uk
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Відкрити в Telegram

Показати більше
1 092
Підписники
+324 години
+247 днів
+2030 день
Архів дописів
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በ2016 የሥራ ፈላጊዎች ቤት ለቤት የሚደረግ ምዝገባን አስመልክቶ ለቀበሌ አንድ ማዕከል፣ የመ
+6
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በ2016 የሥራ ፈላጊዎች ቤት ለቤት የሚደረግ ምዝገባን አስመልክቶ ለቀበሌ አንድ ማዕከል፣ የመንደር ኮሚቴዎችና የቢሮው ባለሙያዎች የምዝገባ ኦረንቴሽን ተሰጠ። በዚህም የኦረንቴሽን መድረክ ለተሳታፊዎች ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ  በአስተዳደሩ የተፈጠሩ የሥራ ዕድሎችን በተለይም ነጻ የንግድ ቀጠና እና የኢንደስትሪዎች መስፋፋት ዕድልን መጠቀም እንዲያስችለን በተጨባጭ ስራ ፈላጊ የሆኑትን ብቻ እንዲመዘግቡ አሳስበዋል። በተጨማሪም የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ሥራ ፈላጊዎች ተቀጥሮ መስራት ላይ ብቻ ሳይሆን በግልም ሆነ ተደራጅተው ስራ እንዲፈጥሩ የሚበረታቱ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በአስተዳደሩ የሚገኙ ዘጠኙም የከተማ ቀበሌዎች ስር የሚገኙ 14, 000 ስራ ፈላጊ ዜጎችን መመዝገብ የታሰበ ሲሆን የቤት ለቤት ምዝገባም የሚካሄድ መሆኑን ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 1/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የሀዋሳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅምንት አባላት  በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ   የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ ዲን  እና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽና ቴክኖሎጂ ሽግግር ሃለፊ ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ   በደህና መጣችሁ ፡፡ ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ብዙ ሺህ ወጣቶች የሙያና የክህሎት ባለቤት ያደረገ ኮሌጅ ነው ኮሌጁ አሁን ለደረሰበት ስኬትም የከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም የኮሌጁ ማህበረሰቦችና ባለድርሻ አካላቶች የማይተካ ሚና አላቸው ያሉ ሲሆን ኮሌጁ በቀጣ የባቡር ምህንድስና የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን ለድሬዳዋ መመስረት ምክንያት የሆነውን የባቡር ቴክኖሎጂ ለማዘመንና አሁን ያሉትን ባለሞያዎች የሚረከቡ ባለሞያዎችን እያፈራ የሚገኝ ተቋም ነው ብለዋል፡፡ የመስክ ምልከታውን መሰረት በማድረግም የልኡካን ቡድኑ ጋር በነበረው የጋራ ውይይት ወቅት  እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየወሰደ ያለው ቁርጠኝነት ለሌሎች ከተሞች አራያ መሆን የሚችል ነው ብለዋል፡፡በተጨማሪም ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ክረምቱን በቴክኒክና ሙያ በሚል መሪቃል የሰራችሁት ስራ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጁ ምን ያክል ወደ ማህበረሰቡ ለመግባት ያደረገው ጥረት እጅግ በጣም የሚያኮራ ስራ ነው ብለዋል፡፡ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለምስራቁ  የሀገራችን ክፍሎች የሚበቃ ነው ያሉ ሲሆን ይህንን አቅም በተገቢው መንገድ በመጠቀም ከተማችሁን ብሎም የምስራቁ የሀገራችንን ክፍል  ማልማት የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ በመስክ ጉብኝቱ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASTRIP ፕሮጀክት አፈጸጸም እንዲሁም የግንባታ ሂደቱን እስካሁን የደረሰበት ደረጃ  በአቶ መሀመድአወል ጠሃ  የቀረበ ሲሆን በመቀጠልም በኮሌጁ የተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ጉብኝት ተደርጓል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 1/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ 2015 በጀት አመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ሰራተኞቹ የምስጋና እውቅና ፕርግራም አካሄደ። የድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ በበጀት አመቱ የተሻለ የስራ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ሰራተኞች የምስጋና እና የእውቅና መርሀ-ግብርም የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት ተካሂዷል ። በእለቱ ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲኖች እና በመርሀ-ግብሩ ላይም ከተጋበዙ የክብር እንግዶች በ 2015 በጀት አመት የተሻለ የስራ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ሰራተኞች የምስጋና እና የእውቅና ሰርተፍኬት እንዲሁም ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ተቀብለዋል። በመጨረሻም የኮሌጁ ዲን ባስተላለፉት መልዕክት በ2015 በጀት አመት የተመዘገቡ ውጤቶች የሁሉም ሰራተኞች ጥረትና ድካም የተገኘ መሆኑን በመግለፅ ከእነዚህ ሰራተኞች ውስጥ የተሻለ አፈፃፀም ያላቸውን ለይተን እውቅና ስንሰጥ ለሌላውም መነሳሳትን እንዲፈጥር በማሰብም ጭምር መሆኑን ገልፀው በቀጣይ በጀት አመትም ተቋሙ የተሻለ የስራ አፈፃፀም እንዲያስመዘግብ ሁሉም በትጋት ሊሰራ ይገባልም ብለዋል። የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መስከረም 26/1/2016 ዓ.ም

photo content
+6

ሮማን የዉበት ማሠልጠኛ በአጫጭር ስልጠና ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን አስመረቀ፤ ወጣት ሮማን በጥቃቅንና አነስተኛ ድጋፍ በተፈጠረላት የሙያ ስልጠና ታግዛ በዋናነት ጠንክራ ሰርታ ለራሷና ለሌሎች በርካታ ሥራ ፈላጊዎች የሥራ እድል በመፍጠር የሴቶች የውበት ሳሎኗን በማስፋት የወንዶች የውበት ሳሎን ጨምራበት እድገቷ ሳይቋጥ የውበት ማሰልጠኛ ማዕከል መክፈት ችላለች፤ በዛሬው ዕለትም ለተከታታይ ስምንተኛ ጊዜ ሲሰለጥኑ የነበሩ ሰልጣኞችን ማስመረቅ የተቻለ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያየዘ በተጨማሪም ብቃት የሥራ ልምምድ ተለማማጅ ወጣቶችን በመቀበል በራሳቸው ሥራ የሚፈጥሩበት የሙያ ባለቤት ሆነዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 26/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ያሰለጠኗቸውን ከ400 በላይ ሰልጣኞች አስመረቁ **** ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ከደረጃ እስከ ዲግሪ መርሐ-ግብር ያሰለጠኗቸውን 420 ሰልጣኞች በዛሬው ዕለት በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አዳራሽ በጋራ አስመርቀዋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር ሀርቢ ቡህ ትምህርት እና ስልጠና ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ እድገት ቁልፍ መሳሪያ ነው ብለዋል። ሀገራችን ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞ በሙያዊ ክህሎት እና በስነምግባር የታነፀ ተነሳሽነት የተላበሰ እና ከአዳዲስ ቴክኖሎጂ እና አሰራሮች ጋር ተዎህዶ መስራት የሚችል አምራች ዜጋን በጥራት እና በብዛት በመፍጠር ረገድ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ እድገት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልፅዋል። በመሆኑም ተማሪዎች በሰለጠኑበት የሙያ መስክ ለሀገርና ለወገን የሚጠቅም ሥራ በመስራት በሀገሪቱ የተጀመረውን የብልፅግና ጉዞ እንዲረጋገጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱም ነው ምክትል ከንቲባ ክቡር ሀርቢ ቡህ በመልክታቸው ያሳሰቡት። የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው በአመለካከት በእውቀት እና በክህሎት እሳድገው እንዲመረቁ ላደረጉ ለኮሌጆቹ አሰልጣኝ መምህራን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። የዛሬው ምርቃት ከወትሮ ለየት የሚያደርገውም ለመጀመሪያ ጊዜ የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ተጠሪ ተቋማት ከሁለቱ ኮሌጆች ጋር በቅንጅት በመስራት እንዲሁም የደረጃ ሲ እና ቢ በአንድ ላይ ማስመረቅ መቻሉ ምርቃቱን ልዩ እንደሚያደርገው ተናግረዋል። በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ከንቲባና የንግድ ኢንደስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ፣ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፣ የድሬዳዋ ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም፣ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን፣ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እና ሌሎች የፌደራልና የአስተዳደሩ ተጋባዦች ተገኝተዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 26/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

100,000 የውጭ ሃገር የሥራ ዕድሎች በኢትዮጲያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት (E-LMIS) ! ለኢትዮጲያ ስኬት ሁሌም እንጥራለን ! በጥረታችን ስኬትም እንበረታታለን! ያለማቋረጥም እንተጋለን! ባለፉ
+1
100,000 የውጭ ሃገር የሥራ ዕድሎች በኢትዮጲያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት (E-LMIS) ! ለኢትዮጲያ ስኬት ሁሌም እንጥራለን ! በጥረታችን ስኬትም እንበረታታለን! ያለማቋረጥም እንተጋለን! ባለፉት አራት ወራቶች በሥራና ክህሎት ሚኒስትር የውጪ ሃገር የሰራተኛ ስምሪት ከመቶ ሺህ (100,000) በላይ ዜጎችን ወደ መካከለኛው ምስራቅ፣ አውሮፓ እና የተለያዩ ሃገራት የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ከሰው ንክኪ ነፃ ሆኖ በቴክኖሎጂ በመታገዝ በዲጂታል ምዝገባ፣ የዜጎቻችንን ደህንነት እና ማግኘት የሚገባቸውን ጥቅም የሚያስጠብቅ እንዲሁም ብልሹ አሰራርን መቀነስ በሚያስችል ቴክኖሎጂ አማካኝነት ዜጎች መሰማራት መቻላቸው የስኬት ጉዞ የመጀመሪያ ምዕራፍ ነው። በተቻለ መጠን ለሁሉም ዜጋ ተደራሽነትን ያረጋገጠ፣ የዜጎችን እንግልት የሚቀንስ፣ በሂደትም የሚያስቀር በውስጥ አቅም ለምቶ ተግባራዊ በተደረገው ቴክኖሎጂ በተቀላጠፈ መንገድ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆናቹ ዜጎች እንኳን ደስ ያላችሁ። በሃገር ውስጥ የስራ ስምሪት  ደግሞ በቅርብ ግዜ በሞባይል አፕሊኬሽን የታገዘ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የስራ አዋጪነት ኢንተርፕራይዝ ማደራጀትን የሚደግፍ፣ ከሰው ንክኪ ነጻ በሆነ መልኩ  የስልጠና እና ሌሎች ልዩ ልዩ ድጋፎችን መስጠት የሚያስችል የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓቱ አካል የሆነ  ስርዓት ለምቶ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል። ይሄንን መረጃ አውቃችሁ በየ አከባቢው  እየተከፈቱ ባሉ የአሻራ መስጫ ማዕከላት ቀርባቹ መረጃዎቻቹን በመሙላትና አሻራ በመስጠት የስርዓቱ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። የምዝገባ ሂደቱን ለማየት: https://youtube.com/@BequELMIS?si=vxFnJR9VdCCdbQwR ለመመዝገብ: https://lmis.gov.et

“በድሬዳዋ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ትምህርትና ስልጠና ተከታትላችሁ ያጠናቀቃችሁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በምትሰማሩበት በአመለካከት፣ በዕውቀት እና በክህሎት የታነጻችሁ ብቁ ዜጋ ሆናችሁ እንደ
+3
“በድሬዳዋ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ትምህርትና ስልጠና ተከታትላችሁ ያጠናቀቃችሁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በምትሰማሩበት በአመለካከት፣ በዕውቀት እና በክህሎት የታነጻችሁ ብቁ ዜጋ ሆናችሁ እንደማያችሁ ሙሉ እምነት አለኝ፤ በዚህም የሀገር እድገት ላይ የድርሻ ሚናችሁን ለተወጣችሁ አሰልጣኞች፣ የዘርፉ አመራሮች እና ባለሙያዎች በሙሉ በቢሮው ስም ምስጋናዬን እያቀረብኩ ስልጠና አጠናቃቂዎች ለተገባችሁ ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ!” አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ እንደሚታወቀው በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር ካሉት ዘርፎች አንዱ የቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ዘርፍ እንደመሆኑ የዘርፉን ግብ እና ዓላማ፤ ለማሳካት በሚደረገው ትግል ውስጥ የማይተካ ሚና ያላቸውና ባለራዕይ የሆኑ ከዘርፉ የሚፈሩ ሰልጣኝ ተማሪዎች እንደሆኑ እሙን ነው፡፡ የድሬዳዋ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጆችም ዘርፉን በአመለካከት፣ በእውቀት እና በክህሎት የበቁ ዜጎችን በማፍራት ላይ ሲገኙ በተለይ በአሁኑ ወቅት እንደ ቢሮ በተፈጠረው ተቀራርቦ የመስራትና የመደጋገፍ ሁኔታዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድነት ሰልጣኝ ተማሪዎችን በጋራ መስከረም 26/2016 ዓ.ም በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ትልቁ አዳራሽ በድምቀት የሚያስመርቁ ይሆናል፤ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!!!

የድሬዳዋ አስተዳደር በስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ዙሪያ ከቀበሌ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በደንብ ማሻሻያ ሃሳቦ
+7
የድሬዳዋ አስተዳደር በስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ዙሪያ ከቀበሌ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በደንብ ማሻሻያ ሃሳቦች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አዘጋጀ፡፡ በመድረኩም በድሬዳዋ አስተዳደር ከብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን መድፈን እንዲያስችል ከድሬዳዋ ማይክሮ ፋይናንስ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን፤ ከተሳታፊዎችም ከብድር ተጠቃሚዎች ምልመላ አንስቶ እስከ አመላለስ ድረስ የታዩ እና እየታዩ ያሉ ችግሮችና ተግዳሮቶችን በተለይም በብድር ተጠቃሚዎች ዘንድ ያለው ለሚያገኙት ብድር ያላቸው አመለካከት እና ተከታትሎ እንዲመለስ በማድረጉ ረገድ የሚመለከታቸው አካላት ቁርጠኝነት አለመኖር የሚታዩ ክፍተቶች በደንቡ ማሻሻያ ትኩረት እንዲሰጣቸው ተነስቷል፡፡ የዳይሬክቶሬቱ ኬዝቲም የሆኑት ወ/ሮ መቅደስ ከፈለኝ እንደተናገሩት ከብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ያለውን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ወሳኝ የሆነው የአሰራር ስርዓቱ ላይ የተስተዋሉ ክፍተቶችንና ችግሮች ለመቅረፍ የሚያስችሉ ገንቢ ሃሳቦቸን ከመድረኩ መገኘቱን ጠቅሰው በቀጣይ ደንቡ ሂደቱን ጠብቆ ሊያሰራና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ የሚሻሻል እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 24/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለወጣቶች በተከታታይ ለአራት ዙር መሠረታዊ የኮምፕዩተር ስልጠና ተሰጠ፤ እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር
+7
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለወጣቶች በተከታታይ ለአራት ዙር መሠረታዊ የኮምፕዩተር ስልጠና ተሰጠ፤ እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር በ2015 ዓ.ም ከ1700 በላይ ሰልጣኞች ተመዝግበው 1500 በላይ የሚሆኑት የ10 ቀን የህይወት ክህሎት ሰልጠና ወስደው 972 የሚሆኑ ወጣቶች ተግባራዊ የሥራ ላይ ልምምድን የተቀላቀሉ ሲሆን በተለያዩ በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንደስትሪዎች ላይ ስድስት ወራት የሚፈጀውን ውጤታማ ቆይታ እያደረጉ ሲገኝ ከዚሁ ጎን ለጎን የአቻ ለአቻ ውይይቶችንና መሰረታዊ የኮምፕዩተር ስልጠና መስጠት ተችሏል፡፡ በዚህ ስልጠና ላይ ተሳታፊ የሆኑ ወጣቶች በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ተጠቃሚነታቸው በአመለካከት፣ በክህሎት እንዲሁም በዕውቀት ከዚህ በፊት ከነበሩበት የተሻለ ነገሮችን የመረዳትና የማድረግ አቅም ማዳበራቸውን የተናገሩ ሲሆን በተለይ በመሠረታዊ የኮምፕዩተር ስልጠና በሁለቱ የመንግስት ኮሌጅ መምህራን የተሻለ ዕውቀት የቀሰሙበት እንደነበር ተናግረዋል፤ በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በበኩላቸው ብቃት የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለአምስት ዓመት የሚተገበር መሆኑና ከ70 ሺ በላይ ወጣቶችን ቋሚ የስራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን አስታውሰው እንደ አስተዳደር በመጀመሪያው ዓመት የፕሮግራሙ አፈጻጸም   በተሰራው ስራ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነት በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተገኙ ውጤቶችን አስጠብቆና አስፍቶ በመስራት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኑነት መስከረም 24/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content

photo content
+5

የቴክኖሎጂ እሴት ሰንሰለት ትንተና እና ሰነድ ዝግጅት ላይ ያኮረ ስልጠና ከየዘርፍ መስሪያ ቤቶች ለተወጣጡ ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠት ጀመረ፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከትኩረት ዘርፍ መ/ቤት ለተውጣጡ ባለሞያዎች፤ ለኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራንና ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለተውጣጡ መምህራኖች የእሴት ሰንሰለት ትንተና ስልጠና ከመስከረም 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ መስጠት ጀመረ፡፡ በስልጠናው ማስጀመሪያ መድረክ ላይ የተገኙት በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ እደገለጹት ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ተልዕኮዎች ውስጥ አንዱ ተወዳዳሪነትን የሚያረጋግጥ አዋጭ ቴክኖሎጂ ለኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መሆኑን ጠቅሰው የምርት ወይም የአገልግሎት የአመራት ሂደት በመተንተን ክፍተቶችን በመለየት እና ለክፍተቶቹም የቴክኖሎጂዎችን መፍትሄ ለማስቀመጥ የእሴት ሰንሰለት ትንተና ማከናወን አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም የዚህ ስልጠና ዋና አላማ ከትኩረት መ/ቤት የተውጣጡ የተለያዩ ባለሞያዎች የዘርፋቸውን እሴት ሰንሰለት መስራት እንዲችሉና ዘርፉን ተወዳዳሪ በማድረግ የስራ ዕድል እንዲፈጥር ለማድረግ ታሳቢ ያደረገ ሲሆን በሚለዩት ቴክኖሎጅዎች የኢንተርፕራይዞችን፣ የተቋማትን እና የኢንዱስትሪዎችን ምርታማነትና ተወዳዳሪነት በመጨመር ለበርካታ ዜጎች የሥራ-ዕድል ለመፍጠርና እና የገቢ መጠን ለመጨመር እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content

“ብቃት” የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የድጋፍና ክትትል ስርዓት ግምገማ ተደረገ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት በስሩ ከምገኙ የወረዳ አንድ ማዕከላት ከሚያስተባብሩ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በአጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም በተለይ በድጋፍና ክትትል ስርዓቱ ላይ የተመላከቱ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመንቀስ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ማድረግ ተችሏል፡፡ በዚህም መድረክ ላይ ፕሮጀክቱ እንደ አስተዳደር ያስገኘውን ጠቀሜታ ከጅምሩ ሰልጣኞች በስልጠና ላይ ሆነው ከአመለካከት አንስቶ በኢንደስትሪዎች ተመድበው በሥራ ላይ ልምምድ እያደረጉ እስከሚገኝበት አሁናዊ ሁኔታ ወጣቶቹ እያሳዩ የሚገኙትን ለውጥ ቤተሰብ የመሰከረለት በሚሰሩበት ኢንደስትሪም ሰማንያ ዘጠኝ የሚሆኑት የሥራ ላይ ልምምዱ ሶስት ወር ሳይሞላው ቋሚ ቅጥር የፈጸሙ መሆኑ የሚያበረታታ መሆኑን በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሰኢድ አሊ ገልጸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ወጣቶቹ የአቻ ለአቻ ውይይቶችንና መሰረታዊ የአይ.ሲ.ቲ ስልጠና እንዲያገኙ የተደረገ መሆኑን አስታውሰው ጥቂት የታዩ የመጠነ ማቋረጥ አዝማሚያዎችን ከኢንደስትሪዎቹ ጋር ተናቦና ተቀራርቦ ከፌደራል በተዘረጋው የድጋፍና ክትትል ስርዓት  የፕሮጀክቱን ውጤታማነት ከዚህ በላይ ለማሳደግ አቅጣጫዎች ተቀምጠው ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መስከረም 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ