uk
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Відкрити в Telegram

Показати більше
1 065
Підписники
-124 години
-47 днів
+530 день
Архів дописів
የትምህርት ክፍል ተጠሪዎችን በማብቃት የኮሌጁን የልህቀት ማእከልነትን ጉዞ እንዲያፋጥኑ በተለያዩ ስልጠናዎች የማብቃቱን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ኮሌጁ አስታወቀ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለትምህርት ክፍል ተጠሪዎችና አስተባባሪዎች በ leadership, change management, innovation management, and strategic management ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና በዛሬው እለት ሰጠ፡፡ በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርት ክፍል ተጠሪዎችንና አስተባባሪዎችን ውጤታማ የለውጥ መሪዎች እንዲሆኑና የአሰልጣኞችን አፈጻጸም ለማሻሻል እንዲሁም አዳዲስ የቴክኖሎጂ አሰራሮችን ከተቋሙ አሰራር ጋር ማዋሃድ እንዲቻል በተለያዩ ስልጠናዎች የማብቃት ስራ ይሰራል ያሉት የኮሌጁ ም/ዲንና የው/ተ/ት/ስልጠና ኃላፊ የሆኑት አቶ ቢቂላ ታደሰ ሲሆኑ አያይዘውም ኮሌጃችን የምስራቅ አፍሪካ የቴክኒክና ሙያ የልህቀት ማእከል እንደ መሆኑ መጠን በትምህርትና ስልጠናው ላይ የሚሰሩ ስራዎች እንዲሁም በስራ ገበያው ላይ በቴክኖሎጂው አማካኝነት የሚመጡ ለውጦችን አስቀድመው የሚተነትኑና ተገቢውን ምልሽ መስጠት የሚችሉ የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች አሰልጣኞች እንዲሁም የአስተዳደር ሰራተኞች ሊኖሩን የይገባል ለዚህም ደግሞ በተገቢው መንገድ የማብቃቱን ስራ የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በዛሬው እለት በዶ/ር ሲሳይ አበራ እና አ/መር ከበደ በቀለ የተሰጠው ስልጠና በዋናነት የንድፈ ሃሳብና የቡድን ትግበራዎች የታገዘ ሲሆን በዚህም ስልጠና የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች እንዲሁም አስተባባሪዎች ውጤታማ የለውጥ መሪዎች በመሆን፣ የአሰልጣኞችን አፈጻጸም በማሻሻልና አዳዲስ የቴክኖሎጂ አሰራሮችን ከተቋሙ ስትራቴጂ ጋር በማዋሃድ የኮሌጁን የቴክኒክና ሙያ የልህቀት ማእከልነት ጉዞ የሚያፋጥኑ ስራዎችን መስራት የሚያስችል ግብአት እንዳገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 9/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መጨመርም ሆነ ተከራይን ከቤት ማስወጣት የተከለከለ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር አስታወቀ፦ 1ኛ,ለቀጣዮቹ 6 ወራት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር የተከለከለ ነው። የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መጨመርም ሆነ ተከራይን ከቤት ማስወጣት በ2016 በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ከወጡ አዋጆች አንዱ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320 መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህ አዋጅ ዋነኛ አላማው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ ከጊዜ ወደጊዜ እየናረ እና በዜጎች ኑሮ ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ ነው። ስለሆነም አሁን እየታየ ያለውን አላግባብ የሆነ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ ለመገደብ የነዋሪውን ቅሬታ ምላሽ ለመስጠት የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ በቀን 8/7/2018 ባደረገው መደበኛ ስብሰባው የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚያደርጉ አከራዮች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እና ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፋል የኑሮ ውድነቱ በመካከለኛ ምስራቅ በተፈጠረ ቀውስ በአብዛኛው አሳማኝ እና ምንም አይነት ኢኮኖሚያዊ ምክንያት የሌለው በሰው ሰራሽ ምክንያቶች የተፈጠረ ነው፡፡ የኑሮ ውድነቱም የአስተዳደሩ ነዋሪ ለከፍተኛ ችግር በመዳረጉ የተዋቀረው ግብረሃይል የተሰጠውን ሙሉ ኃላፊነት በመውሰድ ወደ ስራ የሚገባ ይሆናል። ይህም ወቅታዊ ሁኔታን በመጠቀም አላግብ ለመክበር የሚደረግ ድሬዳዋዊ አብሮነትና ጨዋነትንና መተሳሰብ ጋር በፍፁም የሚቃረን ተግባር ነው። 2ኛ/ በተለያዩ ምርቶች ሰው ሰራሽ እጥረት በመፍጠር የዋጋ ጭማሪ በሚያባብሱ ሕገወጥ ነጋዴዎች ላይ የተጀመረው ህግን የማስከበር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል። የዋጋ ጭማሪውንና ህገወጥ ንግድንየሚቆጣጠር ግብረኃይል ተቋቁሞ ወደ ስራ ገብቷል።ያለአግባብ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዋች ላይ ግብረ ሀይሉ የማያዳግም እርምጃ እንዲወስዱም ኃላፊነት ተሰቶታል። በግብይት ቦታዎች በምግብ ፍጆታዋች ላይ አላስፈላጊ የዋጋጭማሪ እንዲኖር በሚያደርጉ ዳላሎች ላይም "እርምጃ ይወሰዳል" ። 3ኛ,የውሀ አምራች ፋብሪካዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በራሳቸው ተነሳሽነት ባደረጉት ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ አስተዳደሩ በወሰደው አስተዳደራዊ እርምጃ ቀድሞ በነበረ ዋጋ መልሰው እንዲሸጡ ቢደረግም አሁንም ከድርጊታቸው ባለመቆጠብ ዋጋ ጨምረው በሚሸጡ የውሀ ፋብሪካዋች እርምጃ ይወሰዳል ። ዋጋ ጭማሪ ማድረግ ካስፈለገ አስፈላጊነቱ በጥናት ተረጋግጦና ማህበረሰቡ ያማከለ ተደርጎ ፍትሀዊ በሆነ መልኩ በህግ አግባብ ይፋ የማድረግ ስራ እንደሚሰራ አመላክተዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

photo content

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታላቁ የረመዳን ወር ፆምን ምክንያት በማድረግ የኮሌጁ ሰራተኞችና ባለድርሻ አካላት የተካፈሉበት የኢፍጣር መርሃ-ግብር በተቋሙ አካሄደ::  ይህን መሰል የኢፍጣር መርሃ-ግብር እንደ ተቋም ብሎም እንደ ሀገር አብሮነት እና እንድነት የሚፀባረቁበት ልዩ ትዕይንት መሆኑን የተገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም ይህን መደጋገፍና በህብረት መቆምን በሁሉም መስኮች ላይ ጠብቆ ማስቀጠል ይገባል ያሉ ሲሆን ይህን ልዩ የኢፍጣር መርሀ-ግብር ላዘጋጁ እንዲሁም ለተሳተፉ የኮሌጁ ማህበረሰብና አጋር አካላት ምስጋና አቅርበዋል።  በኢፍጣር መርሃ-ግብሩ ላይ የስራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች እንዲሁም የኮሌጃችን አመራርና ሰራተኞችን ጨምሮ ሰልጣኝ ተማሪዎችም የተሳተፉበት የአብሮነት መርሃ-ግብርም ነበር ። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መጋቢት 8/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ የሚጾመውን ታላቁን አብይ ፆምን ምክንያት በማድረግ ለተለያዩ ማህበረሰብ አካላቶች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በርእሰ አድባራት ወገዳማት
+7
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ የሚጾመውን ታላቁን አብይ ፆምን ምክንያት በማድረግ ለተለያዩ ማህበረሰብ አካላቶች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በርእሰ አድባራት ወገዳማት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ለእምነቱ ተከታዮች የማዕድ የማጋራት መርሃ ግብር በዛሬው እለት አከናወነ ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በካይዘን ትግበራ ዙሪያ ለኮሌጆች ስልጠና አዘጋጀ። በዚህም ስልጠናውን ከአስተዳደሩ የካይዘን ኢንስቲትዩት በመጡ ባለሙያ የተሰጠ ሲሆን በተጨማሪም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና የኢትዮ ጣልያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የካይዘን ትግበራ አፈጻጸም ተሞክሮ ቀርቧል፤ ቢሮው ለሪፎርም ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የሚታወቅ ሲሆን እነዚህም ስራዎች የሆነ ጊዜ ብቻ ተግባር አለመሆኑ በሚያሳይ መልኩ የካይዘን ትግበራውን በሁሉም የግል ኮሌጆች ላይ ተግባራዊ ማድረግ በተለየ መልኩ ቦታ ተሰጥቶታል። በመሆኑም መጀመር ብቻ ሳይሆን ማዝለቅ እንደሚገባና ጥሩ አፈጻጸም የሚያስመዘገቡ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎችና ሰራተኞችን ቢሮው እንደሚያበረታ የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 4/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች የኢፍጣር መርሀ-ግብር አካሄዱ፤      መርሃ-ግብሩ በተለይም የቢሮው እና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞችን አብሮነት እና አንድነት በመፍጠርና በማጠናከሩ ረገድ ሚናው ላቅ ያለ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ  አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረው የዛሬውን የኢፍጣር መርሀ-ግብር ላዘጋጁና ለተሳተፉ የቢሮው ማህበረሰብ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።     በዚሁ የኢፍጣር መርሃ-ግብር ላይም የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም የኮሌጅ ዲኖች አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳታፊ ሆነዋል ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 4/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

በአስተዳደሩ ከአራቱም የገጠር ክላስተሮች ለተወጣጡ ወጣቶች በኮሌጁ ሲሰጥ የቆየው የክህሎት ስልጠና ተጠናቀቀ:: ስልጠናው የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ከኮሌጁ ጋር በመተባበር ከአራቱም የገጠር ክላስተሮች ለተወጣጡ 20 ለሚሆኑ ሰልጣኞች የተሰጠ ሲሆን ስልጠናውም በህይወት ክህሎት፣ በመሰረታዊ ቢዝነስ አያያዝ እንዲሁም በካይዘን አተገባበር ላይ የተሰጠ ሲሆን ሰልጣኞችም ላለፉት ሳምንታት በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የተሰጣቸው ስልጠና በአግባቡ ተከታትለው ማጠናቀቅ ችለዋል:: በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በመልዕክታቸውም ይህ ስልጠና ወጣቶቹ ከዚህ በፊት በኮሌጁ የወሰዱትን የMarketing based sanitation concrete slab training በአግባቡ ስራ ላይ እንዲያውሉ የሚያግዛቸው ክህሎት መሆኑን ገልፀው ወጣቶች እዚህ ያገኟቸውን ክህሎቶች በየአካባቢያቸው የሚስተዋሉትን መሰረታዊ ችግሮች በመቅረፍ የሚፈጠርላቸውን የስራ እድል በአግባቡ መጠቀም ይገባቸዋልም ብለዋል:: በአስተዳደሩ የጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ዩሱፍ ሰኢድ በበኩላቸው መሰል ስልጠናዎችን ለአስተዳደሩ ወጣቶች አዘጋጅተው ወደ ኮሌጁ ሲመጡ ምንግዜም ፈጣን ምላሽ ከኮሌጁ እንደሚያገኙ አስታውሰው ለዚህ ስልጠና መሳካት ጉልህ ሚና ለተወጡ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን እና አመራሮችም ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ለወጣቶቹም የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ሰጥተዋል:: በመድረኩ ማጠቃለያም ስልጠናውን በአግባቡ ተከታትለው ላጠናቀቁ ወጣቶች የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መጋቢት 3/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በኮሌጁ የሚሰለጥኑ ሰልጣኞች በስነ ምግባር የታነጹና አገር ወዳድ እንዲሆኑ እየሰራ እንዳለ ኮሌጁ ገለጸ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሀገር ወዳድ እና በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድን ለመፍጠር ያሰበ
+4
በኮሌጁ የሚሰለጥኑ ሰልጣኞች በስነ ምግባር የታነጹና አገር ወዳድ እንዲሆኑ እየሰራ እንዳለ ኮሌጁ ገለጸ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሀገር ወዳድ እና በስነ ምግባር የታነጸ ትውልድን ለመፍጠር ያሰበ ስልጠና ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጋር በመተባበር ለሰልጣኝ ተማሪዎች እየሰጠ ይገኛል፡፡ ኮሌጁ በቀን በማታ እንዲሁም በአጫጭር ስልጠናዎች ኢንዱስትሪውን ማንቀሳቀስ የሚችሉ ስራ ፈጣሪና የቴክኖሎጂ ባለቤቶች እንዲሆኑ ከሚሰጠው ትምህርትና ስልጠና በተጨማሪ ከተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት ጋር በጋራ በመሆን ሰልጣኞችን በስነ ምግባር የማነጹ ስራ መደበኛ ስራ አድርገን እየሰራን ነው ያሉት በስልጠና ማስጀመሪያው እለት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ት/ስልጠና ኃላፊ አቶ ቢቂላ ታደሰ ሲሆኑ አያይዘውም በኮሌጁ በመደበኛነት በስልጠና ስርአቱ ከሚሰጡ ትምህርትና ስልጠናዎች በተጨማሪ ወጣቶቹ ሀገር ወዳድ እንዲሆኑ በስነ ምግባር የታነጹ እንዲሆኑ እንደ ዛሬው አይነት ስልጠናዎችን በተከታታይ የምንሰጥ ይሆናል ብለዋል፡፡ ይህ በዛሬው እለት የተጀመረው ስልጠና ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ፖሊስ አካዳሚ በመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች እየተሰጠ ሲሆን በቀጣይም በኮሌጁ እየሰለጠኑ ላሉ ሰልጣኞች በተከታታይ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 3/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የማሰልጠን ስነ-ዘዴ/ Training Methodology/ ላይ ስልጠና ላልወሰዱ ከለሁለቱ የመንግስት ኮሌጅ አሰልጣኞችና ከግል ኮሌጅ በተለያዩ ሙያዎች ለሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች ለተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ተገኝተው መልክት እንዳስተላለፉት ወቅቱ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ጊዜው በሚጠይቀው ስልጠና ማብቃት ትኩረት የተሰጠው አንደመሆኑ አሰልጣኝ መምህራኑ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ እንዲችሉ ታሳቢ ያደረገ ስልጠና መሰጠቱን አንስተው በተግባርም ውጤታማ ስራ ሰርተው ማሳየት እንደሚገባቸው ተናግረዋል፤ አቶ ታሪኩ አክለውም ከስልጠና ጥራት ጋር ተያይዞ በሰልጣኞች የምዘና ውጤት ላይ የሚስተዋለው ክፍተት ለመሙላት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት ተቀራርቦ እየተሰራ ይገኛል ያሉ ሲሆን በዋናነት ግን የአሰልጣኝ መምህሩን አቅም መገንባት የስልጠና ጥራቱን ከማሻሻል አንጻር የሚጫወተው ሚና የላቀ በመሆኑ ትኩረት መሰጠቱን  ጠቅሰው በቀጣይ በክትትልና ድጋፍ ተፈጻሚነቱ አንደሚረጋገጥ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 30/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

በድሬዳዋ የነበረኝ ቆይታ ቅኝት

photo content
+1