The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
Відкрити в Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
Показати більше3 316
Підписники
+724 години
+267 днів
+11030 день
Архів дописів
የቄስ አለሙ ሼጣ የሽኝት ሥነ-ሥርዓት ዛሬ አምስት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን ወዳጅ ዘመዶች፣ የአገልግሎት ባልደረቦች፣ የቤተ ክርስቲያን መሪዎችና ምዕመናን በተገኙበት ተከናውኗል።
በሽኝት ሥነ-ስርዓቱም ላይ ቤተ ክርስቲያናቸው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት፣ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስትያናት ካውንስል፣ ወዳጅ ዘመዶች፣ በርካታ ሀገር አቀፍና አለማቀፍ የሚስዮን ተቋማት ሀዘናቸውን ገልጠው የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል።
"...የጻድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል።" መዝሙር 112:6
*ዜና እረፍት*
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ለበርካታ አመታት በተለያዬ ከፍተኛ የአመራር ሀላፊነት ሲያገለግሉ የቆዩትን የቄስ አለሙ ሼጣን ዜና እረፍት በታላቅ ሀዘን ሰምተናል፡፡
ቄስ አለሙ ሼጣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የቀድሞ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ፕሬዚደንት፣ የደቡብ ሲኖዶስ መስራችና የመጀመሪያ ፕሬዚደንት በመሆን እና በመካነ ኢየሱስ ሴሚናሪዮም ለበርካታ አመታት በማስተማር፤ በመቀጠልም በቤተክርስቲያኒቱ ዋናው ጽ/ቤት የወንጌል እና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር በመሆንም ቤተክርስቲያኒቱን በትጋትና በታማኝነት አገልግለዋል::
ከዚህም በተጨማሪ ቄስ አለሙ ሼጣ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረትን ከመጋቢት 1999 ዓ.ም እስከ ኅዳር 2008 ዓ.ም በዋና ጸሐፊነት/ፕረዝደንትነት አገልግለዋል::
የቄስ አለሙ ሼጣ አስከሬን ሽኝት ረቡዕ መስከረም 30 ቀን 2016ዓ.ም አምስት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን በ5ሰዓት ሥርዓተ ጸሎት ከተደረገ በኋላ የቀብራቸው ሥነ ሥርዓት በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ከቀኑ በ7:30 ሰዓት ይፈጸማል፡፡
ለባለቤታቸው፣ ለልጆቻቸው፣ ለመላው ቤተሰቦቻቸው እና ምዕመናን ሁሉ እግዚአብሔር መፅናናትን እንዲሰጠን ጸሎታችን ነው።
የመሪዎች የቤተሰብ አገልግሎት ስልጠና በጉዲና ቱምሳ ሁለንተናዊ የስልጠና ማዕከል በመካሄድ ላይ ይገኛል
* * * *
ስልጠናው የሚሲዮን እና ቲኦሎጂ ዲፓርትመንት ከኮንኮርዲያ የቤተሰብ ማዕክል ጋር በጋራ ያዘጋጀው ሲሆን በስልጠናውም ላይ የሲኖዶስ ፕሬዚዳንቶች፣ የሚሲዮን እና ቲኦሎጂ ዲፓርትመንት ዳይሬክተሮች፣ የሴቶች እና የወጣቶች አገልግሎት መሪዎች እየተካፈሉበት ይገኛል።
ስልጠናው አዳዲስ እና ነባር የሲኖዶስ መሪዎችን በትዳርና ቤተሰብ ህይወት ትምህርት እና በቤተ ክርስቲያን ሊኖር ስለሚገባው የቤተሰብ አገልግሎት ግንዛቤተ እንደሚያስጨብጥ ይጠበቃል።
- - - - - - - -
Leaders’ Training in Family ministry is in session at GTWTC
* * * *
The training was organized by Department of Mission and Theology (DMT) in collaboration with Concordia Center for the Family. Synod presidents, DMT directors, Women and Children ministry leaders are attending the training.
The training is expected to give orientation on marriage and family life education and Family ministry in the church.
#Ergaa_atattamaa
Hubachiisa WKWW Mekana Yeesus Ityophiyaa irraa
Walga’iin Kawunsilii (Council) 19ffaan Waldaa Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa Mekaana Yesuus Itiyoophiyaa akka lakkoofsa Etiyoophiyaatti Fulbaana 22—24/2016tti geggeefamee jira. Kaawunsilichi kadhataa fi barsiisa dubbii Waaqayyootiin fuula Waaqayyoo erga turee booda, sirnaan banamee hojii isaa kan itti fufe yoo ta’u, guyyoota hafanitti Haasaa Qajeelfamaa (Keynote Speech) Prezidaantii Waldattiitiin dhi’aate, akkasumas Gabaasa hojii Barreessaa Duree Waldattiitii fi gabaasawwan qaamolii adda addattiin dhi’attan irratti mari’achuudhaan milkiin xumureera.
Qabxiiwwan gurguddaa Haasaa Qajeelfamaa Prezidaantii Waldattiitiin dhi’aatan keessaa inni tokko “Global Mission Strategy” yaada jedhu yoo ta’u akkaataa hojii misiyoonummaa “Europe fi America” keessatti geggeessuun danda’amuu kan ilaallatu ture. Kuni caalaadhumatti Waldoota Kiristiyaanaa fi wangeelaa biyya keenyaan ga’anii hundeefamuu Mekaana Yesuus keessatte shoora olaanaa taphatan, amma garuu ofumaafuu dogoggora keessa galanii jirani baraaruudhaaf (Rescue Mission Strategy) karaa danda’amu irratti mari’achuu ilaallata. Yaadni isaa waggoota kudha tokko dura kaawunsilli 6ffaa Gimbiitti geggeeffame irratti, Waldootii kanaa wajjin hariiroon jiru akka addaan citu murtoo godhameen wal-qabatee yaada kaa’ameedha. Haa ta’u malee murtii “Rescue Mission Strategy” jedhu kana hojiitti jijjiiruudhaaf amma ammaatti tarsiimoon kaa’ame waan hin jirreef, dhimmi isaa xiyyeeffannaa akka argatuuf. Sababni isaa immoo haalli Waldootiin Kiristiyaanaa kun amma keessa jiran kan duraanii caalaa gaddisiisaa ta’aa waan jiruuf.
Kana irratti Kaawunsilichi mari’atte tarsiimoo “Global Mission Strategy” jedhuun sochiin ergaa Wangeelaa adda ta’e karaa itti jalqabamu irratti qophiin akka godhamu qixa kaa’eera. Haa ta’u iyyuu malee akeeki kun Waldaan Kiristiyaanaa keenya dhimma kana ilaalchisee murtii kanaan dura dabarsitee fi ejjennoo “Theology” qabdu irraa bifa kamiin ilee utuu hin mitiqin hojii Misiyoonummaa biyyoota kan keeessatti hojechuun yoo amansiisaa ta’e qofa kan itti adeemamu ta’a.
Kuni akkasiin utuu jiruu jidduu kana “Waldaan Makaana Yesuus Waldoota fuudhaa fi heeruma saal-fakkii (Same sex marriage) deggeran wajjin hariiroo ishee haaressuuf murteessite” jedhu oduun dhugaa irraa fagaate tamsa’aa akka juru hubannee jirra. Namoonni oduu dogoggorsaa kana tamsaasaa jiran kaayyoon isaanii maal akka ta’e hin beekamu. Oduun namni kun facaasaa jiru garuu kallattii Kaawunilichi irratti mari’atee fi murteesse irraa raawwatee kan fagaate ta’uu isaa hubachiisuu jaallanna.
Mula’tni “Rescue Mission” akka milkaa’uuf haa kadhatnu; Waaqayyoof wanti dadhabamu hin jiru. Hinaaffaa Wangeelaa kan qaban hunduu itti hirmaachuuf haa qophaa’an.
#Ergaa_kana_namoota_biraaf_dabarsa!
#EECMY
#19thCouncli
#አስቸካይ_መልዕክት
ከኢት.ወ.ቤ.ክ መካነ ኢየሱስ የተሰጠ ማብራሪያ
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 19ኛ ካውንስል ዓመታዊ ስብሰባ ከመስከረም 22 ቀን 2015 ዓ/ም እስከ መስከረም 24 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ ተካህዷል፡፡ ካውንስሉ የመጀመሪያውን ቀን እስከ ሰባት ሰዓት ድረስ ያለውን ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማትና በጸሎት በእግዚአብሔር ፊት በመቆየት ያሳለፈ ሲሆን የቀሩትን ቀናት አቅጣጫ ጠቋሚ የሆነውን የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚደንት መርሐ ንግግር፣ በጠቅላይ ጸሐፊው ተዘጋጅቶ የቀረበውን የቤተ ክርስቲያኒቱን የአንድ ዓመት የሥራ ክንውን ሪፖርት እንዲሁም የተለያዩ ቦርዶችና ኮሚሲዮኖች ሪፖርቶችን ሰምቶ በርካታ ውሳኔዎችን አስተላልፎ ተነስቷል፡፡
በቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚደንት በቀረበው መርሐ ንግግር ከተካተቱት ሃሳቦች መካከል አንዱና ካውንስሉ አጽንዖት ሰጥቶ በመወያየት አቅጣጫ ያስቀመጠለት፤ በኃይማኖት ለዘብተኝነትና በሰኪዩላሪዝም ተጽዕኖ ሥር የወደቁት በአውሮፓና በአሜሪካ አገሮች የሚኖሩ የወንጌል አጋሮቻችንን በክርስቶስ ወንጌል መታደግ ስለሚቻልበት መንገድ ነበር፡፡ ይህም ከአስራ አንድ ዓመታት በፊት፤ በግምቢ በተካሄደው 6ኛው የካውንስል ስብሰባ፤ ከስዊድን ቤተ ክርስቲያንና ከአሜሪካ ሉተራን ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ጋር የነበረው ግኑኝነት እንዲቋረጥ ሲወስን እነዚህን አብያተ ክርስቲያናት ከዚህ ህይወት ለመታደግ የሚያስችል ሚሲዮናዊ ስልት (Rescue Mission Strategy) እንዲቀየስ አብሮ ወስኖ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ውሳኔውን ለመተግበር እስካሁን የተደረገ እንቅስቃሴ አልነበረም፡፡ ካውንስሉም በዚህ ጉዳይ ላይ በጥንቃቄ በመምከር ቤተ ክርስቲያኒቱ ሚሲዮናዊት በመሆኗ፤ ሥነ መለኮታዊ ማንነቷና ደንቧ እንዲሁም ከዚህ ቀደም ግብረ ሰዶማዊነትንና የተመሳሳይ ጾታን አስመልክቶ የወሰነቻቸው ቋሚ ሥነ መለኮታዊ ውሳኔዎቿ ሳይሸራረፉ ‹‹ግሎባል ሚሲዮናዊ ስልት›› (Global Mission Strategy ) ተቀይሶ ስማቸው ከላይ በተጠቀሰውና በሌሎችም ፍላጎት ባለባቸው የዓለማችን ክፍሎች የመታደግ ሚሲዮናዊነት አገልግሎት የሚካሄድበት ስልት በጥንቃቄ እንዲቀየስና ምክክሮችም እንዲደረጉ ለጥናት መርቷል፡፡
ይሁን እንጂ ካውንስሉ ቀደም ሲል የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን ከሚደግፉ አጋሮቿ ጋር ቤተ ክርስቲያኒቱ አቋርጣ የነበረውን ግንኙነት ለማደስ ወስኗል የሚል እንድምታ ያለው ሃሳብ ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲዘዋወር ተመልክተናል፡፡ ይህንን ሃሳብ እያሰራጩ ያሉት ግለሰቦች ዓላማ ምን እንደሆነ ባይገባንም መልዕክቱ የውይይቱን መነሻ ምክንያትም (Intention) ሆነ ካውንስሉ የተስማማበትን የመጨረሻ ውሳኔ ያላገናዘበ፣ ከእውነት የራቀና ፈጽሞ ቤተ ክርስቲያኒቱን የማይመለከት መሆኑን እንገልጻለን፡፡
የመታደግ ሚሲዮናዊ (Rescue Mission strategy) ራዕይ እንዲሳካ እንጸልይ፡፡ ለእግዚአብሔር የሚሳነው የለምና የወንጌል ቅናት ያላቸው ሁሉ ተሳትፎ ለማድረግ ይዘጋጁ፡፡
#መልዕክቱን_ለሌሎች_ያጋሩ!
#EECMY
#19thCouncil
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
