ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
Відкрити в Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
Показати більше3 306
Підписники
-224 години
-107 днів
-3830 день
Архів дописів
Голосове повідомлення00:01
📖#ታኦዶኮስ
©በመምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
❝.....በጎንደር መንበረ መንግሥት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን የዐራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት የትርጓሜ መምህር የሆኑት የሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ደቀ መዝሙርና የጉባኤ ቤቱ ምክትል መምህር በሆኑት በመምህር በጽሐ ዐለሙ ታኦዶኮስ በሚል ርእስ የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ አማኞችን ሳይቀር ለሚያነታርከው እመቤታችን ጥንተ አብሶ አለባት የለባትም ለሚለው ጥያቄ ከቤተ ክርስቲያናችን ነባር ኣስተምህሮ አንጻር መልስ የሚሰጥ ግሩም መጽሐፍ ነው፡፡
.... ወደፊት በጽሑፍ ልትጠቅሙን የምትመኙ ሁሉ ወደፊት ለምትሠሩት ሥራ ቢያንስ እንደ አንድ መክፈቻ የሆነውንና ሌሎቹንም ጥያቄዎች በአስተማማኝነት ለመመለስ ብልሃትንና መንገድን የሚያሳየውን ይህን ድንቅ መጽሐፍ አንብባችሁ እንድትጠቀሙ በታላቅ ትሕትና ስጋብዛችሁ ከአነበባችሁ በኋላ በምታገኙት ትንሽ የማይባል ጥቅም የምትደሰቱት ደስታ እንደሚኖር በመተማመን ጭምር ነው፡፡
#ብርሃኑ አድማስ (ዲያቆን፣ በሥነ ድርሳን ሁለተኛ ዲግሪ)
⩩እንደ እውነቱ የእናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ነገር የማይሸነቁጠው አማኝ [ኦርቶዶክሳዊ ] አለ ለማለት ያስቸግራል ለዚህም የልብን የሚያደርስ መጽሐፍ እነሆ ያሉንን የኔታ በጽሐ አለሙን ያኑርልንንን እያልን መጽሐፏን ሁላችንም አንብበን እናተርፍበት ዘንድ መጽሐፉን #በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል ።
# ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623
📖“ወልታ ጽድቅ”
❝... የዚህ መጽሐፍ “ወልታ ጽድቅ” አዘጋጅ (በብዕር ስሙ በአማን ነጸረ) ደግሞ ከይዘት አንጻር የሚራራቁ የሚመስሉ ነገር ግን ከላይ ከጠቀስኩት እሳቤና ሁለቱም እመቤታችን ማዕከል ከማድረጋቸውም አንጻር የሚገናኙትን እነዚህን ሁለት ጉዳዮች እንደ ብልህ ገበሬ አንድ ላይ ጠምዶ አቅርቦልናል፡፡ ምንም እንኳ ሁለቱም[ታሪክና ሃይማኖት ]ጉዳዮች በየራሳቸው ገና ብዙ ሊጠኑ፤ ሊጻፍባቸውና ሊብራሩ የሚችሉ ቢሆኑም በእነ ንባብ መሠረት ከሆነ ለዘመኑ ትውልድ በጥሩና በተሻለ መንገድ ሲቀርቡ “ወልታ ጽድቅ” የመጀመሪያ መጽሐፍ ይመስለኛል፡፡ በእኔ እምነት በአማን በእነዚህ ሁለት እጅግ አስፈላጊ ጉዳዮች ላይ ካቀራረቡ ጀምሮ አዲስ ነገሮችን ይዞ ብቅ ብሏል። ስለዚህም በጉዳዩ ላይ ማወቅ፣ ማጥናት፣ መመራመር፣ መሞገት መረዳትና መጻፍ ብቻ ሳይሆን መታዘብ የሚፈልግ እንኳ ቢሆን ወልታ ጽድቅን እንዲያነብብ በልበ ሙሉነት እጠቁመዋለሁ፡፡ ታሪካዊ ግንዛቤን እንደ እምነት ፤ እምነትን እንደ ዐለማዊ ዕውቀት ይዞ ነገር ለተገላበጠበትም ወደ ፍጹሙ መድኃኒትና ድኅነት የምታደርሰው የስቃይ ማስታገሻ (ant pain) ልትሆንለት የምትችል ምርጥ ቅመማ ናት፤ ወልታ ጽድቅ፡፡❞
#ብርሃኑ አድማስ (ዲን፣ በሥነ ድርሣን ሁለተኛ ዲግሪ)
#ይህን ጥዑም መጽሐፍ በግዮን መጻሕፍት ያገኙታል ።
# ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
📍 አድራሻ ምኒልክ አደባባይ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ በምዕራብ በር ማይክሮ ሊንክ እንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
ይደውሉልን !📞፦0913083816
፦0912198891 https://t.me/GhionBookStore1623
Repost from N/a
👉 ©የነነዌን ጾም ማሳለጫችን ይኹን!!
#የምህረት በር
በ ቃኘው ወልዴ
ንስሐን [በአንጻረ-ሕዝበ-ነነዌ] አጥብቆ ሰባኪ ፣ መንፈሳዊነት ለሚጎረብጠው መንቻካ ልብ አለዛቢ ዘይት ፣ መንፈሳዊ ቁመናን ከራስ ጠጉር እስከ እግር ጥፍር በዓይነ ሕሊና የሚከስት መስታወት ፣ የእግዚአብሔርን ምሕረት እና የእኛን ምንነት መሳ ለመሳ እያሳየ ነፍስን ኧረ ንቂ እያለ ወትዋች......
መጽሐፍ #የምሕረት_በር!
የነነዌን ጾም ማሳለጫችን ይኹን!!
ከተጣልኹበት ሰማኝ!!
‹‹... ተጣልኹ ፣ እርሱም ከተጣልኹበት ከጥልቁ ሰማኝ ፣ ሞት በሲኦል መካከል አሳለፈኝ ፣ አንተ ግን ጠበቅኸኝ፡፡ ባሕር ከበበኝ አንተም ያለ መቅዘፊያ ጠበቅኸኝ፡፡ አንተ በጥልቁ ቆለፍኽብኝ ፣ ወደ ባሕሩም ጣልኸኝ፡፡ ወደ ባሕሩ ጥልቅ ወረድኹ ፤ እሞት ዘንድ ግን አልተውኸኝም፡፡ ሞት ሰለቀጠኝ ፣ አንተ ግን በአፉ ውስጥ ሕያው አድርገኽ አኖርኸኝ፡፡ ምንም እንኳን ውኃው ቢሸፍነኝም ፥ እታፈን ዘንድ ግን አልተውኸኝም፡፡ ዳሩ ግን መደነቅ ያዘኝ! ህየንተ ሞት ሕይወት ከፍ ከፍ አደረገኝ! ተስፋዬ ሙሉ ለሙሉ ሲሟጠጥ አንተ መለስኸኝ፡፡ ስለዚኽ ከጥልቁ ባሕር አንደበቴ በብዙ አመሰገነኽ ፤ ከባሕሩ ጠለልም በደስታ ለገናናው ስምኽ ዘመርኩልኽ!🙏 ጌታ ኾይ፥ በኢየሩሳሌም ባለው ታላቅ ቤተ መቅደስ በታቦቱ ተውኩኽ [ከአንተ ተለይቼ <ወደ ፍቃዴ> ወጣኹ] ፣ ነገር ግን በመሬት ሥር በጥልቁ ለእኔ መንገድን ስታዘጋጅልኝ አገኘኹኽ! አንተ ከውኆች በላይና በታች ፣ በእርሱ ውስጥና ከርሱ ወዲያም በምልዓት አለኽ፡፡ አድባራት ፣ ቀላያት ፣ አቅጣጫዎች ኹሉም ያለማቋረጥ ያለመታከት ያመሰግኑኻል!! ...»
[የምሕረት በር፣ ገጽ 261]
መጽሐፉን በ፦ግዮን መጻሕፍት ያገኙታልhttps://t.me/GhionBookStore1623
#ኹለቱ ኪዳናት
"ሌላ መሠረት እንዳትሹ ዕወቁ፤"ዕብ፮÷፩
አንዳንድ ሰዎች ግን የንስሓን /የመናዘዝንና ቀኖና የመቀበልን ምሥጢር ረብህ የሌለው አድርገው ከማስተማራቸው የተነሣ ከእግዚአብሔር መንግሥት ይለያሉ። ትምህርታቸው ቀድሞ ምግባርን በኋላም የምግባርን እናት ሃይማኖትን ያስተዋቸዋልና።
#ኃጢአታችን ይቅር ሊለንና ከዓመፃም ኹሉ ሊያነፃን የታመነና ጻድቅ ነው። 1ኛዮሐ:19❞ስለዚኽ ንስሓ ኃጢአትን ኹሉ የምታስተሠርይ የእግዚአብሔር በር ናት። ❝ቅዱስ ጳውሎስ ንስሓን የሚቃወም ትምህርት ከሞት የማያድን ነውና መሠረትን ደግመን እንመሥርት አለን። “... ይኽን እወቁት " ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ።" ኤፌ.53 13 በማለት አንዳንዶች “ከንቱ ንግግር” በተባለ የውሸት ትምህርታቸው ብዙዎችን የኃጢአት አበጋዝ : አድርገው : ነበርና : ከዚኽ መጠበቅ እንደሚገባ ያስተምረናል። ❞በአኹኑም ጊዜ “እግዚአብሔር ፍጹም መሐሪ ነው" በሚል ፈሊጥ የሰውን ኹሉ ኃጢአት ዝም ብሎ ይቅር እንደሚል የሚያስተምሩና ሰውን ወደ ኃጢአት የሚጋብዙ መኖራቸውን አውቆ ራስን መጠበቅ ያስፈልጋል። የእግዚአብሔር ምሕረት ለተነሣሕያን እንጂ ክሳደ ልቡናቸውን አደንድነው በኃጢአት ለሚተጉት ኹሉ _ አይደለም፤ “እግዚአብሔር የሚያጠፋ እሳት ነው።" ዕብ.12፥29፡፡ ................. ❞ደግሞስ ስለ ቅብዐትና ጸጋ አመጣጥና ታሪካቸውን በወፍ በረር ቃኘት አድርጎ እግረ መንገዱን አጠር ብላ የማታዳግም ምላሽ ሲሰጡ ወቸው ጉድ ሳያስብለን አይቀርም ! 🤔የቀረውንማ ምን ከቃሉ አገባብ በብዙ መንገድ ካለው ፍቺ እኛ ካለንበት አኹናዊ ኹናቴ ኸረ .....በብዙ መንገድ #ዕብራውያን14ቱ መልእክታት ትርጓሜ ላይ ተመስርቶ በደንብ እየተነተነ ልብን በላይኛው ሀገር ይዞ የሚከንፍ #በመሪጌታ ኃይሎም በርሄ ተዘጋጅቶ #ዲያቆን ብርሃኑ አድማስን ደግሞ አርታዒ በማድረግ የቀረበ ይኽ ግሩም መጽሐፍ #በግዮን መጻሕፍት ያገኙታል። # ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 ፦0912198891 https://t.me/GhionBookStore1623
#ገድለ ሐዋርያት
"በሐዋርያት ና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል"ኤፌ፪÷፴...." ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ለተሰጠች ሃይማኖት ተጋደሉ” ተብለናልና፡፡ ይሁ ፩፡፡ የተጠራነውም ልናምን ብቻ ሳይሆን መስቀሉን ልንሸከም መከራ ልንቀበል ጭምር ነው። ስለ እርሱ መከራ ልትቀበሉ እንጂ ልታምነ ብቻ አይደለም” እንዲል። ፊል ፪፡፳፬ ❞የቅዱሳን ሐዋርያትን ታሪካዊ ሕይወት ማወቅ #ቅዱስ እግዚአብሔርን ለሚያመልኩ ምእመናን ጥቅሙ የጎላ ነው፡፡ ለሃይማኖታዊ ጉዟቸው መንገድ መሪዎች ናቸውና፡፡ "የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፤ የእምነታቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው” በማለት ቅዱስ ጳውሎስ ለዕብራውያን ምእመናን የመከረውም ለዚህ ነው፡፡ ዕብ ፲፫፥፯ ስለሆነም ምእመናን በሃይማኖት ዋኖቻቸው የሚሆኑ የሐዋርያትን ታሪክ በተገቢው መንገድ ማወቅና መረዳት ይኖርባቸዋል፡፡ ቅዱሳኑ ለሃይማኖታቸው የከፈሉትን ዋጋ ካወቁና ከተረዱ ‹‹እኔስ ለሃይማኖቴ ምን ማድረግ አለብኝ? ፈጣሪዬንስ እንዴት ላስደስተው?›› የሚለውንና የመሳሰሉ ጉዳዮችን ለመወሰን ይችላሉ፡፡ ❝ቤተ-ክርስቲያን ምእመናኖቿ የዚህ አማናዊና አምላካዊ ቃል ኪዳን ተሳታፊዎች ይሆን ዘንድም ‹‹ዛሬ ቅዱስ ጴጥሮስ ነው፡፡ ዛሬ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው፡፡›› ወዘተ እያለች ገድላቸውን ጽፋ፣ ያልተተረጎመውን ተርጉማ ስለእግዚአብሔር ወዳጆች ቅዱሳን ለምእመናን ታስተምራለች፡፡ በዚህም ምእመናን የበረከት ሰዎች ይሆናሉ፡፡ ”በረከት በጻድቅ ራስ ነውና” ምሳ ፲፮፡፡ መታሰቢያቸው ዘመን የማይሽረው በመሆኑም ምእመናን ለዘለዓለሙ ተጠብቀውበት ይኖራሉ፡፡ #እነዚህና የመሳሰሉት ጉዳዮች ተግባራዊ ይሆኑ ዘንድም ገድለ ሐዋርያት መተርጎም አስፈላጊነቱ ለዚህ ነው፡፡ #በመሆኑም በሐዋርያት መሠረትነት ላይ የተመሠረተ ምእመን እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት በሃይማኖቱ ለመጽናትና ታሪካቸውን ተገንዝቦ የቃል ኪዳናቸው ተሳታፊ ለመሆን መጽሐፉን ማንበብ ተገቢ ነው፡፡ በማለት #መምህር ተስፋሚካኤል ታከለ የተዘጋጀውን ይህን የቅዱሳኑን ዜና ሕይወት [ገድል ]#በግዮን መጽፍት ያገኙታል ። # ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 ፦0912198891 https://t.me/GhionBookStore1623
የብርሃን እናት ለ10 ግዜ ታትማለች
"እግዚአብሔር የሰው ልጅን ያዳነበት መንገድ በዕለተ ዐርብ በመሰቀሉና መከራን በመቀበሉ ብቻ የሚመስለውና ከነገረ መስቀሉ ውጪ ያለው ጉዳይ የሚጠቅም የማይመስለው ሰው ካለ ነገረ ድኅነትን ጨርሶ አልተረዳም፡፡
እንደዚያ ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔር በድንግል ማርያም ተፀንሶ ተወልዶ ሠላሳ ዓመታትን መቆየት ሳያስፈልገው ልክ የመጀመሪያውን አዳም እንደፈጠረው የሠላሳ ዓመት የሆነ ሥጋንና ነፍስን ለራሱ ፈጥሮ መለኮቱን አዋሕዶ ሰው መሆን ይችል ነበር፡፡ ይህንን ቢያደርግም ሦስት ዓመታት በምድር ላይ አስተምሮ በጊዜው ተሰቅሎ የማዳን ሥራውን መፈጸም ይችል ነበር፡፡
እርሱ ግን ማዳኑን የጀመረው በማሕፀን ከመፀነስ ነበር፡፡
አረጋዊው ስምዖን ‘ዓይኖቼ ማዳንህን አይተዋል’ እንዳለ ማዳኑንም የጀመረው ሕፃን ሆኖ በመታቀፉ ነው፡፡ ሉቃ. ፪፥፴
አልፋና ኦሜጋ እኔ ነኝ ላለው ክርስቶስ በምድር ላይ በቆየበት መዋዕለ ሥጋዌው አልፋው ድንግል ማርያም ስትሆን ኦሜጋው መስቀል ነበር፡፡ የተሰቀለ ቀን ብቻ አይተህ ልታውቀው አትችልም፡፡ ሁለተኛ አዳምነቱ ዘልቆ የሚሰማህ ወደ ልደቱ ስትመለስ ነው፡፡ የሰው ልጅ ቁስልም የሻረው ጌታ ሊወለድ ካለበት ቅፅበት ጀምሮ ነው"
የብርሃን እናት ገጽ 97
በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባርና አዳዲስ መጽሐፍትን ዘወትር ብልዩ ቅናሽ ያገኛሉ።
ቅዱስ ጳውሎስ ዕቅበተ እምነትን በአጭር ቃል ሲገልጸው "ወንጌልንም መመከቻና መጽኛ ማድረግ " ይለዋል:: (ፊልጵ. 1:7) አንዲቱ ወንጌል ለተቃዋሚዎች "መመከቻ" ስትሆን በውስጥ ላሉ ምእመናን ደግሞ "መጽኛ" ትሆናለች:: "ለምእመናን ተስፋ ለመ^#ቃን ዘለፋ" እንዲል ትርጓሜው::
የጳውሎስ አቻው ቅዱስ ጴጥሮስ ደግሞ :- "ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመሥጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ" ብሎአል:: ልብ አድርጉ "ለሚሰድቧችሁ" አላለምና እምነታችንን ለሚሳደቡ መልስ አንሠጥም:: ለጥያቄ ግን እንመልሳለን::
ይህንን እውነት ከተረዱ ወንድሞች አንዱ የሆነው የዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው ዳጎስ ያለ ዕቅበተ እምነታዊ መጽሐፍ አቅርቦልናል:: ለራሳችን መጽኛ ለሌላው መመከቻ የሚሆነው መጽሐፉ እጅግ ብዙ ጥያቄዎች በጥንቃቄ የተመለሱበት የተደከመበት ስራ እንደሆነ በወፍ በረር ቅኝቴና መጽሐፉን አይተው አስተያየታቸውን ካሠፈሩ ምስክሮች ተረድቼያለሁ:: በብዙ ድካም የሠራውን መጽሐፍ ከአንድ ኪሎ ሥጋ መሸጫ ባነሰ ዋጋ አበርክቶልናል:: አይለፈን!
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።
ጥቂት የመጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች
ሁ?ከተሰኘው
✍አባታችን አብርሃም ኑሮውን ከእግዚአብሔር ጋር ማድረግ የጀመረው አገሩንና ቤተ ሰዎቹን በተወ ጊዜ ነበር፡፡ አባቶቻችን ሐዋርያት ተመሳሳይ ነገር ነው ያደረጉት፡፡ እነርሱ ሲጠሩ ዓሣ አጥማጆች ሆነው ሳሉ የተዉት መረቦቻቸውንና ታንኳዎቻቸውን ብቻ ሳይሆን ተከትለውትም ሄደዋል፤ማቴ 4፡20እና22፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተናገረው ከሆነማ ያላቸውን ነገር ሁሉ ትተው ነው የከተሉት፤ ማቴ 19፡27፡፡ እናንተስ? ስለ እግዚአብሔር ስትሉ የተዋችሁት ነገር ምንድር ነው? እናንተ ኃጢአተኛ ሕይወታችሁን በመተው ንስሐ ገብታችኋል?...
***
ያዕቆብመልእክት
ከተሰኘው
‹ብዙ ሰዎች እኔን በሀብታም ሰዎች ላይ ያለህ አቋም በጣም ጥብቅ ነው እያሉ ይናገሩኛል፡፡ በእርግጥም እንዲህ በማለታችሁ እውነት ብላችኋል፤ይሁን እንጂ እኔ በሀብታም ሰዎች ላይ ጥብቅ የሆንኩት ገንዘባቸውን ለመሳደቢያ አድርገው ለተጠቀሙበት ሀብታሞች ነው፡፡ እኔ እነርሱን የማጠቃቸው በግል አይደለም፤ነገር ግን የማጠቃው ስስታቸውን ነው፡፡ ........
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
...በተለይ በተለይ በትርጉም ስራ ረገድ ለኛ [ለኢትዮጵያውያን ] አባት ልጁን ለመመገብ እንደሚጨነቅ እና እንደሚፋጠን ኹሉ በልዩ እና በተረዳ እንዲሁም በማይጠገብ መልኩ የሚያዘጋጁልን ፦
#አያሌው ዘኢየሱስን ያቆይልን እያልን ፦
💥አሁንም እነዚህን ሁለት ግሩማን፤ ሐሳቦችን የተሞሉ ፤መጻሕፍት እነኾ ያሉን ሲሆን በግዮን መጻሕፍት ያገኟቸዋል ።
👇ይህ የ fece book ገጻችን ነው ይቀላቀሉን ! https://www.facebook.com/share/15vnjyrzBv/
ለ Telegram በዚህ ይጎብኙን
http://t.me/GhionBookStore1623
ዜና ድጋሚ ኅትመት !
ሳይንስ እና ሃይማኖት
..✍ሳይንስ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን አዕምሮ ተጠቅሞ ያስገኘውና በዚህ ዓለም ያለውን የኑሮ ድካም ማቅለያው የዕውቀት ዘርፍ ሲሆን ሃይማኖት ደግሞ ከአምላኩ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኘው መንገድ ነው። ነገር ግን የሳይንስን ውሱንነት ያልተረዱ ሰዎች ሃይማኖትን በሳይንሳዊ ዕውቀት ለመተንተን ሲሞክሩና ወደ ተሳሳተ ግንዛቤ ሲያመሩ ይስተዋላል። በሌላ መልኩ ደግሞ ሳይንስ ለመንፈሳዊ ሰዎች እርባና የሌለው ነው ብለው የሚያምኑም አሉ።
ይህንን በተመለከተ ለሚነሱ ጥያቄዎችና ፍልስፍናዊ አስተያየቶች፣ ጸሐፊው መምህር ያረጋል አበጋዝ፣ በዚህ መጽሐፉ ከሳይንስና ከሃይማኖት ጋር በተገናኙ ፍልስፍናዊ አስተሳሰቦች ዙሪያ ሰፊ ጥናት በማድረግ ከጥልቅ ትንታኔ ጋር አቅርቦልናል። ስለሆነም መጽሐፉን አንብበን የተሻለ ግንዛቤ እንድናገኝና እንድንጠቀምበት እየጠየቅኩ፣ ለመምህር ያረጋል ዕድሜና ጤናን ለእናንተ ለአንባብያን ደግሞ መልካም ንባብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
ቀሲስ ሰሙ ምትኩ (ፕሮፌሰር)
ቦትስዋና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ
ይህ መንፈሳዊ እና ሳይንሳዊ እሳቤዎችን የተነተነ በግሩማን ሐሳቦች የታጨቀው [የተሞላው] በመምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የቀረበ ጥዑም ማዕድ[መጽሐፍ ] ለ ሁለተኛ ጊዜ የታተመ ሲሆን በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
# ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
፦0912198891
https://t.me/GhionBookStore1623
#ንስሓና_ምጽዋት_ታተመ!
በዚህ መጽሐፍ የተካተቱት ዓሥር ድርሳናት፥ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ በ386 እና በ387 ዓ.ም. በአንጾኪያ ያስተማራቸው ሲኾኑ፥
👉 ኃጥአንም ጻድቃንም ንስሓ እንደሚያሻቸው እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ካለው ወደር የለሽ ፍቅሩ የተነሣ አንድ ዓይነት የንስሓ መንገድ እንዳልሰጠ፣
👉 በዚህ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓምድ ትምህርት በኾነው በንስሓ አማካኝነት ኃጥአን ያሳደፉትን ልጅነታቸውን የሚያድሱበትና ሕይወት ወደ ኾነው ወደ ቅዱስ ቁርባን የሚመልሳቸው መንገድ መኾኑን፣
👉 ወደ ቅዱስ ቁርባን መድረሻ መንገድ ብቻ ሳይኾን ከላይ እንደ ተገለጠው በተለያየ መንገድ ማለትም በጸጸት፥ በምጽዋት፣ በጸሎት፣ በፆም፥ በትሕትና፥ ቅዳሴውንና አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮን በመሳተፍ፥ በአጠቃላይ ምግባር ትሩፋትን በመሥራት ያሸበረቀ ቤተ ክርስቲያናዊ ሕይወትን በመኖር የሚገለጥ ምሥጢር መኾኑን፣
👉 የአምላክን መጠን አለፍ ቸርነት ስጦታ መኾኑን ከብዙ ማሳያዎች ጋር ያስተማረባቸው ናቸው፡፡
መጽሐፉ በ200 ገጾች፣ በሚማርክ ኅትመትና በ300 ብር የሽፋን ዋጋ ለሦስተኛ ጊዜ ታትሞ ለአንባቢያን ቀርቧል።
____
በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ።
💥ሰፌልያ🩸
"ሰፌልያ" የቅዱስ ጳውሎስ ሕይወትን የሚተርክ እስከ ዛሬ ያልሰማናቸውን ዕውቀቶች እየተደመምን የምንጠጣበትና ጽናት የምናግኝበት ልዩ መጽሐፍ ነው።
በሰባኪ ወንጌል ቀሲስ ያሬድ ገ/መድኅን ተደርሶ ለአንባቢያን የቀረበው ይህ አዳዲስ መረጃዎችን የሸከፈው መጽሐፍ፥ የዓለም ብርሃን ንዋይ ኅሩይ ስለ ተባለው የአገልግሎት ውጣ ውረድን የሚዳስስ ሥራ ነው።
በግዮን መጻሕፍት መደብር Ghion Book Store ታገኙታላችሁ።
አድራሻ ምኒልክ አደባባይ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ በምዕራብ በር ማይክሮ ሊንክ እንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኮሌጅ
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
"ብዙ ህዝባችን የሚጠፋው እውቀት ከማጣት ነው!! "
#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ
.....አንተ ሰው! ቊጥር የሌላቸው ክፋቶች ቢኖሩብህም እንኳ በጎ ምግባር በልጅህ ይኖር ዘንድ በማድረግ አካክሰው፡፡ ለክርስቶስ የሚኾን ተሽቀዳዳሚ (ሯጭ) አሳድግ! ወዳጄ ሆይ! እንደዚህ ብዬ ስነግርህ አትፍራ፤ አትሸበርም፡፡ ልጅህ እንዳያገባ አድርገው አላልኩህም፡፡ ወደ ገዳም ወስደህ እንድታመነኩሰው ወይም የብሕትውና ሕይወትን እንዲመራ አድርገው አላልኩህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ይህን አይደለም፡፡ ልጅህ ቢመነኩስ እወድ ነበር፡፡ ብዙዎች ወደዚህ ሕይወት እንዲገቡ የዘወትር ጸሎቴ ነውና፡፡ ነገር ግን የምንኵስና ሕይወት [ሳይጠሩ ከገቡበት] ከባድ ሸክም ስለ ኾነ ሰዎች መነኰሳት ካልኾኑ ብዬ ግድ አልልም፡፡ ለአንተም እንደዚህ በግድ አመንኩሰው አልልህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ለክርስቶስ የሚኾን ተሸቀዳዳሚ ሆነህ አሳድግ ነው፡፡ በዚህ ዓለም አግብቶ፣ ልጆችንም ወልዶ የሚኖር ቢኾንም እንኳን ገና ከሕፃንነቱ አንሥቶ ሰውን የሚያከብር እንዲኾን አድርገህ አሳድገው ነው፡፡
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
#ከኦርቶዶክሳዊ_ቤተሰብ_መጽሐፍ
❝ከ ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅወርቃማ ትምህርቶች አንዱ የሆነውን ይህን መጽሐፍ በግዮን መጻሕፍት የሚያገኙት ሲሆን ሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ ለምትገኙ ውድ አንባቢያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የ delivery
አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ለአንባብያን ተደራሽ እናደርጋለን።❞
📞 ስልክ፦ 0913083816
#ግዮን መጻሕፍት
https://t.me/GhionBookStore1623
…………ለ8ተኛ ጊዜ የታተመ
"እንደ ኦርቶዶክሳውያን ወላጆች፥ ዓላማችን ፍጹማን ወላጆች መኾን አይደለም። ይህ የማይቻል ነውና። ... ልጆች የሚፈልጉት [እና የሚያስፈልጋቸው] እንደ እነርሱ የሚሳሳቱና [ከስሕተታቸው እየተማሩ] የሚያድጉ ወላጆችን ነው።"
#ትንሿ_ቤተክርስቲያን፥ ገጽ 447
ቃና ዘገሊላ መጽሐፍ ለ11ኛ ጊዜ ታተመ።
"የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ሁለትን የመጀመሪያ አንቀጽ መነሻ ያደረገችውና በሰርግ ቤቱ ስም ቃና ዘገሊላ በማለት የተሰየመ ይህ መጽሐፍ፥ እንደ ሰርግ ቤቱ ስድስት ጋኖች በስድስት ምዕራፎች የተከፈለ ነው። ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዝ እንደነበሩት እንደ ቃና ጋኖችም እነዚህ ምዕራፎች እያንዳንዳቸው ሦስት ወይም አራት የንዑስ ርዕስ እንስራን የያዙ ናቸው፡፡ ...
"ይህ መጽሐፍ በስድስቱ ጋኖች /ምዕራፎች/ ውስጥ በቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት ትርጓሜ መነሻነት በሰርግ ቤቱ ውስጥ ጥቂት እንድንቆይ ለማድረግ ይተጋል፡፡ .….
"እንኪያስ እኛም በኄኖክ መሪነት በቃና ዘገሊላ ሰርግ ቤት ውስጥ እንድንመላለስ፣ ከጌታችንና ከሐዋርያቱ ጋር ወደ ሰርግ ቤቱ እንድንገባ፣ ወደ ጓዳ ዘልቀን የወይኑን ማለቅ አስበን እንድንጨነቅ፣ እመቤታችን ስታማልድ ልጇም ሲማለድ እንድናይ፣ ከአገልጋዮቹ ጋር ውኃ ልንቀዳ ወንዝ እንድንወርድ፣ አብረን ውኃውን እስከአፉ ሞልተን ጌታችን የሚያደርገውን እንድንመለከት፣ ከታዳሚዎች ጋር ወይን የሆነውን ውኃ ቀምሰን እንድናደንቅ፣ መልካሙ የወይን ጠጅ ምነው እስካሁን ቆየ? ብለን ከአሳዳሪው ጋር አብረን እንድንቆጭ፣ ከዚያም ከሐዋርያቱ ጋር በስሙ አምነን ከሰርግ ቤቱ እንድንወጣ፣ ከምድራዊው ሰርግ ቤት ወጥተንም ወደ የቤታችን ሳንገባ ወደ ሌላ ሰማያዊ ሰርግ እንድንታደም ይህን ግሩም መጽሐፍ እናንብብ፡፡...
____
በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፎቶችን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኛላችሁ።
ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ።
የቅዱስ ዮሐንስ ምሥክርነት
"እኔስ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ነገር ግን የጫማውን ጠፍር መፍታት የማይገባኝ፣ ከእኔ የሚበረታ ይመጣል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል።"
ሉቃ ፫: ፲፮።
እንኳን ለበዓለ ከተራ ወጥምቀተ እግዚእ አደረሳችሁ❗️❗️❗️
ገድለ አቡነ ጸጋ ዘአብ ወእምነ እግዚእኀረያወገድለ አቡነ ታዴዎስ ጽላልሽ
....ገድላት ኹሉን አቀፍ የመረጃ ምንጮች ናቸው። ዘመን፤ በአንድ አካባቢ፤ በአንድ ተመሳሳይ ሁኔታ የሚጓዙ አለመሆናቸው፤ በተለያዩ የዓለም ክፍል በተለያዩ ዘመናትና ጊዜያት የተነሡ የቅዱሳንን ሕይወት የተመለከቱ፤ ከምእመናን እስከ መዐርገ ጵጵስና ድረስ በተራ ዜግነት ከተሰለፉት እስከ ንጉሥነትና ንግሥትነት ደረጃ እስከ ደረሱት ድረስ ምእመናንንና ምእመናትን በእኩልነት የያዘ በመኾኑ ከሃይማኖት ጥቅሙ በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሰዎችን እኩልነት በማሳየቱ የበለጠ አጎልቶ ይሳያል።
❞ስለዚኽ ይኸ የካህኑ ጸጋ ዘአብ፣የብፅዕት እግዚእ ኀረያ እና የአቡነ ታዴዎስ ገድል የነፍስና የሥጋ በረከት የምንቀበልበት፤ ኹሉን አቀፍ መረጃ የምናገኝበት በመኾኑ በ፯ቱ ዕለታት በመክፈል በግዕዝና በአማርኛ በመተርጎም ቀርቧል።
❞ይኸም ቅዱሳኑ በሕይወተ ሥጋ እያሉም ኾነ ከዕረፍታቸው በኋላ በዐጸደ ነፍስ ሳሉ ያደረጓቸውን ልዩ ልዩ ድንቅ ተኣምራትን መልክዐቸውንም አካቶ የያዘ የካህኑ ጸጋ ዘአብን፣ የብፅዕት እግዚእ ኀረያንና አቡነ ታዴዎስን ዝክረ ስም የሚናገር የምስጋናጸሎት ስለኾነ በዚኸ የጸሎት መጽሐፍ ተጠቅመን በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ እናገኝ ዘንድ ይህን ገድል ኢቲሳ ደብረ ጽላልሽ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም እነሆ ይለናል ።
❞ይኽን የቅዱሳን ተጋድሎ እና ምስጋና የያዘ ገድል በግዮን መጻሕፍት የሚያገኙት ሲሆን በሀገር ውስጥ እንዲሁም ከሀገር ውጭ ለምትገኙ አንባብያን በDHLእና በEMS በመላክ የ Delivery አገልግሎት በመስጠት ተደራሽ እናደርጋለን።
📞 ስልክ ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
