uk
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Відкрити в Telegram

Показати більше
1 064
Підписники
-224 години
-77 днів
+130 день
Архів дописів
የመንግስት ሠራተኞች አዲሱ አዋጅ   1353/2017 ስለ ዲሲፒሊን ቅጣት ምን ይላል? For your understanding. ከባድ የዲሲፕሊን ቅጣት የሚያስከትሉ ጥፋቶች አንቀፅ 69/5   #አዋጁ እንዲህ አስቀምጦታል። +++++++++++++++++++++++++ 1.ሕጋዊ_ትእዛዝን ባለማክበር፣ በቸልተኝነት፣ በመልገም፣ ወይም ሆነ ብሎ የአሠራር ሥነ-ሥርዓት ወይም የመንግስትን ፖሊሲ ባለመከተል በሥራ ላይ በደል ማድረስ፤‌‎ 2. ጉዳዮችን ሆን ብሎ ማዘግየት ወይም ባለጉዳዮችን ማጉላላት፤ ‌‎3. ሥራ እንዳይሠራ ሆን ብሎ ማወክ ወይም ከሚያውኩት ጋር መተባበር፤‌‎ 4. በቀላል የዲስፕሊን ቅጣት እርምጃዎች ባለመታረም ያለበቂ ምክንያት በተደጋጋሚ ከሥራ መቅረት ወይም የሥራ ሰዓት አለማክበር፤ ‌‎5. በሥራ ቦታ በጠብ አጫሪነትን  መደባደብ፤ ‌‎6. በልማዳዊ ስካር ወይም በአደንዛዥ ዕፅ ሱስ በመመረዝ ሥራን መበደል፤ ‌‎7. ጉቦ መቀበል ወይም እንዲሰጠው መጠየቅ፤ ‌‎8. በሥራ ቦታ ለሕዝብ ሞራል ተቃራኒ የሆነ ድርጊት መፈጸም፤ ‌‎9. የሌብነት ወይም የእምነት ማጉደል ድርጊት መፈጸም፤‌‎ 10.የማታለል ወይም የማጭበርበር ድርጊት መፈጸም፤‌‎ 11. በመሥሪያ ቤቱ ንብረት ላይ ሆን ብሎ ወይም በቸልተኝነት ጉዳት ማድረስ፤ ‌‎12. በሥልጣን አለአግባብ መጠቀም፤‌‎ 13. በሥራ ቦታ ላይ ፆታዊ ትንኮሳ ወይም ጥቃት መፈፀም እና 14.በዚህ አንቀፅ ከተዘረዘሩት ጋር ተመሳሳይ ክብደት ያለው ሌላ የዲሲፕሊን ጉድለት መፈፀም ። ++++++++++++++++++++++++++ ሠራተኛን ከሥራ አግዶ ስለማቆየት አንቀፅ 72/1 እና 2 ++++++++++++++++++++++++++ 1.ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ ከሥራ አግዶ ማቆየት የሚቻለው (ሀ)ከተጠረጠረበት ጉዳይ ጋር አግባብነት ያላቸውን ማስረጃዎች በማበላሸት:በመደበቅ ወይም በማጥፋት ምርመራውን ያሰናክላል (ለ)በመንግስት ንብረት ላይ ተጨማሪ ጉዳት ያደርሳል (ሐ)ከተከሰሰበት ጥፋት ክብደት አንፃር የሌሎችን ሰራተኞች ሞራል የሚነካ ወይም የተገልጋዩን ሕዝብ በመሥሪያ ቤቱ ላይ ሊኖረው የሚገባውን እምነት ያዛባል (መ)ተፈፀመ የሚባለው ጥፋት ከሥራ ያስወጣል ተብሎ ሲገመት ነው 2.በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ (1) መሰረት አንድ ሠራተኛ ከሥራና ከደሞዝ ታግዶ ሊቆይ የሚችለው ከሁለት ወር ለማይበልጥ ጊዜ ይሆናል።

photo content

የመንግስት ሠራተኞች አዲሱ አዋጅ 1353/2017 ስለ ዲሲፒሊን ቅጣት ምን ይላል? For your understanding. ከባድ የዲሲፕሊን ቅጣት የሚያስከትሉ ጥፋቶች አንቀፅ 69/5 #አዋጁ እንዲህ አስቀምጦታል። +++++++++++++++++++++++++ 1.ሕጋዊ_ትእዛዝን ባለማክበር፣ በቸልተኝነት፣ በመልገም፣ ወይም ሆነ ብሎ የአሠራር ሥነ-ሥርዓት ወይም የመንግስትን ፖሊሲ ባለመከተል በሥራ ላይ በደል ማድረስ፤‌‎ 2. ጉዳዮችን ሆን ብሎ ማዘግየት ወይም ባለጉዳዮችን ማጉላላት፤ ‌‎3. ሥራ እንዳይሠራ ሆን ብሎ ማወክ ወይም ከሚያውኩት ጋር መተባበር፤‌‎ 4. በቀላል የዲስፕሊን ቅጣት እርምጃዎች ባለመታረም ያለበቂ ምክንያት በተደጋጋሚ ከሥራ መቅረት ወይም የሥራ ሰዓት አለማክበር፤ ‌‎5. በሥራ ቦታ በጠብ አጫሪነትን መደባደብ፤ ‌‎6. በልማዳዊ ስካር ወይም በአደንዛዥ ዕፅ ሱስ በመመረዝ ሥራን መበደል፤ ‌‎7. ጉቦ መቀበል ወይም እንዲሰጠው መጠየቅ፤ ‌‎8. በሥራ ቦታ ለሕዝብ ሞራል ተቃራኒ የሆነ ድርጊት መፈጸም፤ ‌‎9. የሌብነት ወይም የእምነት ማጉደል ድርጊት መፈጸም፤‌‎ 10.የማታለል ወይም የማጭበርበር ድርጊት መፈጸም፤‌‎ 11. በመሥሪያ ቤቱ ንብረት ላይ ሆን ብሎ ወይም በቸልተኝነት ጉዳት ማድረስ፤ ‌‎12. በሥልጣን አለአግባብ መጠቀም፤‌‎ 13. በሥራ ቦታ ላይ ፆታዊ ትንኮሳ ወይም ጥቃት መፈፀም እና 14.በዚህ አንቀፅ ከተዘረዘሩት ጋር ተመሳሳይ ክብደት ያለው ሌላ የዲሲፕሊን ጉድለት መፈፀም ። ++++++++++++++++++++++++++ ሠራተኛን ከሥራ አግዶ ስለማቆየት አንቀፅ 72/1 እና 2 ++++++++++++++++++++++++++ 1.ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ ከሥራ አግዶ ማቆየት የሚቻለው (ሀ)ከተጠረጠረበት ጉዳይ ጋር አግባብነት ያላቸውን ማስረጃዎች በማበላሸት:በመደበቅ ወይም በማጥፋት ምርመራውን ያሰናክላል (ለ)በመንግስት ንብረት ላይ ተጨማሪ ጉዳት ያደርሳል (ሐ)ከተከሰሰበት ጥፋት ክብደት አንፃር የሌሎችን ሰራተኞች ሞራል የሚነካ ወይም የተገልጋዩን ሕዝብ በመሥሪያ ቤቱ ላይ ሊኖረው የሚገባውን እምነት ያዛባል (መ)ተፈፀመ የሚባለው ጥፋት ከሥራ ያስወጣል ተብሎ ሲገመት ነው 2.በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ (1) መሰረት አንድ ሠራተኛ ከሥራና ከደሞዝ ታግዶ ሊቆይ የሚችለው ከሁለት ወር ለማይበልጥ ጊዜ ይሆናል።

በአስተዳደሩ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ኢንተርፕራይዝ ልማትን የሚደግፉ ፕሮጀክቶች ከቢሮውና ብድር ከሚያቀርቡ ድርጅቶች ጋር ያላቸው ቅንጅታዊ አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም ግምገማ እና የመስክ ምልከታ ተደረገ፡፡ በዚህም አቶ ተፈሪ ታደሰ የኢኔብሊንግ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ፣ አቶ ንጉሱ ጥላሁን የኢኔብሊነግ ኢትዮጵያ ሲንየር አማካሪ፣ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እንዲሁም የቢሮው ባለሙያዎች በተገኙበት የፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ቀርቦ በመስክ ምልከታ የታዩ ጉዳዮችን ጨምሮ ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ በመስክ ምልከታ አፈጻጸማቸው ከታየ ፕሮጀክቶች ጥላ ፕሮጀክት አንዱ ሲሆን ገቢያቸው አነስተኛ ለሆኑ የገጠር ወጣት ሴቶች ቀጣይነት ያለው የኑሮ መሻሻል እንዲፈጠር መነሻ ካፒታል የሚሆን የሶስት አመት ከዋስትና ነጻ የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ስልጠናዎችን እንዲያገኙ እና ቢዝነሶቹን በቅርበት ውጤታማነታቸውን በመከታተል መደገፍ ላይ ያለበት ደረጃ ታይቷል። ሌላኛው አፈጻጸሙ የታየው ሳፊ ፕሮግራም ሲሆን ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ላይ የሚሰራና መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ብድሮችን በማቅረብ በተለይ ለኢ-መደበኛ ተበዳሪዎች በመታወቂያ ብቻ ብድሮችን ከእጅ ንክኪ ነጻ የሆነ በAI ታግዘው ብድሮችን ያመቻቻሉ፤ በዚህም በዋናነት 80% ሴቶች፣ 10% ለአካል ጉዳተኞች እና 10% ለተፈናቃዮች ትኩረት አድርጎ የሰራቸው ስራዎች በተጨባጭ ምን ላይ እንደሚገኙ ምልከታ ተደርጎባቸዋል፡፡ በተጨማሪም መስመር ፕሮግራም የብድር አገልገሎት ሴቶችና ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታትና ሥራቸውን ለማስፋፋት የሚሰጠውን የብድር አገልገሎት በአስተዳደሩ የሚገኙ በተለይም በወጣት ሴቶች የሚመሩ የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በመጠነኛ ዋስትናና በአነስተኛ የወለድ መጠን እንዲሁም የሸሪአ መርህን የተከተለ ከወለድ ነጻ የብድር አገልገሎት ተጠቃሚ የማድረግ ስራ ተጠቃሚዎችን በአካል በማነጋገር ያሉበትን ሁኔታ መመልከት ተችሏል፡፡ ቢሮው ከማስተር ካርድ አጋር ድርጅቶች ጋር በቅንጅት የሚሰራ ሲሆን የ2025 የመጀመሪያ ሩብ አመት የአምስቱም አጋር ድርጅቶች ሪፖርት በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+3

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ዘመን የአዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ምዝገባ ከጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 21/2018 ዓ.ም ድረስ የሚያከናውን
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ዘመን የአዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ምዝገባ ከጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 21/2018 ዓ.ም ድረስ የሚያከናውን መሆኑን እናሳውቃለን::

እንቁ ባለሙያዎችን የሚያፈራው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ዘመን የአዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ምዝገባ ከጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚያከናውን መሆኑን እናሳው
እንቁ ባለሙያዎችን የሚያፈራው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ዘመን የአዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ምዝገባ ከጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚያከናውን መሆኑን እናሳውቃለን::

በአዲስ የተዘጋጁ ሀያ ሁለት ስርዓተ ትምህርቶች ላይ ክለሳ የማድረግ ስራ መጀመሩ ተገለጸ፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት በአስተዳደሩ የሚገኙ የግል እና የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችን በማስተባበር የኢንተርፕርነርሺፕ እና ሀገር ወዳድነትና የስራ ላይ ስነ ምግባርን አካቶ በመጨመር የዘርፉን ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ የስርዓተ ትምህርቱን የመከለስ ስራ መጀመሩ ታውቋል። ለ2018 ዓ.ም የክህሎት ስልጠናውን በጥራት ለመስጠት እንዲቻል ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ባለፉት አራት አመታት በስርዓተ ትምህርቱ አተገባበር ሂደት ወቅት ያጋጠሙ ችግሮችን በመገምገም አዳዲስና ከዘመኑ ጋር የሚሄዱ አሰራሮችን የይዘትና የምስል መጣጣም ያለባቸውን ለማጣጣም ወደ ስራ መገባቱን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን ተናግረዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

ለፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን የተዘጋጀ በተግባር የተደገፈ ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስልጠና በሁለቱም ኮሌጆች እየተሰጠ መሆኑ ተገለጸ፡፡ በአቅም ግንባታ ስልጠናው የኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራኑ ሙያዊ ብቃታቸውን የሚያሳድጉበትና ከዚህም ባሻገር በየሙያ መስኩ በየኢንዱስትሪው ተግባራዊ ዕውቀትና ክህሎት እያገኙበት እንደሆነና የተሻለ ልምድና ተሞክሮዎችን ከአቻዎቻቸው የሚቀስሙበትን ዕድል እንደፈጠረላቸው መድረክ አሰልጣኝ መምህራኑ ተናግረዋል፡፡ በዚህ የአቅም ግንባታ ስልጠና የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ተሳታፊ ሲሆኑ ገበያው የሚፈልገውን ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያ ለማፍራት የአሰልጣኞችን ብቃት ተከታታይነት ባለው መልኩ ማሳደግ ወሳኝ በመሆኑ በሁለቱም ኮሌጅ እየተሰጠ እንደሚገኝ በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

የ2018 የቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና የመግቢያ ነጥብ መሰረት በአስተዳደሩ ባሉ ሰባት የግልና የመንግስት ኮሌጆች ሰልጣኞችን ለመቀበል ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጸ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሞያ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በሰጡት መግለጫ የ2018 የቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና የመግቢያ ነጥብ ይፋ መሆኑን ተከትሎ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማሰልጠን ዝግጅት ማጠናቀቁን ገለጹ ። ሀላፊዋ እንደገለጹት በ5 የግል ኮሌጆች እና በሁለቱ የመንግስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ከ4 ሺ በላይ አዳዲስ ተማሪዎችን ለማሰልጠን ዝግጅት ተጠናቋል ብለዋል:: ምዝገባውም ከጥቅምት 12 ጀምሮ ይካሄዳል። በመንግስት ኮሌጆች የሚገቡት በሁለቱ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የሳይኮ ሜትሪክ ምዘና እና የባዮ ሜትሪክ ምዝገባ በማድረግ ሲሆን በተመሳሳይ ወደ ግል ኮሌጆች ለመግባት ደግሞ በወረዳ አንድ ማዕከላት የባዮ ሜትሪክ ምዝገባ በማድረግ የሌበር መታወቂያ በመያዝ መመዝገብ እንደሚችሉ ጠቅሰዋል ። በ2017 ዓ.ም አስራ ሁለተኛ ክፍል ያጠናቀቁና ከዚህ በፊት 12ተኛ ክፍል አጠናቀው ወደ ኮሌጅ ያልገቡ ተማሪዎች በቴክኒክና ሞያ የመግቢያ ነጥብ መስፈርት መሰረት መግባት እንደሚችሉም በመግለጫው ተጠቅሷል። የትምህርትና ስልጠናው በመንግሥት ኮሌጆች ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 5 እንዲሁም በደረጃ 6 ዲግሪ ፕሮግራም የሚሰጥ ሲሆን በግል ኮሌጆች ደግሞ ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 4 ድረስ ይሰጣል። ኃላፊዋ አክለው እንደገለጹትም አስተዳደሩ ከአጎራባች ክልሎች ሰልጣኝ ተማሪዎችን እንደሚቀብሉም ጠቁመዋል። ©️ DireTvአማርኛ | ጥቅምት 11፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

photo content
+1

photo content

በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ከ4 መቶ 54 ሺህ 106 በላይ ዜጎችን ተቀብሎ ለማስተናገድ ዝግጅት ተደርጓል ክቡር ተሻለ በሬቻ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ የ2018 የትምህርትና ስልጠና ዘመን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የመቁረጫ ነጥብ ዛሬ ይፋ ተደርጓል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ለዜጎች ተግባራዊ እውቀትና ክህሎትን በማስታጠቅ የሥራ ፈጠራ አቅምና ችግር ፈቺ አስተሳሰቦችን ያለውን ቁልፍ ሚና በመገንዘብ መንግስት ለዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራበት ይገኛል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት ዘርፉ ለሀገራዊ የልማት ፍላጎት ምላሽ መስጠት እንዲችል የሥራ ገበያውን መሰረት ያደረገ የክህሎት ልማት አቅጣጫ ነድፎ በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በመደበኛና አጫጭር ስልጠና ተደራሽ እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ መሠረት 2017 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውጤትን፣ የሥራ ገበያው ፍላጎት እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የቅበላ አቅምን ከግምት ውስጥ በማስገባት የ2018 የትምህርትና ስልጠና ዘመን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት መቀበያ መቁረጫ ነጥብን ይፋ አድርጓል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) የመቁረጫ ነጥቡን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ባለፉት ሦስት ዓመታት በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ከ1,500 ባላይ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በአካባቢያቸው ያለውን ተፈጥሯዊ ፀጋ መሰረት ባደረገ መልኩ እንዲደራጁና ስልጠና እንዲሰጡ መደረጉን ክቡር ሚኒስትር ድኤታው አስታውቀዋል፡፡ የተቋማቱን የቅበላ አቅም ለማሳደግ በሚያስችል መልኩ የውስጥና የዲጂታል መሰረተ ልማትን የማስፋፋት ሥራ ሲሠራ መቆየቱን የገለፁት ሚኒስትር ዴኤታው በ2017 ዓ.ም በመደበኛ ከ5መቶ ሺ በላይ፣ በአጫጭር ስልጠና ደግሞ ከ4ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ማስተናገድ መቻሉን አስረድተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከ1መቶ ሺ በላይ የሚሆኑ በልምድ የሙያ ባለቤት የሆኑ ዜጎች ተመዝነው ዕውቅና ማግኘታቸውን ብሎም ከ5መቶ ሺ የሚልቁ ደግሞ ለውጭ ሀገር ሥራ ሥምሪት ብቁ የሚያደርጓቸውን ስልጠናዎች በቴክኒክና ሙያ ተቋማት መከታተላቸው ተገልጿል፡፡ በ2018 የትምህርትና ስልጠና ዘመን 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ከ4መቶ 54ሺ1መቶ ስድስት የሚሆኑ ዜጎችን ተቀብሎ በመደበኛ ፕሮግራም ለማሰልጠን፣ 4ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች አጫጭር ስልጠና በመስጠት ለሀገር ውስጥ የሥራ መስኮች ለማብቃት እንዲሁም ቁጥራቸው እስከ 8መቶ ሺ የሚሆኑ ዜጎችን ደግሞ በስልጠና አብቅቶ ለውጭ ሀገር የሥራ ገበያ ዝግጁ ለማድረግ የሚያስችል ዕቅድ መያዙንም አስታውቀዋል፡፡ ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: t.me/fdre_mols TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ “Gender based Violence code of conduct “ላይ ትኩረቱን ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለሁሉም የኮሌጁ ሰራተኞች አደረገ፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ወቅት ተገኝተው ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ኢ/ኤ/ቴ/ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በንግግራቸውም የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሰፊ ስራ እንደሚሰራበት መጠን ከብዙ ባለ ድርሻ አካላት ጋር ግንኙነት እንዲፈጠር ያደርጋል ስለሆነም በዚህ ዘርፍ ውስጥ ተሳታሲ የሆኑ አካላት ደግሞ በህግ አግባብ ስራቸውን መስራት እንዲችሉ መደላደል መፈጠር አለበት ያሉ ሲሆን ይህ በጀንደር ዩኒትና በEASTRIP ፕሮጀክት በኩል ተዘጋጅቶ የቀረበው code of conduct ደግሞ Gender based የሆኑ የViolence ችግሮች ቢፈጠሩ እነዚህን ችግሮች በምን አይነት መንገድ መፍታት ይቻላል የሚለውን የሚፈታ ነው ብለዋል፡፡ “Gender based Violence code of conduct “በጀንደር ዩኒትና በEASTRIP ፕሮጀክት በኩል በኮሌጁ በተቋቋመው የሪሰርች ቡድን ተጠንቶ የተዘጋጀ ሲሆን ሰነዱም ሙሉ በሙሉ ከከተማ አስተዳደሩ የሰራተኞች አዋጅ ጋር ተስማሚ ሆኑ የተዘጋጀ እንደሆነ በግንዛቤ ማስጨበጫ ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 7/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ You tube: Dire Dawa Polytechnic College(DDPTC) Facebook: https://web.facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: https://t.me/diredawapolytechniccollege TikTok: tiktok.com/@diredawapolytechnicollege