ch
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

前往频道在 Telegram
1 092
订阅者
+324 小时
+247
+2030
帖子存档
“ብቃት” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የድጋፍና ክትትል ስርዓት ግምገማ ተደረገ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት በስሩ ከምገኙ የወረዳ አንድ ማዕከላት ከሚያስተባብሩ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በአጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም በተለይ በድጋፍና ክትትል ስርዓቱ ላይ የተመላከቱ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመንቀስ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ማድረግ ተችሏል፡፡ በዚህም መድረክ ላይ ፕሮጀክቱ እንደ አስተዳደር ያስገኘውን ጠቀሜታ ከጅምሩ ሰልጣኞች በስልጠና ላይ ሆነው ከአመለካከት አንስቶ በኢንደስትሪዎች ተመድበው በሥራ ላይ ልምምድ እያደረጉ እስከሚገኝበት አሁናዊ ሁኔታ ወጣቶቹ እያሳዩ የሚገኙትን ለውጥ ቤተሰብ የመሰከረለት በሚሰሩበት ኢንደስትሪም ሰማንያ ዘጠኝ የሚሆኑት የሥራ ላይ ልምምዱ ሶስት ወር ሳይሞላው ቋሚ ቅጥር የፈጸሙ መሆኑ የሚያበረታታ መሆኑን በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሰኢድ አሊ ገልጸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ወጣቶቹ የአቻ ለአቻ ውይይቶችንና መሰረታዊ የአይ.ሲ.ቲ ስልጠና እንዲያገኙ የተደረገ መሆኑን አስታውሰው ጥቂት የታዩ የመጠነ ማቋረጥ አዝማሚያዎችን ከኢንደስትሪዎቹ ጋር ተናቦና ተቀራርቦ ከፌደራል በተዘረጋው የድጋፍና ክትትል ስርዓት  የፕሮጀክቱን ውጤታማነት ከዚህ በላይ ለማሳደግ አቅጣጫዎች ተቀምጠው ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

ሼር በማድረግ መረጃውን ያድርሱ!! የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው የስራ ማስታወቂያ ላይ ከድሬዳዋ የተመዘገባችሁ ስራ ፈላጊዎች በሙሉ የፅሁፍ ፈተና ጥቅምት 03/2016 ዓ.ም ስለሚሰጥ በእለቱ ከጠዋ
+3
ሼር በማድረግ መረጃውን ያድርሱ!! የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው የስራ ማስታወቂያ ላይ ከድሬዳዋ የተመዘገባችሁ ስራ ፈላጊዎች በሙሉ የፅሁፍ ፈተና ጥቅምት 03/2016 ዓ.ም ስለሚሰጥ በእለቱ ከጠዋቱ 2:30 በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ እንድትገኙ አየር መንገዱ ጥሪ አስተላልፏል። ስም ዝርዝራችሁን ከታች አያይዣለው። ©️ via አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ

በኮሌጅ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን የማሰልጠኛ መርጃ መሳሪያ (TTLM) አዘገጃጀት ላይ ስልጠና ተሰጠ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የ2016 የስልጠና ዘመን አዲስ ለሚጀመረው ለደረጃ አንድ እና ሁለት በፌደራል ደረጃ በማዕከል ለተሰሩ የሥርዓተ ትምህርቶች እና የማሰልጠኛ መርጃ መሳሪያዎች በማዘጋጀት የትምህርትና ስልጠናውን ጥራት ለማሻሻል ከሚያስችሉትና ሚያግዙት የተለያዩ ሰነዶችን በማዘጋጀትና በማሰልጠን ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ከመስከረም 05/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 (አስር) ስልጠና ፕሮግራሞች ከየዲፓርትመንት ለተውጣጡ አሰልጣኞችና አዘጋጅ አሰልጣኞች የማሰልጠኛ መርጃ መሳሪያ (TTLM) አዘገጃጀት ላይ ስልጠና በመስጠት የአሰልጣኙ መምሪያ (Teachers Guide ) ለማዘገጀት ከሁለቱም ኮሌጆች ለተውጣጡ አሰልጣኞች ይህ የአሰልጣኝ መምሪያ አዘገጃጀት ስልጠና በመስጠት እንዲያዘጋጁ ለማድረግ መቻሉን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም ገልጸዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 19/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+3

በድሬዳዋ አስተዳደር በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ለኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በቴክኖሎጂ ሰ
+7
በድሬዳዋ አስተዳደር በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ለኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በቴክኖሎጂ ሰነድ አዘገጃጀት ላይ ስልጠና ተሰጠ፡፡ በዚህም የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራኖችን ክፍተታቸው በመለየት የፈለጉትን ቴክኖሎጂ ለመቅዳት/ኮፒ ለማድረግ እንዲችሉ የቴክኖሎጂው የአዋጭነት ትንተና ከተሰራለት በኋላ ለመቅዳትና ወደ ኢንተርፕራይዞች ለማሸጋገር ደረጃውን የጠበቀ የቴክኖሎጂ ሰነድ አዘገጃጀት ላይ ያለባቸውን ክፍተት ለመሙላት ለሰባት ተከታታይ ቀናቶች  የግንዛቤ ማስጨበጫ በቴክኖሎጂ ሰነድ አዘገጃጀት ላይ ለ50 አሰልጣኝ መምህራኖች በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አዳራሽ መስጠት ተችሏል፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ የተገኙት የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በዋነኛነት የማህበረሰቡን ችግር ሊፈቱ የሚችሉ የተለያዩ ከውጪ የሚገቡ ቴክኖሎጂዎችን አስመስሎ በመስራትና መቶ ፐርሰንት በመቅዳት በአስተዳደሩ ለሚገኙ ለጥቃቅን አነስተኛና በመካከለኛ ደረጃ ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች/አንቀሳቃሾች ምርጥ ቴክኖሎጂዎችን በመቅዳትና በማቅረብ የቴክኖሎጂ አቅማቸውን በመገንባት ሀብት ንብረት እንዲያፈሩ ማድረግ ላይ በማተኮር በተለይ በ2016 ዓ.ም በኮሌጆች የተሰሩ ቴክኖሎጂዎች ማሳያ ማዕከላትን ማዘጋጀት ላይ ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 18/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሴት ሠራተኞች ከቢሮው ሠራተኞች ያሰባሰቡትን ጥሬ ገንዘብና የተለያዩ አልባሳት ለአሰገደች የአረጋውያን መጦሪያ ማዕከል በአካል በመገኘት ድጋፍ
+7
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሴት ሠራተኞች ከቢሮው ሠራተኞች ያሰባሰቡትን ጥሬ ገንዘብና የተለያዩ አልባሳት ለአሰገደች የአረጋውያን መጦሪያ ማዕከል በአካል በመገኘት ድጋፍ አደረጉ፤ ለዚህም ድጋፍ በማዕከሉ የተገኙት አመራሮችና ሠራተኞች የማዕከሉን ሁኔታ ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ማዕከሉ እየሰጠ የሚገኘውን አገልግሎት አድንቀው ከተደረገው ድጋፍ በተጨማሪ በቀጣይ የቢሮውን እና በስሩ የሚገኙ ኮሌጆችን አቅም በመጠቀም የተለያዩ ሞያዊና የአይነት ድጋፎችን እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል፡፡ አሰገደች የአረጋውያን መጦሪያ በድሬዳዋ  ከተማ በ1980 ዎቹ የተቋቋመ የበጎ አድራጎት ድርጅት ነው። ድርጅቱ የተጠነሰሰው በወ/ሮ አሰገደች መኖሪያ ቤት ሲሆን ይህ ጅማሮ የመንግስት እና የበጎ አድራጊ ግለሰቦች ጥረት ታክሎበት አሁን ያለበትን የአገልግሎት ማዕከል መመስረት ችሏል፤ በአሁኑ ወቅት ማዕከሉ ውስጥ ለሚገኙ አዛውንቶች የምግብ፣ የመጠልያ፣ የጤና፣ እና የንፅህና ግልጋሎቶች ይሰጣል። ከዚህ በተጨማሪም ከመጠለያ ውጪ ላሉ በርካታ አዛውንቶች የገንዘብ ድጋፍ ይደረጋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 16/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ። በመድረኩም ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ለተወጣጡ አሠሪ
+6
በድሬዳዋ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ። በመድረኩም ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ለተወጣጡ አሠሪና ሠራተኞች በሁለትዮሽ ማህበራዊ ምክክር ዝርጋታ እና በሠሰሪና ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1156 ላይ ማብራሪያና ተሳታፊዎች በስራ አለም የሚገጥማቸውን ተጨባጭ ገጠመኞች በመጥቀስ ጥያቄዎችን አንስተው ምላሽና ውይይት አድርገዋል። የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መሐመድ ኢብራሂም አሠሪና ሠራተኛው አዋጁን በመረዳት ግንዛቤውን ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የስራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸው እንደሚሆን ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 15/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተለያዩ የስራ ክፍሎች በISO 21001/2018 (EOMS) manual የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናና ስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዛሬው እለት አከናወነ፡፡ በግንዛቤ ማስጨ
+8
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተለያዩ የስራ ክፍሎች በISO 21001/2018 (EOMS) manual የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናና ስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዛሬው እለት አከናወነ፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና ስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን እና የ ISO ትግበራ ቡድን ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ እንዳሉት ከዚህ ቀደም በ ISO 21001/2018 (EOMS) manual ላይና ትግበራ ሂደት ላይ ከተለያዩ የክፍል ተጠሪዎችና የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ጋር ተስማምተንና ተፈራርመን ወደ ስራ መግባታችን የሚታወስ ነው፡፡ዛሬ ያደረግነው ስራ ማስጀመሪያና ከመመሪያዎች እንዲሁም መስሪያ ከሆኑ ፎርማቶች ጋር የማስተዋወቅ ስራ አንዱ የትግበራው አካል ነው፡፡ስለዚህ ሁሉም የኮሌጁ ሰራተኛ በተመደበበት ቦታ በመገኘት የተጣለበት ኃላፊነት መወጣት አለበት ብለዋል፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ላይ የሰው ሀብት ክፍል፣የጽዳትና ጥበቃ፣ፋይናንስና ግዢ፣ዴይኬር፣ሹፌርና ፖስተኛ፣ዲን ቢሮና የለውጥ ስራዎች፣ንብረት አስተዳደር፣የሬጀስትራር ባለሞያዎች፣የላይብራሪ ባለሞያዎች፣ሴክረተሪዎች፣የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች፣የውስጥ ኦዲትር እንዲሁም የውሃና የመብራት ጥገና ባለሞያዎች ስልጠናው ላይ ተካፋይ ሆነዋል፡፡ የ ISO 21001/2018 (EOMS) ትግበራ ስራ በሁሉም ትምህርት ክፍሎችና የስራ ሂደቶች ላይ ለማስጀመር ከዚህ ቀደም በተዘጋጀ መርሃ ግብር ፊርማቸውን አኑረው ወደስራ መገባቱ የሚታወስ ነው፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መስከረም 14/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ ክህሎት ለሽግግርና ቀጠናዊ ትስስር ፕሮጀክት(EASTRIP) በራስ አቅም ያስጠናው የምሩቃን እና የስራ ገበያና ፍላጎት የጥናት ውጤት ሪፖርት የቀረበበት መድረክ ተካሄደ፡፡ ይህ የዳሰሳ ጥናት እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር ያለብንን ክፍተት የለየና በቀጣይ በምን የስልጠና መስኮች ስልጠናዎችን መስጠት እንደሚኖርብን ያመላከተ የዳሰሳ ጥናት ነው ያሉት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ ኃላፊዋ በንግግራቸው ወቅት ወጣቶችን አሰልጥኖ ማስመረቅ ብቻ ሳይሆን በሰለጠኑበት ሙያ ለሀገር እድገት አስተዋጽኦ ማበርከት የሚችሉ ሰልጣኞችን ወደ ገበያው ማስገባትና ክትትል ማድረግ እንዲሁም የድሬዳዋና የአካባቢውን ጸጋ ተጠቅመው ራሳቸውንና አካባቢያቸውን መለወጥ የሚችሉ ሰልጣኞችን ማፍራት ላይ ትኩረት አድርገው ኮሌጆች መንቀሳቀስ እንዳለባቸው ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ደግሞ የድሬደዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስራዎችን እየሰራበት ያለው መንገድ የሚበረታታና ለሌሎች አቻ ኮሌጆች እንደ ተሞክሮ የሚቀርብ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል ፡፡ በተጨማሪም በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ዲን የሆኑት አቶ ሳሊም ኡስማን እንዳሉት ይህ የዳሰሳ ጥናት በተከታታይ ሁለት አመታት የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተመራቂዎች ገበያው ከሚፈልገው የሰው ሀይል ፍላጎት አንጻር ያሉበትን ሁኔታ ላይ ትኩረት ያደረገ እንደነበረና የጥናቱ ውጤትም ኮሌጁ ከተቋቋመበት አላማ አንጻር ሲታይ አላማውን ለማሳካት ምን አይነት ስራዎችን በቀጣይ መስራት እንዳለበት የጠቆመ የዳሰሳ ጥናት ነው ያሉ ሲሆን በቀጣይ በዳሳ ጥናቱ የተገኙ ግብአቶችን እቅድ ውስጥ በማካተት የሚሰራ ይሆናል በማለት በመጨረሻም ለዚህ ጥናት መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላቶች ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ጥናቱን አስመልክቶ የEASTRIP ፕሮጀክት የM & E Specialist የሆኑት አቶ መሳይ ጥላሁን እንደገለጹት ከዚህ ቀደም በICOS Consulting PLC ተመሳሳይ ጥናት መደረጉን አስታውሰው አሁን የተጠናው ጥናት በራስ አቅም ማስጠናት መቻላችን በወጪ ረገድ ዋጋ ቆጣቢ የሆነና ከመረጃ ጥራት ጋር በትኩረት መስራት እንድንችል ያደረገ ሲሆን በቀጣይ ደግሞ ቴክኒክና ሞያ ኮሌጃችን ከኢንዱስትሪው ጋር የማስተሳሰር ስራ እንዲሁም ቀሪ ጥናቶችን ደግሞ ሁሉን አሳታፊ አድርገን የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በመድረኩ ላይም የሥራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ዳይሬክትር ፣ የንግድና ኢንዱስትሪ ም/ኃላፊ፤የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊዎችና ተወካዮች፤የሁለቱም ኮሌጆች ዲኖችና ም/ዲኖች እንዲሁም የኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት፤የኢንዱስትሪ አማካሪ ቦርድ አባላቶች እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች ተካፋይ ሆነዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መስከረም 12/2016 ዓ.ም ሀረር

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በቢሮው ለሚገኙ ሠራተኞች ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለልጆቻቸው መማሪያ የሚሆን የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ:: ቢሮው ከዚህ
+5
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በቢሮው ለሚገኙ ሠራተኞች ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለልጆቻቸው መማሪያ የሚሆን የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ:: ቢሮው ከዚህ ቀደም ሠራተኛውን ሊደጉሙ የሚችሉ የፍጆታ ግብዓቶችን በቅናሽ በማቅረብ ያለውን የኑሮ ውድነት ጫና ለመቀነስ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱ የሚታወስ ነው።

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ከኔዘርላንድ የልማት ድርጅት (SNV) ጋር በመተባበር እድሜያቸው ከ 18 እሰክ 35 የሆኑ ለተደራጁ ዘጠኝ ኢንተርፕራይዞች የኢንተርፕሩነርሺፕና የህይወት ክህሎት ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ ለእያንዳንዳቸው ግምቱ ሃምሳ ሺህ ብር የሚገመት ለእርባታ የሚሆኑ የዶሮዎች ድጋፍ ተደረገ፤ የድጋፍ ርክክብ ስነ ስርዓቱ የቢሮው ተወካይ እና የቀበሌ የአንድ ማዕከላት እንዲሁም የእንስሳት ጤና እና ሀብት ልማት ተወካይ በተገኙበት የተደረገ ሲሆን ድጋፉን በተመለከተ ንግግር የደረጉት የSNV ድርጅት ተወካይ አቶ ኃይለየሱስ ለምለም የተደራጁት ወጣቶች የሥራ እድል ለራሳቸውና ለሌሎች እንደሚፈጥሩ እንዲሁም ለሌሎች ምሳሌ በመሆን ዶሮ እርባታ ላይ በአነስተኛ አቅምና እውቀት አሁን በመጀመር በቀጣይ አስፍተውና አጠናክረው እንዲቀጥሉ ከባለሙያዎች ጋር ገለጻ አድርገዋል፤ አክለውም ድርጅታቸው ከቢሮው ጋር በመተባበር ሥራ የሌላቸው ሴቶችና ወጣቶችን በገጠርና በከተማ በማደራጀት በተለያዩ ርዕስ ጉዳዮዎች በተለይ በኢንተርፕሩነርሺፕና በህይወት ክህሎት ስልጠናዎችን በመስጠት እና ተደራጅተው በሚሰማሩበት ሥራ ዘረፍ ላይ አሰፈላጊው ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ጠቅሰው የዛሬውን ድጋፍ ጨምሮ በአጠቃላይ ለሃያ ስድስት በከተማና በገጠር ለተደራጁ ወጣቶች ከአንድ ነጥብ ሶስት ሚሊየን ብር የሚገመት ድጋፍ መደረጉንና በቀጣይም በተመሳሳይ ኢንተርፕራይዞቹን በቅርበት በመከታተል ድጋፍ የሚያደርጉ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡ በመቀጠል ድጋፍ የተደረገላቸው ተጠቃሚዎች እንደተናሩት በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮና በSNV የጋራ ትብብር ለተሰጣቸው  ስልጠና እና የአይነት ድጋፍ በማመስገን ለበለጠ ሥራ ለመሥራት እንደሚያነሳሳቸው ተናግረው ከዚህ በፊት በዚሁ የዶሮ እርባታ ላይ በአነስተኛ አቅምና እውቀት የጀመሩትን  አስፍተውና አጠናክረው ለመስራትም መነሳሳት የፈጠረላቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡  የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 10/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በዛሬው ዕለት 105 ደርዘን ደብተር ባለ50 ፍሬ የሚይዝ 6 ፓኬት ብዕር እንዲሁም ባለ12 ፍሬ የሚይዝ 12 ፓኬት ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ተማሪ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በዛሬው ዕለት 105 ደርዘን ደብተር ባለ50 ፍሬ የሚይዝ 6 ፓኬት ብዕር እንዲሁም ባለ12 ፍሬ የሚይዝ 12 ፓኬት ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ተማሪዎች ልጆች የሚሆን የመማሪያ መርጃ ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ፡፡ ይህንንም ድጋፍ የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወ/ፈጡም ሙስጠፋ ለአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አቡበከር አዶሽ ያስረከቡ ሲሆን በቀጣይም መሰል ድጋፍ ማድረግ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 9/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በዘጠኙም የከተማ ወረዳ አስተዳደር ስር ከሚገኙ አስራ አንድ የወረዳ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች ጋር  የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡ በዚህም የውይይት መድረክ ላይ ማዕከላቱን የሚመለከቱ ስራዎችን በመቁረስ ለአስራ አንዱም የቀበሌ አንድ ማዕከላት ማውረድ የተቻለ ሲሆን በቀጣይም በመናበብ የአስተዳደሩን ነዋሪ ተደራሽና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎችን በተጨባጭ ለመስራት አስፈላጊውን ምችችት እንደሚደረግና የሚታይ ውጤትና ለውጥ ለማምጣት ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሰኢድ አሊ ገልጸዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ ከታቀደው በዋናነት ከተመላከተው፡-   14,300 ስራ ፈላጊዎች ይመዘገባሉ፡፡   14,456 ቋሚ የስራ ዕድል ይፈጠራል፡፡   3,554 ጊዜያዊ የስራ ዕድል ይፈጠራል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 8/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6