ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
Відкрити в Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
Показати більше3 306
Підписники
-224 години
-107 днів
-3830 день
Архів дописів
#ዜና ድጋሚ ኅትመት
📖ኆኅተ ስብከት📖
ቅዱስ ያሬድ በምድር ስንኖር ሊኖረን ስለሚገባን ሥነ ምግባርና ማኅበራዊ ትስስር፤ በዚህች ምድር ስለሚያስፈልጉን ነገሮች፤ በዙሪያችን ስላሉ ድንቅ ተፈጥሮዎች ተቀኝቷል፡፡ ለምሳሌ ስለመረጋጋት፣ ስለፍቅርና ስለሰብአዊ እኩልነት ካዜመው ውስጥ ለምሳሌ ቁም በዘሀሎከ ኢታንቀልቅል ወኢትትሐወክ ለዓለመ ዓለም፤ ወዘሰ ሕኑፅ በመሠረተ እግዚአብሔር አልቦቱ ዘተኀጕለ ወኢያፍቱከ ምክሮሙ ለረሲዓን ተዘከር ሠናያተ ዘገብረ ለከ እግዚአብሔር። ወንድሞቼ ሆይ ሰውን መጥላት ምን ይጠቅመናል? ወንድምን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነውና፡፡ ባለህበት ጸንተህ ቁም፤ ተረጋጋ፤ አትነዋወጥ አትጨነቅ፤ ለዘለዓለምም አትታወክ፤ በእግዚአብሔር መሠረት ላይ የታነጸ ሰው ጥፋትና ጉስቁልና የለበትምና፤ የክፎዎች ምክራቸውና ሥራቸው አያስጎምጅህ፤ አንተ ግን እግዚአብሔር በጎ በጎ ነገር ያደረገልህን ብቻ አስብ›› በማለት በኑሮ ሒደት ማኅበራዊ ቀውስ ገጥሟቸው የተጨነቁትን አካላት በዜማው ሲያረጋጋ እናገኘዋለን፡፡
የዝማሬ፣ የፍልስፍና፤ የስነ ከዋክብት፤ የሕግ፤ የታሪክ፣ የመልክዐ ምድርና የቋንቋ ሊቅ የሆነው ቅዱስ ያሬድ ዛሬ ዓለም ለደረሰበት የዜማ፣ የተፈጥሮ ሳይንስና የማኅበራዊ ሕይወት ፍልስፍናም መሠረት ነው ሊያስብል የሚያስችሉ ሰማያዊ ሰነዶችን ትቶልን አልፏል፡፡ የተፈጥሮን ሁኔታ ያስቃኘናል፡፡
ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ
-ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ ያዘጋጁት "ኆኅተ ስብከት ዘቅዱስ ያሬድ" የተሰኘ መጽሐፍ ለ4ኛ ጊዜ ስለታተመ በግዮን መጻሕት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
📚ግዮን መጻሕፍት መደብር ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ለበለጠ መረጃ፦በ0913083816 ይደውሉ።
t.me/GhionBookStore1623
ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ እና በመንፈስ ቅዱስ የባሕርይ አምላክነት ጥርጥር ባነሡ ከሐድያን ላይ እንዳደረገችው ኹሉ በእመቤታችን ላይም ክሕደት የተናገሩትን መናፍቃን ኹሉ እያራገፈቻቸው ራሷን አስከብራ ከእኛ ዘመን ደርሳለች። ከፍ ካለው የእምነት ተራራ ወደ ዝቅታው የኑፋቄ ንጥፍ ዓለት ስሑት ትምህርታቸውን አድቅቃ ፈጥፍጣቸዋለች።
ንስጥሮስ ወላዲተ አምላክ አትባልም ብሎ የጀመረውን ከፍተኛ ኑፋቄ አሳምና በመርታቷ እርሱ ቀረ እርሷ ቀጠለች። ያንን ጠንካራ ዕቅበተ እምነት ያየውና በጣም ዘግይቶ የተነሣው ሉተር እየፈራ እየተባ አታማልድም ወደ ማለት ዝቅ ለማለት ተገደደ። የእርሱም ክሕደት በቃለ እግዚአብሔር መዶሻ ስለተቀጠቀጠ ትርፍራፊዎቹ ቤዛዊት ዓለም አትባልም ወደ ማለት እንደገና ወረዱ። እነርሱ እየወረዱ እየወረዱ ወደ ጥልቁ ይከስማሉ። የድንግል ክብር ግን እያደር ይበልጥ ይገንናል።
📖#የሐዋርያው_የቅዱስ_ጳውሎስ_መለእክታት_ከሮሜ_እስከ_ገላትያ
❝#በሃይማኖት ላይ የሚጨምረውን ደፋር የሚቀንሰውን ሌባ ልንለው ይገባል እንዳለ ዮሐንስ አፈወርቅ በተግሣጹ ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንትም አባቶቻቸው ባስረከቧቸው ሃይማኖታዊ ምሥጢር ላይ ሳይጨምሩ እና ሳይቀንሱ ቅዱስ መጽሐፍን ንባቡ ለጆሮ ምሥጢሩ ለአእምሮ እንዲስማማ አድርገው ሲተረጉሙ ኖረዋል፡፡ #መጋቤ ሐዲስ ስቡሕ አዳምጤም ሃይማኖት ያላቸው ወደ ምግባር፣ ምግባር የሌላቸው ወደ ሃይማኖት እንዲቀርቡ በማሰብ ሃይማኖት ከምግባር የታረቀበትን ሕግ ከጸጋ የተስማማበትን የቅዱስ ጳውሎስን መልእክት ተንትነው እና አብራርተው አቅርበውልናል ።
❝በዚህ መሠረት ያላነበበ ክርስቲያን የሰይጣን ጉዳይ አስፈጻሚና የብልጣብልጥ መናፍቃን የሐሳብ መስጫ ሳጥን ይሆናልና ሃይማኖታዊ ዐይኑን ገልጦ መንፈሳዊ ጆሮውን ከፍቶ ውድ ጊዜውን ሠውቶ ቢያነበው እንደጠንቋይ የገመቱትን ከሚያወሩ ሐሰተኞች ሰባክያን ይጠብቀዋል ብዬ አምናለሁ፡፡
#መልካም_ንባብ!
#መጋቤ_ሐዲስ_እሸቱ_ዓለማየሁ
በሰዋሰወ ብርሃን ቅ/ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ መምህር
፨ ይህ ግሩም መጽሐፍ በድጋሚ የታተመ ሲኾን #በግዮን መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
📚በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባርና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ።
እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢያን በDHL እና በEMS መጽሐፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።አድራሻ ምንሊክ አደባባይ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ማኅበር ፊት ለፊት፤
ለበለጠ መረጃ፦በ0913083816 ይደውሉ።
t.me/GhionBookStore1623
📖#ሕይወተ_ማርያም_ድንግል📖
❝ሕይወተ ማርያም ድንግል በሚል ርዕስ የተጠቀሰው መጽሐፍ እመቤታችን ከፅንሰቷ ወራት ጀምሮ እስከ ዕስተ እረፍቷ የተጓዘችበትን የሕደወት መስመር በምሥጢራዊ አገላለጥ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መጽሔተ ብርሃን ሆና አግኝቼዋለሁ፣ አቀራረቡም ትምህርተ አበውን የተከተለ፣በትርጓሜ የበሰለ፤ ትውፊት አበውን አጉልቶ የሚያሳይ ቅዱስ መጽሐፍን መሠረት ያደረገ በመሆኑ እውነተኛ የቤተ ከርስቲያኒቱን ልጆች ያስተምራል ብየ አምናለሁ፤ በጸሐፊውም መንፈሳዊ ኩራት ይሰማናል፣ ብዙዎች ስለ እመቤታችን መስበክና መጻፍ አንደ ነውር ተቆጥሮባቸው በተፈተኑበት ዘመናችን በቋንቋ አጠቃቀሙ በአቀራረቡ የተዋሕዶ ልጆችን የሚያበረታታ ጽሐፍ በመጻሩቸው አደንቃቸዋለሁ: ለወደፊቱም ብዙ እጠብቃለሁ አነሣስቶ ላስጀመራቸው፤ አስጀምሮም ላስፈጸማቸው
ለልዑል እገዚአብሔር ከብርና ምስጋና ይሁን፡፡❞
#አባ_አብርሃም
⨳የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
❝እንደው እለት እለት አዲስ ኹል ጊዜ ልዩ እንደያውም ወይን ነው ብል ትክክል ነኝ !ምክንያቱም እያደር አዲስ ነው እለት እለት ሲነበብም ልዩ ለዩ ጣፋጭ እውቀትን ያስይዛልና። ስለ እመቤታችን ስለ ቅድስቷ ሕይወት ከጽንሰቷ -እርገቷ ድንቅ በሚባል አጻጻፍ ሲያትትማ ወይ ጉድ ሳያሰኝ አይቀርም!
#ውድ_አፍቃርያነ_ንባብ ብቻ ደስ በሚል ኹኔታ የተጻፈ ብሎም ውስጣችን ያለውን #የድንግሏ ፍቅሯን ይበልጥ እንዲቀጣጠል ያደርጋልና አያምልጠን እያልን መጽሐፉን #በግዮን_መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል።
📚በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባርና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ።
እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢያን በDHL እና በEMS መጽሐፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።አድራሻ ምንሊክ አደባባይ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ማኅበር ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ፦በ0913083816 ይደውሉ።
t.me/GhionBookStore1623
#ቅዳሴ_ ዐዲስ መጽሐፍ
-በቀሲስ መብራቱ ኪሮስ(ዶ/ር) የተዘጋጀ "ቅዳሴ" የተሰኘ ዐዲስ መጽሐፍ በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
📚በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባርና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ።
እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢያን በDHL እና በEMS መጽሐፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። አድራሻ ምንሊክ አደባባይ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ማኅበር ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ፦በ0913083816 ይደውሉ።
t.me/GhionBookStore1623
#ሕይወተ_ማርያም_ድንግል📖
❝ሕይወተ ማርያም ድንግል በሚል ርዕስ የተጠቀሰው መጽሐፍ እመቤታችን ከፅንሰቷ ወራት ጀምሮ እስከ ዕስተ እረፍቷ የተጓዘችበትን የሕደወት መስመር በምሥጢራዊ አገላለጥ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መጽሔተ ብርሃን ሆና አግኝቼዋለሁ፣ አቀራረቡም ትምህርተ አበውን የተከተለ፣በትርጓሜ የበሰለ፤ ትውፊት አበውን አጉልቶ የሚያሳይ ቅዱስ መጽሐፍን መሠረት ያደረገ በመሆኑ እውነተኛ የቤተ ከርስቲያኒቱን ልጆች ያስተምራል ብየ አምናለሁ፤ በጸሐፊውም መንፈሳዊ ኩራት ይሰማናል፣ ብዙዎች ስለ እመቤታችን መስበክና መጻፍ አንደ ነውር ተቆጥሮባቸው በተፈተኑበት ዘመናችን በቋንቋ አጠቃቀሙ በአቀራረቡ የተዋሕዶ ልጆችን የሚያበረታታ ጽሐፍ በመጻሩቸው አደንቃቸዋለሁ: ለወደፊቱም ብዙ እጠብቃለሁ አነሣስቶ ላስጀመራቸው፤ አስጀምሮም ላስፈጸማቸው
ለልዑል እገዚአብሔር ከብርና ምስጋና ይሁን፡፡❞
#አባ_አብርሃም
⨳የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
❝እንደው እለት እለት አዲስ ኹል ጊዜ ልዩ እንደያውም ወይን ነው ብል ትክክል ነኝ !ምክንያቱም እያደር አዲስ ነው እለት እለት ሲነበብም ልዩ ለዩ ጣፋጭ እውቀትን ያስይዛልና። ስለ እመቤታችን ስለ ቅድስቷ ሕይወት ከጽንሰቷ -እርገቷ ድንቅ በሚባል አጻጻፍ ሲያትትማ ወይ ጉድ ሳያሰኝ አይቀርም!
#ውድ_አፍቃርያነ_ንባብ ብቻ ደስ በሚል ኹኔታ የተጻፈ ብሎም ውስጣችን ያለውን #የድንግሏ ፍቅሯን ይበልጥ እንዲቀጣጠል ያደርጋልና አያምልጠን እያልን መጽሐፉን #በግዮን_መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ አዘጋጅተናል።
#ቅዳሴ_ ዐዲስ መጽሐፍ
-በቀሲስ መብራቱ ኪሮስ(ዶ/ር) የተዘጋጀ "ቅዳሴ" የተሰኘ ዐዲስ መጽሐፍ በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
📚በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባርና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ።
እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢያን በDHL እና በEMS መጽሐፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። አድራሻ ምንሊክ አደባባይ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ማኅበር ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ፦በ0913083816 ይደውሉ።
t.me/GhionBookStore1623
"እግዚአብሔር ከእንቅልፉ እንደሚነቃ ተነሣ" (መዝ 78:65)
ውድ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም በጤና አደረሰን!!!
"ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና (1ኛ ቆሮ 15፡21)
"ሰማያት (ሰማያውያን መላእክት) የደስታ በዓልን ያደርጋሉ፤ ደመናት (ቅዱሳን) የደስታን በዓል ያደርጋሉ፣ ምድር (ምድራውያን ሰዎችም) በክርስቶስ ደም ታጥባ (ታጥበው) የፋሲካን በዓል ታደርጋለች (ያደርጋሉ/ያከብራሉ /ታከብራለች)፡፡ ዛሬ በሰማያት (በሰማያውያን መላእክት) ዘንድ ታላቅ ደስታ ሆነ፤ ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ የፋሲካን የነጻነት በዓል ታደርጋለች፡፡ የትንሣኤያችን በኲር ክርስቶስ ከሙታን ሁሉ ተለይቶ ቀድሞ ተነሣ፡፡" (ድጓ ዘፋሲካ)
ክርስቶስ ከዲያብሎስ ባርነት ነፃ አወጣን እኛም ራሳችንን ከዘመኑ የኅሊና ባርነት ነፃ እናውጣ!
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን!
በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን!
አሠሮ ለሰይጣን!
አግዐዞ ለአዳም!
ሰላም!
እምይእዜሰ!
ኮነ!
ፍሥሐ ወሰላም!
መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንልን!!!
ሳይንስ እና ሃይማኖት
..✍ሳይንስ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን አዕምሮ ተጠቅሞ ያስገኘውና በዚህ ዓለም ያለውን የኑሮ ድካም ማቅለያው የዕውቀት ዘርፍ ሲሆን ሃይማኖት ደግሞ ከአምላኩ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኘው መንገድ ነው። ነገር ግን የሳይንስን ውሱንነት ያልተረዱ ሰዎች ሃይማኖትን በሳይንሳዊ ዕውቀት ለመተንተን ሲሞክሩና ወደ ተሳሳተ ግንዛቤ ሲያመሩ ይስተዋላል። በሌላ መልኩ ደግሞ ሳይንስ ለመንፈሳዊ ሰዎች እርባና የሌለው ነው ብለው የሚያምኑም አሉ።
ይህንን በተመለከተ ለሚነሱ ጥያቄዎችና ፍልስፍናዊ አስተያየቶች፣ ጸሐፊው መምህር ያረጋል አበጋዝ፣ በዚህ መጽሐፉ ከሳይንስና ከሃይማኖት ጋር በተገናኙ ፍልስፍናዊ አስተሳሰቦች ዙሪያ ሰፊ ጥናት በማድረግ ከጥልቅ ትንታኔ ጋር አቅርቦልናል። ስለሆነም መጽሐፉን አንብበን የተሻለ ግንዛቤ እንድናገኝና እንድንጠቀምበት እየጠየቅኩ፣ ለመምህር ያረጋል ዕድሜና ጤናን ለእናንተ ለአንባብያን ደግሞ መልካም ንባብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
ቀሲስ ሰሙ ምትኩ (ፕሮፌሰር)
ቦትስዋና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ
ይህ መንፈሳዊ እና ሳይንሳዊ እሳቤዎችን የተነተነ በግሩማን ሐሳቦች የታጨቀው [የተሞላው] በመምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የቀረበ ጥዑም ማዕድ[መጽሐፍ ] ለ ሁለተኛ ጊዜ ታተሞ እያለቀ ስለሆ ውስን ቅጅዎች ስላሉን ይጎብኙን በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኛሉ።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
#ቀዳሚት_ሥዑር_ (#ሥዑር_ቅዳሜ)፤ #ገብረ_ሰላመ_፤ (#ለምለም_ቅዳሜ)
#ሰንበት_ዐባይ #ቅዱስ_ቅዳሜ፤ #ቀዳሚት_ሰንበት
#ቀዳሚት_ሰንበት፤ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ ከፈጸመ በኋላ ያረፈባት ስለሆነች፤ የእግዚአብሔር የዕረፍት ዕለት፤ ቀዳሚት ሰንበት (የዕረፍት ቀን) ትባላለች፡፡
#ሰንበት_ዐባይ (ታላቋ ሰንበት)፤ የመጀመሪያዋ ሰንበት በመሆኗ ታላቋ ሰንበት ትባላላች፡፡
#ቀዳሚት_ሥዑር_ (#ሥዑር_ቅዳሜ)፤ እግዚአብሔር ሥነ ፈጥረትን ከመፍጠር ዕረፍት እንዳደረገባት ዅሉ፣ የፍጥረት ርእስ የኾነውን አዳምን ለማዳን ሕማምና ሞት የተቀበለው አምላካችን ክርስቶስ በከርሰ መቃብር አርፎባታል፡፡ (ማቴ. ፳፯፥፷፩)፡፡
፠ ‹ሥዑር› የተባለችበት ምክንያትም በዓመት አንድ ቀን ስለምትጾም (የጾም ቀን በመኾኗ) ነው፡፡
የጌታችን እናት ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ወዳጆቹ ቅዱሳን ሐዋርያትና ሌሌችም የጌታ ወዳጆች ጌታችን ተላልፎ ከተሰጠበት ዕለት ጀምሮ ብርሃነ ትንሣኤውን እስኪያዩ ድረስ እህል ውኃ በአፋቸው አልዞረም፡፡ ይመኩበትና ተስፋ ያደረጉት የነበረ አምላካቸው በመቃብር ስላረፈ ዕለቷን ሞቱን በማሰብና ትንሣኤውን በመናፈቅ በጾም አክብረዋታል፡፡
፠ የቻልን ሕዝበ ክርስቲያንም ይህን መነሻ በማድርግ ከዐርብ ጀምረን በማክፈል (በመጾም) እህል ውኃ ሳንቀምሱ ለሁለት ቀናት እናድራለን (እንካፍላለን)፡፡ እንደ ዋልድባና ማኅበረ ሥላሴ ባሉ ገዳማት ያሉ ታላላቅ አባቶችና ወንድሞች ደግሞ ከሆሳዕና አንዳንዶችም ከዕለተ ረቡዕ ጀምረው ለ7ት ቀናት ወይም ለ3ት ቀናት ያከፍላሉ፡፡
#ገብረ_ሰላመ_፤ (#ለምለም_ቅዳሜ)
ቅዳሜ የጠዋቱ ጸሎት ሲፈጸም ካህናቱ ‹‹ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፤ (በመስቀሉ ሰላምን አደረገ፥ መሠረተ)›› እያሉ በቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰቡ ምእመናን የምሥራች ቄጠማ ያድላሉ፡፡
፠ ቄጠማው በኖኅ ዘመን በንፍር ውኃ ምደር በተጠለቀለቀች ጊዜ፤ ኖኅ ወደ መርከብ ይዟቸው ከገባው እንስሳት መካከል የውኃውን መጉደል ለመረዳት ርግብን በመርከብ መስኮት አሾልኮ ልኮ እርሷም ቄጠማ በአፏ ይዛ በመመለስ የምሥራች ምልክት፥ የውኃውን መድረቅ እንደተነገረችውና እንደተደሰተ ሁሉ (ዘፍ. ፱፥፩-፳፱)፡፡ ‹‹በክርስቶስ ሞት፤ ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ፤›› ስንል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቅዳሜ ጠዋት ደባትር መዘምራን ዝማሬን ካቀረቡ በኋላ ለልጆቿ ቄጠማ ታድለናለች፡፡ የምሥራች ተምሳሌት የኾነውን ቄጠማም፤ ከሲኦል ቃጠሎ ወደ ጥንተ ማኅደራችን ገነት መመለሳችንን ለመመስከር በግንባራችን እናስረዋለን፡፡
#ቅዱስ_ቅዳሜ፤ ለ5500 በሲኦል ሲማቅቁ የነበሩ ነፍሳትን ሰላም ለሁላችሁን ይሁን ብሎ ወደ ገነት አስገብቷቸዋልና፤ ይህች ቅዳሜ ቅዱስ (የተለየች) ቅዳሜ ትባላለች፡፡
ዜና ድጋሚ ኅትመት !
ሳይንስ እና ሃይማኖት
..✍ሳይንስ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን አዕምሮ ተጠቅሞ ያስገኘውና በዚህ ዓለም ያለውን የኑሮ ድካም ማቅለያው የዕውቀት ዘርፍ ሲሆን ሃይማኖት ደግሞ ከአምላኩ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኘው መንገድ ነው። ነገር ግን የሳይንስን ውሱንነት ያልተረዱ ሰዎች ሃይማኖትን በሳይንሳዊ ዕውቀት ለመተንተን ሲሞክሩና ወደ ተሳሳተ ግንዛቤ ሲያመሩ ይስተዋላል። በሌላ መልኩ ደግሞ ሳይንስ ለመንፈሳዊ ሰዎች እርባና የሌለው ነው ብለው የሚያምኑም አሉ።
ይህንን በተመለከተ ለሚነሱ ጥያቄዎችና ፍልስፍናዊ አስተያየቶች፣ ጸሐፊው መምህር ያረጋል አበጋዝ፣ በዚህ መጽሐፉ ከሳይንስና ከሃይማኖት ጋር በተገናኙ ፍልስፍናዊ አስተሳሰቦች ዙሪያ ሰፊ ጥናት በማድረግ ከጥልቅ ትንታኔ ጋር አቅርቦልናል። ስለሆነም መጽሐፉን አንብበን የተሻለ ግንዛቤ እንድናገኝና እንድንጠቀምበት እየጠየቅኩ፣ ለመምህር ያረጋል ዕድሜና ጤናን ለእናንተ ለአንባብያን ደግሞ መልካም ንባብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
ቀሲስ ሰሙ ምትኩ (ፕሮፌሰር)
ቦትስዋና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ
ይህ መንፈሳዊ እና ሳይንሳዊ እሳቤዎችን የተነተነ በግሩማን ሐሳቦች የታጨቀው [የተሞላው] በመምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የቀረበ ጥዑም ማዕድ[መጽሐፍ ] ለ ሁለተኛ ጊዜ የታተመ ሲሆን በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0912198891
፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
+4
✨✨✨✨✨✨✨✨✨
#ንሴብሖ_ለእግዚአብሔር_ስቡሐ_ዘተሰብሐ
#ለወደደን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን፥
መንግሥትም ለአምላኩና ለአባቱም ካህናት እንድንሆን ላደረገ፥ ለእርሱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ክብርና ኃይል ይሁን፤
“አሜን በረከትና ክብር ጥበብም ምስጋናም ውዳሴም ኃይልም ብርታትም ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ለአምላካችን ይሁን፤ አሜን ።” — ራእይ 7፥12
እንኳን አደረሰን!
🙏🙏🙏
# ከ መምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተገኙ እንቁ መጻሕፍት
©አነዚኽን ጣፋጭ ምግቦች ተመግበዋቸው ይኾን...?
📚#ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
ሕይወቱ እና ትምህርቱ እና
# ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ
#ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
ሕይወቱ እና ትምህርቱ
ከሕይወቱ ቅምሻ
[....አባ እለእስክንድሮስም አትናቴዎስን በመንበረ ፓትርያርኩ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርትና ሥርዓት እያስተማረ አሳደገው፤ እርሱም ተወዳጅ ልጅ ሆነው፡፡ ከዚሁም ጋር ሰዋስው፣ ፍልስፍና፣ ክሂሎተ ነቢብና ሌሎች በዘመኑ የነበሩ ትምህርቶችንም በሚገባ ተማረ፡፡ ቆይቶም ለመዓርገ ምንኵስና በቃ᎓᎓ በቅድስናው፣ በሞያውና በግብረ ገብነቱ እንከን የሌለው ወጣቱ አትናቴዎስ በ23 ዓመቱ ....]
#ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ሕይወቱ እና ትምህርቱ
ከሕይወቱ ቅምሻ
[....ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ራሱን ከዚህ ዓለም የበለጠ ለመሰወርና ብቻውን ዘግቶ ለመኖር በመፈለጉ ወደ ዋሻ ውስጥ ገብቶ በብሕትውናና በጽኑ ትኅርምት ለሁለት ዓመት ሲጋደል ኖረ። በዚያም በትጋሃ ሌሊት፣ ለራሱ ዕንቅልፍ በመከልከል፣ በቀዊም፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን በቃል በማጥናት፣ በጸሎትና በተዘክሮ ኖረ በመቀጠልም ....]
【#ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ከውስጥ ገጽ የተቆረሰ】
[..ሁሉም የሌሊት ቅዠቶች ኖረዋል፡፡ ሌሊቱ አልፎ ቀኑ በመምጣቱ ከጨለማው ጋር አብረው የጠፉ ህልሞች ብቻ ነበሩ፡፡ ያለ መስሎ ታይቶ እንደጠፋ ጥላ፣ ወደ አየር ተኖ እንደጠፋ ጢስ፣ ሟሙቶ እንዳለቀ አረፋ፣ እንደተበጣጠሰ የሸረሪት ድር ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሁል ጊዜ ይህንን መንፈሳዊ መዝሙር እንዘምራለን፡- “ሁሉ ከንቱ፣ የከንቱ ከንቱ ነው” የሚለውን፡፡]››
👉መጻሕፍቱን በግዮን መጻሕፍት ያገኙታል !
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
