1 084
Підписники
+524 години
+107 днів
+530 день
Архів дописів
የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ እና ኤስ ኦ ኤስ ህፃናት መንደር በጋራ በመሆን ያቋቋሙት ሥራ ፈላጊ ለሆኑ ወጣቶች ዘላቂ የገቢ ማስገኛ የሆነውን ሀርላ ጋርመንት ፕሮጀክትን ለመደገፍ የሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች ፕሮጀክቱ የሚተገበርበት ቦታ በአካል በመገኘት ጎበኙ።
በዚህም ጉብኝት የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የሆኑት ወጣቶች ህይወታቸው ተቀይሮ ለሌሎችም ወጣቶች ምሳሌ የመሆን ህልማቸውን ለማሳካት ሰው ተኮር አገራዊ ተልዕኮ ይዞ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የሥራና ክህሎት ቢሮ የሚጠበቅበትን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚደረግላቸው የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 23/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ እና ኤስ ኦ ኤስ ህፃናት መንደር በጋራ በመሆን ሥራ ፈላጊ ለሆኑ ወጣቶች ዘላቂ የገቢ ማስገኛ የሆነውን ሀርላ ጋርመንት ፕሮጀክትን ለመደገፍ የሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች ፕሮጀክቱ የሚተገበርበት ቦታ በአካል በመገኘት ጎበኙ።
በዚህም ጉብኝት የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የሆኑት ወጣቶች ህይወታቸው ተቀይሮ ለሌሎችም ወጣቶች ምሳሌ የመሆን ህልማቸውን ለማሳካት ሰው ተኮር አገራዊ ተልዕኮ ይዞ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የሥራና ክህሎት ቢሮ የሚጠበቅበትን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚደረግላቸው የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 23/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ የሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ዝግጅታቸውን አጠናቀው የ2017 ዓ.ም አዲስ ገቢ ሰልጣኞችን ለመቀበል እየተጠባበቁ መሆኑን ገለጹ፤
ይህንንም የገለጹት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስርአት ላይ የድጋፍና ክትትል በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ማለትም በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ላይ በተደረገበት ወቅት ነው፡፡
የድጋፍና ክትትሉ የቢሮው ባለሙያዎች በቼክሊስት በተደገፈ ኮሌጆቹ አዲሱን የዘርፉን ፖሊሲና ስትራቴጂ ትግበራ ለማሳካት ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ በተለይ በዝግጅት ምዕራፍ ለ2017 ነባርና አዳዲስ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለማሰልጠን በዕቅድ የሰሯቸው ዋናዋና ጉዳዮች ላይ ምልከታ ማድረግ ተችሏል፡፡
በመሆኑም ኮሌጆቹ በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ዕሳቤዎች መሰረት ሰልጣኞችን ለመቀበልና ዘርፉን ተመራጭ በሆነ መልኩ ዜጎችን ለማገልገል እንዲያስችል ታሳቢ ያደረገ የድጋፍና ክትትል መደረጉ ታውቋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 22/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በ2017 የሥራ ፈላጊዎች ምዝገባን እና "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሁለተኛ ዙር ትግበራ ማጠቃለያን አስመልክቶ ለከወረዳ ዋናና ምክትል ሥራ አሥፈጻሚዎች፣ የአንድ ማዕከል እና የቢሮው ባለሙያዎች ጋር ውይይት ተካሄደ።
በዚህም መድረክ ለተሳታፊዎች ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በአስተዳደሩ የተፈጠሩ ዕድሎችን በተለይም የኢንደስትሪዎች መስፋፋት ተከትሎ የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎችን የአስተዳደሩ ሥራ ፈላጊዎች እንዲጠቀሙ የሥራ ፈላጊዎች ምዝገባው ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የቢሮ ኃላፊው አክለውም ዘንድሮ የሚከናወነው ምዝገባ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ https://lmis.gov.et መሆኑ ከዚህ በፊት የነበረውን አሰራር ያዘመነና ለሥራ ፈላጊዎች አለምዓቀፍ የሥራ አማራጮችን ያቀረበ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ሥራ ፈላጊዎች ተቀጥሮ መስራት ላይ ብቻ ሳይሆን በግልም ሆነ ተደራጅተው ሥራ እንዲፈጥሩ የሚያበረታቱ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ወደ አስተዳደሩ መምጣታቸውን አስታውሰው በዚህም የዕድሎቹ ተጠቃሚ ለመሆን ከመስከረም 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ እንዲመዘገቡ ጥሪ አድረገዋል።
በመሆኑም በአስተዳደሩ የሚገኙ የከተማ ወረዳዎች ስር የሚገኙ 19, 000 ሥራ ፈላጊ ዜጎችን መመዝገብ የታሰበ ሲሆን ተመዝጋቢ ሥራ ፈላጊዎች በአቅራቢያቸው በሚገኙ የወረዳ አንድ ማዕከላት ቀርበው ምዝገባቸውን ከማጠናቀቃቸው በፊት አስቀድመው https://lmis.gov.et በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ መመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።
በመጨረሻም "ብቃት" የወጣቶች ሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሁለተኛ ዙር ትግበራ ማጠቃለያን አስመልክቶ እስካሁን የታየው አፈጻጸም ሁሉም አካላት በቅንጅት በመስራታቸው የተገኘ ውጤት መሆኑ ከየወረዳዎቹ ከቀረቡ ሪፖርቶች የተመላከተ ሲሆን በቀጣይም የሥራ ላይ ልምምድ ያደረጉ ወጣቶች ቅጥር እንዲፈጸምላቸው ትኩረት ሰጥተው ሁሉም አካላት እንዲሰሩ መግባባት መፍጠር ተችሏል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 21/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በ2017 የሥራ ፈላጊዎች ምዝገባን እና "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሁለተኛ ዙር ትግበራ ማጠቃለያን አስመልክቶ ለከወረዳ ዋናና ምክትል ሥራ አሥፈጻሚዎች፣ የአንድ ማዕከል እና የቢሮው ባለሙያዎች ጋር ውይይት ተካሄደ።
በዚህም መድረክ ለተሳታፊዎች ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በአስተዳደሩ የተፈጠሩ ዕድሎችን በተለይም የኢንደስትሪዎች መስፋፋት ተከትሎ የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎችን የአስተዳደሩ ሥራ ፈላጊዎች እንዲጠቀሙ የሥራ ፈላጊዎች ምዝገባው ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የቢሮ ኃላፊው አክለውም ዘንድሮ የሚከናወነው ምዝገባ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ https://lmis.gov.et መሆኑ ከዚህ በፊት የነበረውን አሰራር ያዘመነና ለሥራ ፈላጊዎች አለምዓቀፍ የሥራ አማራጮችን ያቀረበ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ሥራ ፈላጊዎች ተቀጥሮ መስራት ላይ ብቻ ሳይሆን በግልም ሆነ ተደራጅተው ሥራ እንዲፈጥሩ የሚያበረታቱ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ወደ አስተዳደሩ መምጣታቸውን አስታውሰው በዚህም የዕድሎቹ ተጠቃሚ ለመሆን ከመስከረም 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ ጥሪ አድረገዋል።
በመሆኑም በአስተዳደሩ የሚገኙ የከተማ ወረዳዎች ስር የሚገኙ 19, 000 ሥራ ፈላጊ ዜጎችን መመዝገብ የታሰበ ሲሆን ተመዝጋቢ ሥራ ፈላጊዎች በአቅራቢያቸው በሚገኙ የወረዳ አንድ ማዕከላት ቀርበው ምዝገባቸውን ከማጠናቀቃቸው በፊት አስቀድመው https://lmis.gov.et በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ መመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።
በመጨረሻም "ብቃት" የወጣቶች ሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሁለተኛ ዙር ትግበራ ማጠቃለያን አስመልክቶ እስካሁን የታየው አፈጻጸም ሁሉም አካላት በቅንጅት በመስራታቸው የተገኘ ውጤት መሆኑ ከየወረዳዎቹ ከቀረቡ ሪፖርቶች የተመላከተ ሲሆን በቀጣይም የሥራ ላይ ልምምድ ያደረጉ ወጣቶች ቅጥር እንዲፈጸምላቸው ትኩረት ሰጥተው ሁሉም አካላት እንዲሰሩ መግባባት መፍጠር ተችሏል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 21/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ኢንዱስትሪ ፓርክ ለሚገኙ ከስድስት የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ለተወጣጡ ሰራተኞችና የሴፍቲ የኮሚቴ አባለት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማዘጋጀት በሙያ ደህንነትና ጤንነት ላይ ስልጠና መስጠቱ ተገለጸ።
በቢሮው የውጭ አገር ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት በዋናነት የኢንደስትሪውን ሰራተኛ ደህንነትና ጤና የማስጠበቅ ሥራዎች ትኩረት የተሰጣቸው ሲሆኑ ይህም የኢንዱስትሪውን ምርታማነት በማሳደግ የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የሚጫወተው ሚና ቀላል አለመሆኑን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ መሀመድ ኢብራሂም ተናግረዋል።
በመሆኑም በአስተዳደሩ በሚገኙ ኢንደስትሪዎች የሙያ ደህንነትና ጤንነት ኮሚቴ አንዲደራጅና እንዲቋቋም ድጋፍ በማድረግ ለተመሰረቱት ኮሚቴዎችም በቀጣይ በሚያከናውኗቸው ሥራዎች በማስገንዘብ በተለይ የሙያ ደህንነቱና ጤናው የተጠበቀ የሥራ አካባቢን በመፍጠር የኢንደስትሪውን ሰላም እና ደህንነት በማስጠበቁ በተጨባጭም ውጤት እያስገኘ ይገኛል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 21/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ለህዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት ካሳ የሚከፈልበት እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን የወጣ አዋጅ ቁ.1161/2011 ላይ ለገጠር ወረዳና ቀበሌ አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፤
በዚህም መድረክ የሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ የልማት ተነሺ የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ቋሚ የሥራ ዕድል ለራሳቸውና ለሌሎች በመፍጠር በዘላቂነት እራሳቸውን እንዴት ማቋቋም እንደሚገባቸው ገለጻ ተደርጓል፡፡
በመሆኑም የልማት ተነሺ የሚሆኑ ዜጎች ከዚህ በፊት የተከፈላቸውን ካሳ ዕሴት በማይጨምሩ ጉዳዮች ላይ በማዋል እራሳቸውንም ሆነ ሌላውን በዘላቂነት ሳይጠቅም ይባክን የነበረውን ሃብት በተቀናጀ አግባብ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠርና አሰራርን በመዘርጋት ዕሴት የሚፈጥር ይሆናል፡፡
ይህንንም ተፈጻሚ ለማድረግ በአስተዳደሩ ከንቲባ ጽ/ቤት የሚገኘው ካሳ ክፍያና መልሶ ማቋቋም ዳይሬክቶሬት ከሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት፤ ከገጠር ወረዳና ቀበሌዎች፤ ከባንኮች እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻዎችን ጋር በመሆን ይተገበራል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 16/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
'#ትንሿኢትዮጵያ' 🇪🇹 ድሬዳዋ
የኢትዮጵያ ኮደርስ ስልጠናን ለመተግበር የተከወኑ ቅድመ ዝግጅቶችን አስመልክቶ፥ የአስተዳደሩ ሥራ እና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ኮደርስ ኢኒሼቲቭ፥ በ2025 ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ የተጀመረውን ጥረት ለመሳካት እና ለአገር ሁለንተናዊ የዕድገት ጉዞ ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለው በወቅቱ ተገልጿል።
ይህን ፕሮጀክት በዚህ ወር በድሬዳዋ ለመተግበር ቅድመ ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን፥ የቴክኖሎጂ ስልጠናውን የሚወስዱ ወጣቶች ከሚያገኙት ዓለምአቀፍ የምስክር ወረቀት በተጨማሪ፥ በዘመኑ የዲጂታል ዓለም ተወዳዳሪ እና ተመራጭ ስራ ፈጣሪ ለመሆን ያስችላቸዋል።
ለ3 ዓመታት በሚዘልቀው የኢትዮጵያ ኮደርስ ስልጠና ከ32 ሺህ በላይ የአስተዳደሩ ወጣቶች ተጠቃሚ ሲሆኑ፥ በዚህ ወር በሚጀምረው የኮዲንግ ስልጠና 8 ሺህ ወጣቶች ይሳተፋሉ።
ስልጠናው ወጣቶች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪና ሥራ ፈጣሪ ሆነው ለአገር ዕድገት ሚናቸውን እንዲወጡ መሠረታዊ ክህሎት ከማስጨበጡ ባሻገር፥ በአስተዳደሩ የሚገኙ 180 አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ዲጂታላይዝ በማድረግ፥ ድሬዳዋ ስማርት ሲቲ እንድትሆን ለተጀመረው ጥረት ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
በአስተዳደራችን ለሚተገበረው የኢትዮጵያ ኮደርስ ስልጠና 20 የመማሪያ ክፍሎች እና 400 ኮምፒውተሮች የተዘጋጁ ሲሆን፥ ለፕሮጀክቱ መሳካት የድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ እና ሁለቱ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጆች እንዲሁም ሌሎችም መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የድርሻቸውን ለመወጣት ተዘጋጅተዋል።
©️ Mayor Office - ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የውጭ አገር ሥራ ስምሪትና የሠራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት በድሬዳዋ አስተዳደር ከሴክተር ተቋማትና ከወረዳ አንድ ማዕከላት ለተወጣጡ የባለድርሻ አካላት ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
በመድረኩም ለባለድርሻ አካላት በሰዎች መነገድ፣ ሰዎችን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር እና ለሥራ ወደ ውጭ አገር መላክ ወንጀል አዋጅ ቁጥር 1178/2012 እና ህጋዊ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አዋጅ ቁጥር 1246/2013 ላይ በባለሙያዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
በዚህም ተሳታፊዎች አዋጆቹን በመረዳት በሰዎች የመነገድ፣ በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር እና በህገወጥ መንገድ ለስራ ወደውጭ አገር መላክ ወንጀልን በመከላከል ረገድ ከቢሮው ጋር በቅንጅት ለመስራት መግባባት ተፈጥሯል፡፡ ፡፡
በማጠቃለያውም በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ (https://lmis.gov.et/auth) ሥራ ፈላጊው ህብረተሰብ እንዲመዘገብ እና ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ደህንነቱ የተረጋገጠ የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 16/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
