1 065
Підписники
-124 години
-47 днів
+530 день
Архів дописів
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+5
ተግባር ተኮር ጥናትና ምርምርን በመጠቀም የማህበረሰቡን ችግር ለመፍታት እየሰራ እንዳለ ኮሌጁ ገለጸ፡፡
ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በመደበኛው ከሚሰጡት ስልጠና በተጨማሪ የማህበረሰቡን ችግር ለመፍታት የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ እንዲሁም ተግባር ተኮር ጥናትና ምርምርን በማድረግ በአካባቢው የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታት እንደሚኖርባቸው ይታወቃል፡፡
በዚህ መሰረት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአካባቢውን ማህበረሰብ መጥቀም የሚችሉና ችግሮችን በተገቢው መንገድ መፍታት እንዲቻል በኮሌጁ ውስጥ የሚገኙ መምህራንን ለማብቃት ያለመ የተግባር ተኮር ጥናትና ምርምር አሰራርና አተገባበር ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና በዛሬው እለት የተሰጠ ሲሆን፤
በዛሬው እለት የተሰጠው ስልጠና በዋነኛነት ለዘርፉ እንዲሁም ለማህበረሰቡ ችግር ፈቺ የሆኑ ሃሳቦችን በማፍለቅ አሰራሮችን በማሻሻል እና ወደ ተግባር እንዴት መቀየር እንደሚቻል ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በመጡት በዶ/ር ወንዲፍራው አማካኝነት በቂ ግንዘቤ መፍጠር የተቻለ ሲሆን በቀጣይም ይህንን ስልጠና እንደ ግብአት በመጠቀም ለአካበቢው እንዲሁም ለኢንዱስትሪው ግብአት መሆን የሚችሉ በሃገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን የሚያስችል ተግባራዊ ጥናትና ምርምር መስራት እንዳለባቸው በኢ/ኤ/ቴ/ሽ የቴክኖሎጂ ሽግግር ኬዝ ቲም አስተባባሪ የሆኑት አቶ ዘየደ ተክሌ አሳስበዋል፡፡
ኮሌጁ ከዚህ ቀደም በከተማ ደረጃና በአገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉ እንዲሁም ለማህበረሰቡና ለኢንዱስትሪዎች ግብአት መሆን የሚችሉ ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ስራዎችን በማቅረብ የተለያዩ እውቅናዎችን ማግኘቱ የሚታወስ ነው፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
#ዜና /በድሬዳዋ አስተዳደር በህ-ወጥ መንገድ የሚከናወኑ ስደቶችን ለማስቀራት ብሎም ከስደት ተመላሾችን አሰልጥኖ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መድረክ ተካሄደ
#DGC መጋቢት 24/2018
የዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት (IOM) ከድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ጋር እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን በድሬዳዋ ያለውን የስራ አጥ ቁጥር ለመቀነስ ያለመና በህ-ወጥ መንገድ የሚከናወኑ ስደቶችን ለማስቀራት ብሎም ከስደት ተመላሾችን አሰልጥኖ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል የፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር አካሂዷል።
በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በፕሮጀክቱ በወረዳዎች የሚገኙ የስራ ማዕከላትን ምቹ፣ ሳቢና ለዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ የማዘመንና የማጠናከር ስራዎች እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
አቶ ሮቤል አያይዘውም ማንኛውንም ስራ በቁርጠኝነት ለመስራትና ጠንካራ የስራ ባህልን ለማዳበር የሚያስችሉ የኢንተርፕርነርሺፕ እና የማይንድ ሴት ስልጠናዎች በስፋት የሚሰጡ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን በአስተዳደሩ የሚገኙትን ሁለቱን የመንግስት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆችን የማጠናከር ስራም እንደሚሰራ ጠቁመዋል።
ፕሮጀክቱ ለ3 ዓመታት የሚተገበር ሲሆን በህገ-ወጥ መልኩ ስደት የሄዱ ዜጎችን ከቤተሰብ ጋር በማቀላቀል የተለያዩ የክህሎት ስልጠናዎች እንደሚሰጡ ተመላክቷል።
በኤደን ሳሙኤል
ፎቶ:-የአብስራ ተክሉ
ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.diredawacommunication.org
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/DGCOMU
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/@Direcommunication
ቴሌግራም፦ https://t.me/DDGCAB
ትዊተር፦ https://twitter.com/DawaOffice
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
#ዜና /በድሬዳዋ አስተዳደር በህ-ወጥ መንገድ የሚከናወኑ ስደቶችን ለማስቀራት ብሎም ከስደት ተመላሾችን አሰልጥኖ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መድረክ ተካሄደ
#DGC መጋቢት 24/2018
የዓለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት (IOM) ከድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ጋር እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን በድሬዳዋ ያለውን የስራ አጥ ቁጥር ለመቀነስ ያለመና በህ-ወጥ መንገድ የሚከናወኑ ስደቶችን ለማስቀራት ብሎም ከስደት ተመላሾችን አሰልጥኖ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል የፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር አካሂዷል።
በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በፕሮጀክቱ በወረዳዎች የሚገኙ የስራ ማዕከላትን ምቹ፣ ሳቢና ለዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ የማዘመንና የማጠናከር ስራዎች እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
አቶ ሮቤል አያይዘውም ማንኛውንም ስራ በቁርጠኝነት ለመስራትና ጠንካራ የስራ ባህልን ለማዳበር የሚያስችሉ የኢንተርፕርነርሺፕ እና የማይንድ ሴት ስልጠናዎች በስፋት የሚሰጡ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን በአስተዳደሩ የሚገኙትን ሁለቱን የመንግስት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆችን የማጠናከር ስራም እንደሚሰራ ጠቁመዋል።
ፕሮጀክቱ ለ3 ዓመታት የሚተገበር ሲሆን በህገ-ወጥ መልኩ ስደት የሄዱ ዜጎችን ከቤተሰብ ጋር በማቀላቀል የተለያዩ የክህሎት ስልጠናዎች እንደሚሰጡ ተመላክቷል።
በኤደን ሳሙኤል
ፎቶ:-የአብስራ ተክሉ
ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.diredawacommunication.org
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/DGCOMU
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/@Direcommunication
ቴሌግራም፦ https://t.me/DDGCAB
ትዊተር፦ https://twitter.com/DawaOffice
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚገኙ ተማሪዎች በንድፈ ሃሳብ የሚያውቋቸውን ትምህርቶች ወደ ተግባር ተኮር እውቀት እንዲቀይሯቸው ኮሌጁ እየሰራ እንዳለ ገለጸ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሳቢያን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመጡ ተማሪዎች በቮኬሽናል ትምህርትና ስልጠና በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡
መንግስት የትምህርት ስርአቱን ለማሻሻል ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የቮኬሽናል ትምህርትና ስልጠና በሁሉም ትምህርት ቤቶች ላይ እንዲጀመርና ተማሪዎች ከታች ጀምሮ ክህሎቶችን እንዲያዳብሩ እንዲሁም በንድፈ ሃሳብ ያዩትን እውቀት በተግባር እንዲሰሩ የሚያግዝ ስርአተ ትምህርቶችን በማዘጋጀት ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል፡፡የቮኬሽናል ትምህርትና ስልጠናውን በተገቢው መንገድ መስጠት እንዲቻል ደግሞ ትልቁን ድርሻ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚወስዱ ይሆናል፡፡
በዚህ መሰረት በድሬዳዋ አስተዳደር ውስጥ የሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በጋራ እየሰሩ እንዳለ የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ የገለጹ ሲሆን አያይዘውም ከታች ጀምሮ ሁሉም ተማሪዎች ክህሎት ያላቸውና የፈጠራ ችሎታ እንዲኖራቸው ኮሌጁ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር እንዲሁም ስልጠናውን ክህሎት ባላቸው አሰልጣኞች በማሰልጠን ላይ እንገኛለን፡፡ኮሌጁ በርካታ የተግባር ክህሎትን ለማዳበር የሚያስችሉ ማሽነሪዎች አሉት መደበኛ ተቀብሎ ከሚያሰለጥናቸው ሰልጣኞች በተጨማሪ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችን በቮኬሽናል ትምህርትና ስልጠና ለማሰልጠን ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡
በኮሌጁ እየተሰጠ ያለው ስልጠና በመደበኛ ትምህርት ያገኙትን የንድፈ ሃሳብ እውቀት ወደ ተግባር ተኮር እውቀት እንዲቀይሩ አግዟቸዋል ያሉት የኮንስትራክሽን ትምህርት ክፍል ተጠሪ የሆኑት አቶ ተሾመ ሸለመ ሲሆኑ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የኮሌጁን አቅም በመረዳት ያለውን እምቅ አቅም ሊጠቀሙበት ይገባል፡፡
ስልጠናውን ለመውሰድ የመጡ ተማሪዎች በበኩላቸው የኮሌጁ መመህራኖች የንድፈ ሃሳብ እውቀታቸውን በተግባር በታገዘ ስልጠና እንድናዳብር ረድተውናል በቀጣይም ቴክኒክና ሙያን መቀላቀል እንደሚፈልጉ የገለጹ ሲሆን በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታ እጅግ እንደ ተደሰቱና ሌሎች ወጣቶች ኮሌጁን በመቀላቀል ህልማቸውን እውን እንዲያደርጉም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 23/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
የዓብይ ፆምን ምክንያት በማድረግ የማዕድ ማጋራት ተካሄደ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች እና ሰራተኞች የዓብይ ፆምን ምክንያት በማድረግ ለኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ እህት ወንድሞች በዛሬው እለት የማዕድ ማጋራት አካሂደዋል ።
የዓብይ ፆምን ምክንያት በማድረግ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ለሆኑ ወንድም እህቶቻቸው የማዕድ ማጋራት በማድረጋቸው ደስተኛ መሆናቸውን በማዕድ ማጋራት መርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው የተለያዩ እምነት ተከታዮች በጋራ የመስራት እንዲሁም ደግሞ በዓላትን በጋራ የማክበር እሴታችንን በሚያጎላ መልኩ መሰል ስራዎችን በቀጣይም አጠናክረው እንደሚያስቀጥሉ ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 22/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ለድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የባዮሜዲካል ሰልጣኝ ተማሪዎች በቀዝቃዛ ሰንሰለት የሚሠሩ የህክምና መሣሪያዎች (ColdChain equipment management) ቅድመ-ሥራ ላይ ሰልጠና ተሰጠ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴር እና ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በቀዝቃዛ ሰንሰለት የሚሠሩ የህክምና መሣሪያዎች (ColdChain equipment management) ቅድመ-ሥራ ላይ ሰልጠና ለባዮሜዲካል ሰልጣኝ ተማሪዎች ሰልጠና ሰጥቷል።
በስልጠናው ማጠናቀቂያ የተገኙት በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የፈውስ ህክምና ተሃድሶ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብዶ ሙሜ ስልጠናውን በአብሮነት ለሰልጣኞች እንዲሰጥ ያደረጉትን ጤና ሚ/ርን እና ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክን በማመስገን የባዮሜዲካል ዘርፍ ባለሞያዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ አነስተኛ በመሆናቸውና የባለሞያ እጥረት በመኖሩ ሰልጣኞች በዚህ በየጊዜው እራሱን እያዘመነ ባለው የሞያ ዘርፍ ስልጠና መውሰዳችሁ ላለው የባለሞያ እጥረት በጥቂቱም ቢሆን መፍትሄ የሚሰጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ አብዶ ጨምረውም ሰልጣኞች ከወሰዳችሁት ስልጠና ባሻገር በግላችሁም በየጊዜው ከወቅቱ ጋር እራሳችሁን በማናበብና በዘርፉ ለአዳዲስ ነገሮች በማዘጋጀት የጤና ተቋማትን የባለሞያ ችግር በመፍታት በስነ-ምግባር የተቃኘ ሙያዊ አገልግሎት መስጠት ይጠበቅባችኋል ያሉ ሲሆን ቢሮውም በሚያስፈልጓችሁ ሞያዊ እገዛዎች ከጎናችሁ ይሆናል ብለዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው የምንሰጠውን ትምህርትና ስልጠናዎችን የሚደግፍ እንደ ጤና ቢሮ ያለ ተቋም ማግኘታችን እጅግ ዕድለኝነት ነው ያሉ ሲሆን ሰልጣኞች የባዮሜዲካል ስልጠናን ከጤና ቢሮ በመጡና በቀጥታ የሞያው ባለቤት በሆኑ ስልጠናውን ማግኘት ለሰልጣኞች የበለጠ አቅም የሚሰጥ መሆኑንና ሰልጣኞች የወሰዱትን ስልጠና መሰረት በማድረግ ወደ ጤና ተቋማት በመሄድና ተከታታይነት ያለው አገልግሎት በመስጠት እራሳቸውን ሊያበቁ እንደሚገባም ተናግረዋል አቶ ታደለ።
በስልጠናው የተሳተፉ ተማሪዎች በበኩላቸው በተሰጣቸው ስልጠና ደስተኞች መሆናቸውንና በተለይ በጤና ተቋማት በተማሩበትና ጤና ቢሮ ባመቻቸላቸው ዕድል በሰለጠኑበት የሞያ ዘርፍ አገልግሎት እንዲሰጡ ለተገባላቸው ቃል በማመስገን በቀጣይም ጤና ቢሮና ኮሌጃችን መሰል ስልጠናዎችን የምናገኝበትን ሁኔታዎች እንዲያመቻቹልን እንጠይቃለን ብለዋል።
ስልጠናው ከክፍል ባሻገር በተግባር የተደገፈ ስልጠና እንደነበር የስልጠናው አስተባባሪዎች ተናግረዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
21/07/2018 ዓ.ም
ለ40 ኢንተርፕራይዞች በስራ ፈጠራና በንግድ ክህሎት ዙሪያ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።
**** ***
በስልጠናው መዝጊያ ወቅት የድሬዳዋ አስተዳደር የግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ሀላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ እንደገለጹት፣ ተሳታፊዎች ለሌሎች አርአያ እንዲሆኑ እና የተሰጣቸውን እድል በአግባቡ ተጠቅመው ራሳቸውን እንዲቀይሩ ጠይቀዋል። እንዲሁም የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የሚከናወኑ ስራዎች በተግባር ለውጥ እንደሚያመጡ ማስመስከር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚደረገው የብልጽግና ጉዞ ከሚደግፉ ዋና ጉዳዮች አንዱ ለወጣቶችና ሴቶች በርካታ የስራ እድል መፍጠር መሆኑን ጠቅሰው፣ በዚህ ሂደት ለኢንተርፕራይዞች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በተጨማሪም የሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ እንደተናገሩት፣ የተፈጠረላቸው እድል ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚሰሩ ተግባራት ግልጽ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ አቶ ኢህሳም ሁሴን በበኩላቸው፣ የተሰጠው ድጋፍ ከተረጂነት ወደ ራስ-ተቀባይነት ለመሻገር ዕድል መሆኑን ገልጸው፣ በታትነትና በትጋት በመስራት የተሻለ የኑሮ ደረጃ ላይ መድረስ እንደሚጠበቅ አሳስበዋል።
በስልጠናው ተሳታፊዎችም በሰጡት አስተያየት፣ ስልጠናው ጥሩ ግንዛቤ ያስገኘላቸው እና ወደፊት ለተሻለ ሥራ መነሳሳት የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። እንዲሁም የተማሩትን ወደ ተግባር በመተግበር ለሌሎች አርአያ ሆነው የጋራ እድገት ለማምጣት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።
''56 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ኢንተርፕራይዞች ወደ ስራ ይገባሉ''
የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ለ40 ኢንተርፕራይዞች በስራ ፈጠራና የንግድ ስራ ክህሎት ዙሪያ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ግብርና ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ሀላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ
ለሌሎች ተምሳሌት እንድትሆኑ እና የተመቻቸላችሁን እድል በአግባቡ ተጠቅማችሁ ራሳችሁን እንድትለውጡ አደራ ማለት እፈልጋለሁ ብለዋል፡፡የቆላማ አካባዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የሚሰራቸውን ስራዎችንም በተግባር የለወጠ እንደሆነ ማስመስከር አለባችሁ ብለዋል፡፡ከተረጂነት ወደ ምርታማት የብልጽግና ጉዞ ከሚደግፉ አበረታች ጉዳዮች ዋነኛው ለወጣቶች እና ሴቶች በርካታ ስራ ዕድል መፍጠር ስለሆነ በዚህ ሂደት ለኢንተርፕራይዞች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅሰዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ እንደተናገሩት አሁን የተፈጠረላችሁ እድል ወጣቶችን ተጠቃሚነትን ለማድረግ የሚሰሩ ስራዎች ማሳያ ናቸው ሲሉ ተናረዋል፡፡
አቶ ኢሳም ሁሴን የቆላማ አካባቢዎች ማጠናከርያ ፕሮግራም ስራ አስኪያጅ በበኩላቸው የተሰጠው ገንዘብ ራሳችሁን ለውጣችሁ ከተረጂነት ለመላቀቅ መንገድ የሚያቃና ሲሆን በልበ ሙሉነት ሰርቶ የተሸለ ኑሮ ደረጃ ላይ መገኘት ይጠበቅባችኋል ብለዋል፡፡
ሰልጣኞችም በሰጡት አስተያት ጥሩ ግንዛቤ ያገኙበት እና ለተሻለ ወደፊት መነቃቃትን የፈጠረልን ስልጠና ነው ብለዋል፡፡ወደ ተግባር ለውጠን ለሌሎች አርአያ ሆነን የጋራ ዕድገት ለማማጣት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+6
በሆቴልና ቱሪዝም ኢንዱስትሪው ላይ የሚገኙ ባለሙያዎችን በስልጠና በማብቃት በኢንዱስትሪው ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታት ያስፈልጋል ተባለ፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት እና በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመተባበር ከመጋቢት 14 እስከ 18/2018 ድረስ የሚቆይ ለቱሪስት አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ባለሙያዎችን በምግብ አዘገጃጀት ለማብቃት ታልሞ የተዘጋጀው ስልጠና በኮሌጁ ሆቴል ቱሪዝም ትምህርት ክፍል ማሰልጠኛ ማእከል እየተሰጠ ይገኛል፡፡
በሀገራችን ከሚገኙ ለቱሪስት ምቹ ከሆኑ ከተሞች መከካል የፍቅር ከተማ የሆነችው የድሬዳዋ ከተማ አንዷ ነች፡፡ ታድያ ይህን የቱሪስት ፍሰት በተገቢው መንገድ ለመጠቀምና ከኢንዱስትሪው ተገቢውን ገቢ ለማግኘት የሆቴል እና የቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዘመናዊና ሳቢ በሆነ መንገድ ተግባራዊ ሊሆን ይገባል፡፡ በዚህ ረገድ ቱሪስቶች በተሸለ መልኩ ከተማዋን እንዲጎበኙና ከዘርፉ የሚገኘው ገቢም እንዲጨምር በሆቴልና ቱሪዝም ኢንዱስትሪው ላይ የሚገኙ ባለሙያዎች ትልቁን ድርሻ ይወስዳሉ፡፡
ለቱሪስት አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ባለሙያዎችን በምግብ አዘገጃጀት በስልጠና በማብቃት በኢንዱስትሪው ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታት ዋና አላማው ያደረገ ስልጠና የአስተዳደሩ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ከድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመተባበር በኮሌጁ ማሰልጠና ማእከል ለከታታይ 5 ቀን የሚቆይ ተግባር ተኮር ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡በዚህም ስልጠና ባለሙያዎችን በማብቃት ኢንዱስትሪው ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች መፍታት እንደሚያስችል ለማወቅ ተችሏል፡፡
በኮሌጁ እየተሰጠ ያለው ስልጠና ከፌደራል ቱሪዝም ማሰልጠና ኢንስቲቲዩት በመጡ ካፍተኛ ባለሙያዎችና በኮሌጁ አሰልጣኞች እየተሰጠ ይገኛል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 17/7/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
በአዲሱ የኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ እንዲሁም የስትራቴጂው ውጤት በሆነው መሰረታዊ የስልጠና ሰነዶች(Basic Skill Module) ላይ በድሬዳዋ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ።
አዲሱ እሳቤ "ከስልጠና በላይ"
ችግር መፍታት
የስልጠና ተቋማት የዘርፉን ችግር የመፍታት፣ መፍትሔ የማመንጨት እና ሀብት የመፍጠር እምቅ አቅማቸውን መጠቀም የሚያስችል ነው።
ገበያ መር
የሥራ ገበያው የማይፈልገው ሙያ ማሰልጠን ሥራ አጥ ከማብዛት ያለፈ ፋይዳ አይኖረውም። ስልጠናው ገበያ መር እንዲሆን ያስገድዳል።
ቴክኖሎጂ ሽግግር
በፋብሪኬሽን ኢንጅነሪንግና ለቴክኖሎጂ ሽግግር ልዩ ትኩረት ሰጥቷል። ይህም ኢኮኖሚያዊ ነጻነትን ለመጎናጸፍ አቅም ይፈጥራል።
አራት ስትራቴጂካዊ የትኩረት መስኮች
1. ገቨርናንስን ማጎልበት
2. አግባብነትና ጥራት
3. ለሥራ ዝግጁ የሚያደርጉ ክህሎቶች
4. ምርምር እና ፈጠራ
የመሰረታዊ ክህሎት ሞጁሎች ዝርዝር
1. የሰው ልጅ የላቀ ክህሎቶች/ሰውኛ ክህሎቶች/
2. መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎቶች
3. ስነ-ምግባር እና ዜጋዊ ኃላፊነት
4. የስራ ፈጣሪነትአስተሳሰብን መለየትና ማሳደግ
5. የንግድ ስራዎችን መንደፍና ማስጀመር
በዚህም ለመድረኩ ተሳታፊዎች ከላይ የተዘረዘሩት አምስቱ ሞጁሎች በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ውስጥ የተቀረጹት ሰልጣኞች ከተግባራዊ ክህሎት ባሻገር ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን የልል ክህሎቶች(Soft Skills) እንዲያገኙ የሚያደርግ መሆኑ ተመላክቷል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 17/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
