቅምት 03/2016 ዓ.ም ስለሚሰጥ በእለቱ ከጠዋቱ 2:30 በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ እንድትገኙ አየር መንገዱ ጥሪ አስተላልፏል።
ስም ዝርዝራችሁን ከታች አያይዣለው።
©️ via አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
በኮሌጅ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን የማሰልጠኛ መርጃ መሳሪያ (TTLM) አዘገጃጀት ላይ ስልጠና ተሰጠ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የ2016 የስልጠና ዘመን አዲስ ለሚጀመረው ለደረጃ አንድ እና ሁለት በፌደራል ደረጃ በማዕከል ለተሰሩ የሥርዓተ ትምህርቶች እና የማሰልጠኛ መርጃ መሳሪያዎች በማዘጋጀት የትምህርትና ስልጠናውን ጥራት ለማሻሻል ከሚያስችሉትና ሚያግዙት የተለያዩ ሰነዶችን በማዘጋጀትና በማሰልጠን ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
በመሆኑም ከመስከረም 05/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 (አስር) ስልጠና ፕሮግራሞች ከየዲፓርትመንት ለተውጣጡ አሰልጣኞችና አዘጋጅ አሰልጣኞች የማሰልጠኛ መርጃ መሳሪያ (TTLM) አዘገጃጀት ላይ ስልጠና በመስጠት የአሰልጣኙ መምሪያ (Teachers Guide ) ለማዘገጀት ከሁለቱም ኮሌጆች ለተውጣጡ አሰልጣኞች ይህ የአሰልጣኝ መምሪያ አዘገጃጀት ስልጠና በመስጠት እንዲያዘጋጁ ለማድረግ መቻሉን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም ገልጸዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 19/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ለኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በቴክኖሎጂ ሰነድ አዘገጃጀት ላይ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በዚህም የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራኖችን ክፍተታቸው በመለየት የፈለጉትን ቴክኖሎጂ ለመቅዳት/ኮፒ ለማድረግ እንዲችሉ የቴክኖሎጂው የአዋጭነት ትንተና ከተሰራለት በኋላ ለመቅዳትና ወደ ኢንተርፕራይዞች ለማሸጋገር ደረጃውን የጠበቀ የቴክኖሎጂ ሰነድ አዘገጃጀት ላይ ያለባቸውን ክፍተት ለመሙላት ለሰባት ተከታታይ ቀናቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ በቴክኖሎጂ ሰነድ አዘገጃጀት ላይ ለ50 አሰልጣኝ መምህራኖች በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አዳራሽ መስጠት ተችሏል፡፡
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ የተገኙት የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በዋነኛነት የማህበረሰቡን ችግር ሊፈቱ የሚችሉ የተለያዩ ከውጪ የሚገቡ ቴክኖሎጂዎችን አስመስሎ በመስራትና መቶ ፐርሰንት በመቅዳት በአስተዳደሩ ለሚገኙ ለጥቃቅን አነስተኛና በመካከለኛ ደረጃ ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች/አንቀሳቃሾች ምርጥ ቴክኖሎጂዎችን በመቅዳትና በማቅረብ የቴክኖሎጂ አቅማቸውን በመገንባት ሀብት ንብረት እንዲያፈሩ ማድረግ ላይ በማተኮር በተለይ በ2016 ዓ.ም በኮሌጆች የተሰሩ ቴክኖሎጂዎች ማሳያ ማዕከላትን ማዘጋጀት ላይ ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 18/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሴት ሠራተኞች ከቢሮው ሠራተኞች ያሰባሰቡትን ጥሬ ገንዘብና የተለያዩ አልባሳት ለአሰገደች የአረጋውያን መጦሪያ ማዕከል በአካል በመገኘት ድጋፍ አደረጉ፤
ለዚህም ድጋፍ በማዕከሉ የተገኙት አመራሮችና ሠራተኞች የማዕከሉን ሁኔታ ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ማዕከሉ እየሰጠ የሚገኘውን አገልግሎት አድንቀው ከተደረገው ድጋፍ በተጨማሪ በቀጣይ የቢሮውን እና በስሩ የሚገኙ ኮሌጆችን አቅም በመጠቀም የተለያዩ ሞያዊና የአይነት ድጋፎችን እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል፡፡
አሰገደች የአረጋውያን መጦሪያ በድሬዳዋ ከተማ በ1980 ዎቹ የተቋቋመ የበጎ አድራጎት ድርጅት ነው። ድርጅቱ የተጠነሰሰው በወ/ሮ አሰገደች መኖሪያ ቤት ሲሆን ይህ ጅማሮ የመንግስት እና የበጎ አድራጊ ግለሰቦች ጥረት ታክሎበት አሁን ያለበትን የአገልግሎት ማዕከል መመስረት ችሏል፤ በአሁኑ ወቅት ማዕከሉ ውስጥ ለሚገኙ አዛውንቶች የምግብ፣ የመጠልያ፣ የጤና፣ እና የንፅህና ግልጋሎቶች ይሰጣል። ከዚህ በተጨማሪም ከመጠለያ ውጪ ላሉ በርካታ አዛውንቶች የገንዘብ ድጋፍ ይደረጋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 16/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
በመድረኩም ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ለተወጣጡ አሠሪና ሠራተኞች በሁለትዮሽ ማህበራዊ ምክክር ዝርጋታ እና በሠሰሪና ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1156 ላይ ማብራሪያና ተሳታፊዎች በስራ አለም የሚገጥማቸውን ተጨባጭ ገጠመኞች በመጥቀስ ጥያቄዎችን አንስተው ምላሽና ውይይት አድርገዋል።
የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መሐመድ ኢብራሂም አሠሪና ሠራተኛው አዋጁን በመረዳት ግንዛቤውን ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የስራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸው እንደሚሆን ተናግረዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 15/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተለያዩ የስራ ክፍሎች በISO 21001/2018 (EOMS) manual የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናና ስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዛሬው እለት አከናወነ፡፡
በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና ስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን እና የ ISO ትግበራ ቡድን ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ እንዳሉት ከዚህ ቀደም በ ISO 21001/2018 (EOMS) manual ላይና ትግበራ ሂደት ላይ ከተለያዩ የክፍል ተጠሪዎችና የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ጋር ተስማምተንና ተፈራርመን ወደ ስራ መግባታችን የሚታወስ ነው፡፡ዛሬ ያደረግነው ስራ ማስጀመሪያና ከመመሪያዎች እንዲሁም መስሪያ ከሆኑ ፎርማቶች ጋር የማስተዋወቅ ስራ አንዱ የትግበራው አካል ነው፡፡ስለዚህ ሁሉም የኮሌጁ ሰራተኛ በተመደበበት ቦታ በመገኘት የተጣለበት ኃላፊነት መወጣት አለበት ብለዋል፡፡
በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ላይ የሰው ሀብት ክፍል፣የጽዳትና ጥበቃ፣ፋይናንስና ግዢ፣ዴይኬር፣ሹፌርና ፖስተኛ፣ዲን ቢሮና የለውጥ ስራዎች፣ንብረት አስተዳደር፣የሬጀስትራር ባለሞያዎች፣የላይብራሪ ባለሞያዎች፣ሴክረተሪዎች፣የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች፣የውስጥ ኦዲትር እንዲሁም የውሃና የመብራት ጥገና ባለሞያዎች ስልጠናው ላይ ተካፋይ ሆነዋል፡፡
የ ISO 21001/2018 (EOMS) ትግበራ ስራ በሁሉም ትምህርት ክፍሎችና የስራ ሂደቶች ላይ ለማስጀመር ከዚህ ቀደም በተዘጋጀ መርሃ ግብር ፊርማቸውን አኑረው ወደስራ መገባቱ የሚታወስ ነው፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መስከረም 14/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
