1 077
Підписники
+524 години
+107 днів
+530 день
Архів дописів
“ብቃት” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ኘሮጀክት ለተጠቃሚ ወጣቶች የሥራ አፈላለግ ክህሎት ስልጠና በኮሌጆች መሰጠት ጀመረ፤
በዚህም ወጣቶቹ ባለፉት ስድስት ወራት በኢንዱስትሪዎች ውስጥ የሥራ ላይ ልምምድ ማድረጋቸው ይታወቃል በቀጣይ ከሥራ ጋር ለመተሳሰር እንዲያስችላቸው ደግሞ ለተከታታይ አምስት ቀናት በሚወስዱት ስልጠና ሥራ የማፈላለግ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩ ይሆናል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 5/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
የISO 9001:2015 QMS የጥራት ሥራ አመራር ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሸላሚ::
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 ዓ.ም አዲስ ገቢ የቀንና የማታ ተማሪዎችን የእንኳን ደህና መጣችሁ መርሀግብር በኮሌጁ አዳራሽ አከናወነ፡፡
በመርሀግብሩ ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰልሀዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት በቅድሚያ በምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል የሆነውን ኮሌጃችንን ስለመረጣቸሁ በኮሌጁ ማህበረሰብ ስም አመሰግናለሁ ያሉ ሲሆን::
አያይዘውም ቴክኒክና ሙያ ማለት የወደቁ ተማሪዎች መሰብሰቢያ ሳይሆን ይልቁንም የእውቀት፣የክህሎትና የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት የሚፈልጉ ወጣቶች የሚማሩበትና በእጃቸው ሰርተው በላባቸው ሀገራቸውን መቀየር የሚፈልጉ ወጣቶች የሚሰባሰቡበት ትልቅ የትምህርትና ስልጠና ማእከል ነው ብለዋል፡፡
ኮሌጃችን የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዘመኑን የሚመጥን የትምህርትና ስልጠና ዘዴዎችን እየተጠቀመ ስልጠናዎችን እንደሚሰጥ ይታወቃል ስለዚህ በኮሌጁ ውስጥ በምትቆዩበት ወቅት ስራ ፈጣሪ ብሎም ኢንዱስትሪዎችን አንቀሳቃሽ እንድትሆኑ አድርገን ነው የምናሰለጥነው ብለዋል፡፡
አያይዘውም ድሬዳዋ ከተማች የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም ነጻ የንግድ ቀጠና እንደመሆኗ መጠን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሰለጠኑ ወጣቶችን በብዛት ይፈለጋሉ ስለዚህ በኢንዱስትሪዎች ተቀጥሮ ለመስራት እንዲሁም የራስን ስራ ፈጥሮ ለመንቀሳቀስ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ መሰልጠን ያስፈልጋል ብለዋል በማስቀጠልም በኮሌጁ ውስጥ የሚኖራችሁ ቆይታ እውቀት፣ክህሎት እንዲሁም መልካም አስተሳሰብ ያላችሁ ወጣቶች የምትሆኑበት እንዲሁም በምታገኙት እውቀትና ክህሎት ደግሞ ከተማችሁን ብሎም ሀገራችሁን የምትጠቅሙ ዜጎች እንደምትሆኑ እተማመናለሁ ያሉ ሲሆን የስልጠና ቆይታችሁም መልካም እንዲሆን መልካም መኞቴን ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል፡፡
በመርሀግብሩ ላይ በኮሌጁ ውስጥ የሚገኙ ሁሉም የትምህርት ክፍሎች ስለ ትምህርት ክፍሎቻቸው ገለጻ ያደረጉ ሲሆን ከገለጻው በኋልም በኮሌጁ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎችንና ማሰልጠኛ ወርክሾፖችን ጎብኝተዋ፡፡በቀጣዩ ቀንም የህይወት ክህሎትና የማይንድ ሴት ስልጠና እንደሚሰጥ በመድረኩ ላይ ተገልጿል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
“የግል ኮሌጆችን በኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ ላይ መሳተፍ መጀመራቸው የግሉን ዘርፍ በማህበረሰብ ዓቀፍ አገልግሎት ውስጥ ኃላፊነቱን እንዲወጣ የሚያስችል ይሆናል።”
ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ
የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ በተመላከተው መሰረት የግል የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ለኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ መስጠት እንዲያስችላቸው የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ ማዘጋጀቱ ይታወሳል።
ይህንንም ተከትሎ በዛሬው ዕለት የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ከሁለቱ የመንግስትና የግል ኮሌጆች ተወካዮች ጋር የግል ኮሌጆች ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ ማድረግ በሚችሉበት አግባብ ላይ ወደ ትግበራ እንዲገቡ የሥራ አቅጣጫ በመስጠት ውይይት ያደረጉ ሲሆን በዚህም ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ጋር በክላስተር በመክፈል በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞችን በማዳረስ ረገድ የተፈጠረውን ጫና የሚጋሩ ይሆናል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 3/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የISO 9001:2015 የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ባለቤት ሆነ።
በድሬዳዋ አስተዳደር ከሚገኙት የመንግስት ኮሌጆች አንዱ የሆነው የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የትምህርት ስርዓት የጥራት ማረጋገጫ እና የብቃት መመዘኛ ISO 9001:2015 QMS አለም አቀፍ ሰርተፊኬት አገኘ።
በሰርተፊኬት ርክክብ ስነ-ስርአቱ ላይ የተገኙት የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ እና የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሃላፊ እንዲሁም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሀርቢ ቡህ በድሬዳዋ 233 አነስተኛ ፣ 70 መካከለኛ እና 36 ከፍተኛ የኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች እንደተመዘገበ ጠቁመው የምስራቋ የኢንደስትሪ ኮሪደር እንደመሆኗ መጠን በኮሌጁ የሰለጠኑ ባለሙያዎችና ከፍተኛ የሰው ሃይል እንደሚያስፈልጋት አረጋግጠዋል።
ጥራት ያለው የሰው ሃይል ለማፍራት ፤ ጥራት ባለው የትምህርት ስርዓት እና ምዘና ማለፍ ይገባል ሲሉ በመክፈቻ ንግግራቸው ወቅት የገለፁት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲሆኑ በብቃት የሰለጠነ የሰው ሃይልን በማፍራት ለኢንደስትሪው ማበርከት ይጠበቅብናል ሲሉ ተናግረዋል።
በመድረኩ ላይ በእንግድነት የተገኙት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ነቢሃ መሀመድ እንደገለፁት በሀገር አቀፍ ደረጃ እድሉን ካገኙ 20 ትቋማት መካከል 5ቱ እራሳቸውን በጥራት ደረጃ ማሳለፍ መቻላቸውንና ከእነዚህም መካከል የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እንዱ መሆኑን አስታውቀዋል።
አክለውም ይህ የጥራት ማረጋገጫ ከምስራቅ ኢትዮጵያ የመጀመሪያው እንደሚያደርገው ገልፀው በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እና ተፈላጊ ባለሙያዎችን በማሰልጠን የስራ እድልን ከመፍጠር በዘለለ ትልልቅ ድርጅቶችንና ኩባንያዎችን የሚያንቀሳቅሱ ለማድረግ መታቀዱን ጠቁመዋል።
የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬቱን ለኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ያስረከቡት የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መዓዛ አበራ ተቋማቸው በሀገሪቱ 9 የተደራጁ የጥራት ላቦራቶሪዎችን በማደራጀት እየፈተሸ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
በግብርና ፣ በምግብ ስርዓት ፣ በኢንደስትሪ ምርት እና በትምህርት ስልጠና የብቃት ደረጃዎችን የመለካት ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልፀው በአጠቃላይም 50 ሚሊየን ዶላር በመመደብ የጥራት ደረጃዎችን ለማሻሻልና ለመፈተሽ እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በመርሃግብሩ ማጠቃለያም ለኮሌጁ የትምህርት ስርዓትና የጥራት ደረጃ አስተዋፅኦ ላበረከቱ መምህራን የእውቅና እና ማበረታቻ ሽልማት ተበርክቷል።
©️ Diretv ህዳር 3/2017
በዛሬው ዕለት በተለምዶ ኮንጎ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው ሥፍራ በሚገኘው የወጣቶች ማዕከል አዳራሽ የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን አስመልክቶ በአስተዳደሩ ባሉ የሴክተር ተቋማትና ወረዳዎች የተከናወኑ ስራዎችን የሚያስቃኝ የፎቶ አውደ-ርዕይ ተጀመረ።
በፎቶ አውደ ርዕዩ ላይ በእንግድነት ተገኝተው በይፋ ያስጀመሩት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እንደተናገሩት ብልፅግና ፓርቲ ከህዝብና ባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን መስተጋብር ከፍ በማድረግ፤ ድጋፍ ለማሰባሰብና ቅቡልነቱን ለማሳደግ በህዝባዊ ተሳትፎ ቀጣይነት ያለው ስኬቶችን እያስመዘገበ ይገኛል ብለዋል
ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር አክለውም በሥራ እድል ፈጠራ ፣ በአምራች ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ልማት ከዚያም ባለፈ የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ረገድ የተሻሉ ስኬቶችን ማስመዝገብ መቻሉን ገልፀዋል።
የፎቶ አውደ-ርዕዩ ከህዳር 2 እስከ ህዳር 6 የሚቆይ ሲሆን የብልፅግና ፓርቲ አምስተኛ አመት የምስረታን በማስመልከት ከህዳር 1 እስከ ህዳር 15 በተለያዩ ኹነቶች እና የበጎ አድራጎት ተግባራቶች እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል።
ህዳር 2/2017 ዓ.ም
ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት አምስት አመታት በፖለቲካ፣ በማህበራዊ እና በልማቱ ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ ያስመዘበበት ነው ሲሉ የድሬዳዋ አሰተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ገለጹ ።
ብልፅግና ፓርቲ "የህልም ጉልበት ለእምርታዊ ዕድገት"ለመንግስት ሠራተኛ አባላቶቹ የሠጠውን ስልጠና ሲያጠናቅቅ 5ኛ አመት ምስረታውንም አያይዞ አክብሯል።
በዚሁ ጊዜም የድሬዳዋ አሰተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በፖለቲካ፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚ ዘርፍ ተጨባጭ ለውጦች ላለፉት አምስት አመታት መገኘታቸውን ጠቅሠው በቀጣይነትም በእነዚህ አምስት አመታት የፓርቲው ጉዞ ጎልተው የወጡ ጠንካራ ጎኖችን አጠናክሮ ማስቀጠል ክፍተቶችን ደግሞ እያረሙ መሄድ ያስፈልጋል ብለዋል።
አቶ ሮቤል አክለውም በሀገራችን በቀደመው የፖለቲካ ምህዳር አንዱ ተጠቃሚ ሌላው ከዳር ተመልካች እንደነበር አስታውሰው ባለፉት አምስት አመታት ግን እንደ ብልፅግና ፖርቲ ከተመዘገቡ ስኬቶች መካከል በተግባቦት ላይ የተመሠረተ፣ ሁሉን አሳታፊና አካታች የፖለቲካ መስመር መዘርጋት መቻሉ ዋነኛው መሆኑን ገልፀዋል።
ባለፉት የብልጽግና የአምስት አመታት ጉዞ ከተመዘገቡ አብይ ድሎች ሌላኛው አደጋ ላይ ከመውደቅ ባለፈ አፈጻጸሙ የተጓተተውን ታላቁን የህዳሴ ግድብ የነበሩበትን ግዙፍ ችግሮች ቀርፎ በትክክለኛ ቁመና ስራው እንዲከናወን ማድረግ መቻሉ ነው ያሉት ደግሞ በዛው የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ናቸው።
"የህልም ጉልበት ለእምርታዊ ዕድገት" ለመንግስት ሠራተኞች ብልጽግና ፓርቲ ሲሠጥ የነበረው ስልጠና የተጠናቀቀ ሲሆን ይሄው ስልጠና ለከተማ ቀበሌ የፓርቲው አባል ሠራተኞች እየተሠጠ ይገኛል።
©️ Dire tv አማርኛ ጥቅምት 30/2017
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዘንድሮ አዲስ ለማሰልጠን የተቀበላቸውን ሰልጣኞች በአስተዳደሩ የሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎችን አስጎበኘ::
ኮሌጁ ያዘጋጀው የጉብኝት መርሃ-ግብር በእስተዳደሩ ከሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ጋር በመተባበር የተከናወነ ሲሆን በዚህም ሰልጣኝ ተማሪዎች ጉብኝታቸውን በኮካኮላ፣ናሽናል ሲሚንት፣ሬድዋ ሞተርስ እና ኒውዌቭ ፋብሪካዎች ላይ ተዘዋውረው እዲጎበኙ ማድረግ ተችሏል::
ሰልጣኝ ተማሪዎቹ በኢንዱስትሪ ጉብኝት ቆይታቸው በኮሌጁ ለመሰልጠን ከመረጡት የሙያ ዘርፍ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ፉብሪካዎች ላይ ተመድበው የጎበኙ ሲሆን ይህም በኮሌጁ ቆይታቸው ስለሚሰለጥኑት የሙያ ዘርፍ የተሻለ ግንዛቤ እንዲያገኙም አስችሏቸዋል::
ይህን መሰል መርሃ-ግብር ሰልጣኝ ተማሪዎች በኮሌጁ ስልጠናቸውን ካጠናቀቁ በኃላ ያሏቸውን የስራ እድሎች ምን እንደሚመስሉ ከውዲሁ እንዲረዱና በቴ.ሙ.ስ ዘርፍ በሚኖራቸው ቆይታ መነቃቃትን እንዲፈጥርላቸው ታስቦ የተዘጋጀ የጉብኝት መርሃ-ግብር ነው::
ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም
«የህልም ጉልበት፣ ለእምርታዊ እድገት» በሚል መሪ ቃል ለሥራና ክህሎት ቢሮ የብልፅግና ፓርቲ መሰረታዊ ድርጅት አባላት 4ተኛ ዙር የአባላት የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።
ጥቅምት 29/2017 ዓ.ም
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
