The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
Відкрити в Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
Показати більше3 294
Підписники
Немає даних24 години
+127 днів
+9230 день
Архів дописів
#የመካኒሳ_መካነ_ኢየሱስ_ማህበረ_ምዕመናን_ሥርዓተ_አምልኮን_እንዲያግዙ_በከፍተኛ_ወጪ_ከባህር_ማዶ_የመጡ_መሳሪያዎችን_አስመርቆ_ለአገልግሎት_አዋለ
* * * * * *
በመዲናችን አዲስ አበባ ላለፉት 50 ዓመታትና ከዚያም በላይ የወንጌልና ማህበራዊ አገልግሎቶችን በመሥራት ላይ ከሚገኙ ቀደምት የቤተ ክርስቲያኒቱ ማህራነ ምዕመናን መካከል የመካኒሳ ማ/ም ተጠቃሽ ነው።
ማህበሩም ለምዕመናን አምልኮ አመቺ እንዲሆን መደበኛውን የአምልኮ አዳራሽ አድሶ ለአገልግሎት ክፍት ካደረገ ጥቂት ወራቶች መቆጠራቸው የሚታወስ ነው።
እድሳቱንም ተከትሎ በምዕመናን፣ በአመራሮች እና ለዚሁ አገልግሎት በተቋቋመው ኮሚቴ በተሰራው ሰፊ ስራ እግዚአብሔር መከናወንን ሰጥቷቸው፤ ሥርዓተ አምልኮን የሚያግዙ መሳሪያዎች በከፍተኛ ወጪ መጥተው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል።
ከነዚህም ቴክኖሎጂዎች፤ በድምሩ 20 ካሬ የሚሆኑ ሁለት ሰፋፊ እስክሪኖች፣ የሳውንድ ሲስተም፣ አገልግሎቶችን በምስል እና በድምጽ ለመቅረፅ እንዲሁም በቀጥታ ለማሰራጨት የሚያግዙ መሳሪያዎች ይጠቀሱበታል።
ባሳለፍነውም ዕሁድ በመደበኛ የአምልኮ ፕሮግራም እነዚህን መሳሪዎች የማህበሩ ምዕመናን፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች እና አገልጋዮች በተገኙበት በታላቅ ምስጋና ተመርቀው ለአገልግሎት ውለዋል።
መሳዎቹም በማኅበሩ ከሚሰጡት አገልግሎት ባሻገር ለወደፊት በኪራይ መልክ ለገቢ ማስገኛ እንደሚውሉ በአዕለቱ የተጠቀሰ ሲሆን አገልግሎቱን ላስተባበሩ አገልጋዮች እውቅና ተሰጥቷል።
ምስል: መካኒሳ መካነ ኢየሱስ ማኅበረ ምእመናን ሚድያ አገልግሎት
#ዛሬ_በእንጦጦ_ማህበረ_ምዕመናን_ለ4_አገልጋዮች_የቅስና_ሹመት_ተሰጠ
* * * * * *
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በአዲስ አበባ ሲኖዶስ ለቃሉ እና ቅዱሳት ሚስጥራት እንዲያግዝ ዛሬ ሚያዝያ 19 ቀን 2017 ዓ/ም ለ4 አገልጋዮች የቅስና ሃላፊነት ተሰጥቷል።
የቅስና ሃላፊነቱን የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዘዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የሰጡ ሲሆን አገልጋዮቹ በቤተ ክርስቲያኒቱ አሰራር አስፈላስጊውን ዝግጅት ያጠናቀቁ መሆኑን በመግለጽ፤ ማወቅ የሚገናቸውን ብዙ ነገር ያወቁ፤ ገናም ግን እያደጉ የሚሄዱ ናቸው ብለዋል።
በዛሬውም እለት በቡሌ ሆራ ስለሚካሄደው የቅስና ሃላፊነት የመስጠት መርሃ ግብር በመጥቀስ በመካነ ኢየሱስ እግዚአብሔር ብዙ በረከት እያደረገ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
በስፍራውም የሲኖዶሱ አመራሮች፣ አገልጋዮች እና የቀደሙ ቀሳውስት የተገኙ ሲሆን ለእጩ ቀሳውስቱ እጅ በመጫን ፀልየዋል።
ለመከሩ አገልግሎት እግዚአብሔር ብዙ አገልጋዮችን እያበዛልን ስለሆነ የተመሰገነ ይሁን።
ምስል፡ አገልጋይ ግዛቸው አይካ
#ለ17_አገልጋዮች_የቅስና_ሹመት_ተሰጠ
* * * * * *
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ለ17 አገልጋዮች የቅስና ሹመት ዛሬ ሚያዝያ 19 ቀን 2017 ዓ/ም ተሰጥቷል።
አገልጋዮቹም የቅስና ሃላፊነታቸውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ታሪኩ ቶለሳ የተቀበሉ ሲሆን ምክትል ፕሬዚዳንቱ አገልጋዮቹ ከዚህ በፊት በተቀበሉት ተልዕኮ ላይ ተጨምሮ የተሰጣቸው መሆኑን ገልፀዋል።
የሲዶሱም ፕሬዚዳንት ቄስ ደስታ ሀሮ ብዙ ከተቀበለ ሰው ብዙ እንደሚጠበቅ በማስታወስ ሀላፊነቱን የተቀበሉን አገልጋዮች ምዕመናን በፀሎት እና በምክር እንዲደግፏቸው አሳስበዋል።
ሚያዝያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም፤ ቡሌ ሆራ
ምስልና ዘገባውን ከሲኖዶሱ የማህበራዊ ሚድያ አገኘነው።
_ _ _ _ _ _
Tajaajiltoota 17f muudamni lubummaa kenname
* * * * * *
WWWMYI Sinoodoosii kibba Itoophiyaatti tajaajiltoota 17f guyyaa har'aa, Ebla 19, 2017 muudamni lubummaa kennamee jira.
Tajaajiltootni kunneenis muudama lubummaa isaanii Itti Aanaa pirezdaantii waldaa Worra Wongeelaa Mekaanee Yesuusii Itoophiyaa Luba Dr Taarikuu Tolosaa irraa fudhatanii jiru. Lubni Dr. Taarikuunis Tajaailtoonni kun ergama duraan qaban irratti dabalataan kan itti kenname ta'uu himaniiru.
Pirezdaantin sinoodoosichaa lubni Dastaa Haroo nama baayyeen itti kenname irraa baayyeen akka eegamu yaadachiisuun amantoonni tajaajiltoota itti gaafatamummaa fudhatan kana gorsaa fi kadhannaadhaan akka deeggaran hubachiisanii jiru.
Eebla 19/8/2017 SKI, Bulee Horaa
Gabaasnii fi suuraan midiyaa hawaasaa sinoodoosichaa irraa kana fudhatamee dha.
የአራተኛው ዓመት "የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንት" ብሔራዊ ክብረ በዓል ቅስቀሳ እና ግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በቢሾፍቱ ከተማ ተካሄደ
* * * * * *
ቤተ ክርስቲያኒቱ ስለምታካሂዳቸው የቋንቋ ልማት፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉምና ቅዱሳት መጽሐፍ አጠቃቀም አገልግሎቶች ምዕመናን ግንዛቤ እንዲኖራቸው እና ለአገልግሎቱ መስፋፋትና ተደራሽነች የግላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ታስቦ የሰኔ ወር ሁለተኛ ሳምንት በቤተ ክርስቲያኒቱ የጊዜ መቁጠሪያ ሰሌዳ "የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንት" ሆኖ እንከበር ተቀምጧል።
የዘንድሮውም ዓመት ክብረ በዓል በአራቱም የሀገሪቱ መአዘናት በሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅሮች፣ ተቋማት ፣ ሴሚናሪዎች እና ማኀበራነ ምዕመናን "ሁሉም ለመጽሐፍ ቅዱስ" በሚል መሪ ቃል ከሰኔ 9-15 ቀን 2017 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ይከበራል።
የዚህም ክብረ በዓል አካል በመሆን በቢሾፍቱ ከተማ ልዩ ሴሚናር፣ የደም ልገሳ፣ የከተማ ጽዳት እና የጎዳና ላይ ሩጫ ከሰኔ 13-14 እንዲካሄ ተወስኖ ዝግጅቶች ተጀምረዋል። ለበዓሉም ስኬታማነት በከተማው እና በአከባቢው የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሰበኮችና ከ100 በላይ የሚቆጠሩ ማኀበራነ ምዕመናን የዝግጅቱ ባለቤት ሆነው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ይጠበቃል። ለዚሁ አላማ የቤተ ክርስቲያኒቱ የቅዱሳት መጽሐፍት አጠቃቀም ብሔራዊ አስተባባሪ የሆኑት ቄስ አለሙ ቡሳዋ በገላን በአደአ ሰበካ ከ28 ማኀበራነ ምዕመናን ለመጡ አገልጋዮችና ተወካዮች ገለፃ አድርገዋል።
አገልጋዮቹም በተለዩት መርሃ ግብሮች ምዕመናንን አሳትፈው ለመካፈል ያላቸውን ተነሳሽነት የገለፁ ሲሆን የዚሁ አይነት ተመሳሳይ ቅስቀሳዎች በሌሎች ሰበኮች እንደሚቀጥል አገልጋይ ቄስ አለሙ ገልጸዋል።
- - - - - - - - -
The fourth year national Bible Week celebration awareness raising and mobilization program was held at Bishoftu city.
* * * * * *
For giving awareness and increase engagements of members for the expansion and sustainability of the Church’s language development, Bible translation, and scripture engagement ministers, the third week of June is dedicated as a "Bible Week" on the church's calendar.
This year's celebration will be held colorfully within the structure of the church, institutions, seminaries, and congregations in four directions across the country, under the overarching theme "All for the Bible" from June 16-22.
As part of the celebration; a seminar, blood donation, city cleaning, and street running are organized at the city of Bishoftu, from 21-22 June 2024. The church’s national coordinator for Scripture engagement ministry, Rev. Alemu Busawa briefed ministers and representatives from the 28 congregations of the Gelan Ada Parishe. On the celebration, parishes in and around the city and the congregations that count more than 100 are expected to own and participate.
Following the mobilization session, the ministers have expressed their commitment to mobilize and engage with members of their congregations on the celebration. This kind of session will also take place in other parishes, said Rev. Alemu.
_ _ _ _ _ _
Telegram - t.me/EECMYeth
YouTube News - https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=sKYiY4tgy3n6lErq
YouTube Teaching - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=Flw2QQIBv5GDGUZL
Young missionaries from the Norwegian Lutheran Mission visited the Church's central office.
* *
After their two weeks visit in different part of the country, the missionaries were in preparation to return back when they visited the Church’s central office. During the visit, the president of the Church, Rev. Dr. Yonas Yigezu welcomed the young missionaries at his office. Following a brief conversation about their time here, the President prayed for the missionaries' safe return and a ministry ahead of them.
The director for the Church’s Children and Youth Ministry, Mr. Wondmagegn Udessa presented about the background establishment history and current missial and development works of the Church. He also shared the experience of his department, from the accomplishments obtained as a result of statistical approaches to address children and youth of the Church.
The Norwegian Lutheran Mission is one of the leading mission organizations within the nation and strong mission partners of the Church with active engagement since 1948.
_ _ _ _ _ _
Telegram - t.me/EECMYeth
YouTube News - https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=sKYiY4tgy3n6lErq
YouTube Teaching - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=Flw2QQIBv5GDGUZL
ከኖርዌጂያን ሉተራን ሚስዮን (Norwegian Lutheran Mission) የመጡ ወጣት ሚስዮናዊያን የቤተ ክርስቲያኒቱን ዋና ጽሕፈት ቤት ጎበኙ
* *
በኢትዮጵያ የነበራቸውን የሁለት ሳምንት ቆይታ አጠናቀው ወደ ሀገራቸው ለመመለስ በዝግጅት ላይ የነበሩት ሚስዮናዊያኑ ዛሬ ማለዳ በቤተ ተክርስቲያኒቱ ዋና ጽሕፈት ቤተ ለጉብኝት ተገኝተው ነበር። በጉብኝታቸው ወቅት የቤተ ክርስቲያኑቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ወጣቶቹን በቢሯቸው ተቀብለው ስለ ቆይታቸው በመጠየቅ ወደ ሀገራቸው ስለ ሚያደርጉት ጉዞና ስለ አገልግሎታቸው ፀሎት አድርገውላቸዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ወንድማገኝ ኡዴሳ ለወጣቶቹ ስለ ኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ምስረታ፣ ታሪክና አሁናዊ የወንጌል እና የልማት እንቅስቃሴ ገለጻ አድርገዋል። አያይዘውም በመምሪያው በኩል በልጆችና በወጣቶች አገልግሎት ዙሪያ በስልታዊ መንገድ ተቀርጸው እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እና መልካም ተሞክሮዎችን አካፍለዋል።
የኖርዌጂያን ሉተራን ሚስዮን በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የወንጌል አገልግሎት በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱ የሚስዮን ተቋማት ውስጥ አንዷ ስትሆን ከ1948እኤአ ጀምሮ ከቤተክርስቲያኒቱ ጋር በሁለንተናዊ አገልግሎት አብሮ እየሰራች ያለች ከቀደምት እና መስራች የሚስዮን ተቋማት አንዷ ናት፡፡
_ _ _
Dargaggoonni Dhaabbata Misiyoonii Lutaraanii Noorweey irraa dhufan Waajjira Muummee WKWWMYI Daawwatan
* *
Turtii torbee lamaa Itoophiyaa keessa turan xumuranii gara biyyaatti deebi'uuf qophaa'aa kan turan misiyoononni dargaggootaa kunneen ganama har'aa daawwannaadhaaf waajjira muummee waldichaatti argamaniiru. Yeroo daawwannaa isaaniitti pirezidaantiin WKWWMYI Lubni Dr. Yoonaas Yiggazuu dargaggoota kana waajjira isaanii keessatti simachuun waa’ee turtii isaanii gaafachuun, waa’ee imala gara biyya isaaniitti godhanii fi tajaajila isaaniitiif kadhannaa isaaniif godhaniiru.
Daarektarri Qajeelcha Tajaajila Ijoollee fi Dargaggootaa WKWWMYI Wondmagegn Udessa waa'ee hundeeffama, seenaa, fi sochii Wangeelaa fi misoomaa WKWWMYI yeroo ammaa dargaggootaaf ibsa kennaniiru. Kana malees hojii fi muuxannoo gaggaarii gama tajaajila ijoollee fi dargaggootaatiin bifa tarsiimawaa ta'een irratti hojjatamaa jiru qoodaniiru.
Dhaabbatni Miisiyoonii Lutaraanii Noorweey, dhaabbata miisiyoonotaa kan jalqabaa fi hundeessitoota waldattii keessaa tokko yoo ta’u, bara 1948 irraa eegalee tajaajila hundagaleessa irratti WKWWMYI waliin hojjechaa jira.
_ _ _ _ _ _
Telegram - t.me/EECMYeth
YouTube News - https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=sKYiY4tgy3n6lErq
YouTube Teaching - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=Flw2QQIBv5GDGUZL
_ _ _
Dargaggoonni Dhaabbata Misiyoonii Lutaraanii Noorweey irraa dhufan Waajjira Muummee WKWWMYI Daawwatan
* *
Turtii torbee lamaa Itoophiyaa keessa turan xumuranii gara biyyaatti deebi'uuf qophaa'aa kan turan misiyoononni dargaggootaa kunneen ganama har'aa daawwannaadhaaf waajjira muummee waldichaatti argamaniiru. Yeroo daawwannaa isaaniitti pirezidaantiin WKWWMYI Lubni Dr. Yoonaas Yiggazuu dargaggoota kana waajjira isaanii keessatti simachuun waa’ee turtii isaanii gaafachuun, waa’ee imala gara biyya isaaniitti godhanii fi tajaajila isaaniitiif kadhannaa isaaniif godhaniiru.
Daarektarri Qajeelcha Tajaajila Ijoollee fi Dargaggootaa WKWWMYI Wondmagegn Udessa waa'ee hundeeffama, seenaa, fi sochii Wangeelaa fi misoomaa WKWWMYI yeroo ammaa dargaggootaaf ibsa kennaniiru. Kana malees hojii fi muuxannoo gaggaarii gama tajaajila ijoollee fi dargaggootaatiin bifa tarsiimawaa ta'een irratti hojjatamaa jiru qoodaniiru.
Dhaabbatni Miisiyoonii Lutaraanii Noorweey, dhaabbata miisiyoonotaa kan jalqabaa fi hundeessitoota waldattii keessaa tokko yoo ta’u, bara 1948 irraa eegalee tajaajila hundagaleessa irratti WKWWMYI waliin hojjechaa jira.
+2
ቄስ ዶ/ር ዩናስ ይገዙ በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት(ፖፕ) ፍራንቼስኮስ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ኀዘን ገለጹ
* *
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ በሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ኀዘን ለኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብጽዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ በላኩት የኀዘን መግለጫ፤ ገልጸዋል።
በመልዕክታቸው የቅዱስ አባትነታቸው ሞት ለመላው የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እና ለመላው ዓለም ትልቅ ጉድለት መሆኑን ገልፀው፤ በቃልና በተግባር ለርህራሄ፣ ለትህትና፣ ለሰላማዊ ንግግና እና የተገለሉትን ሁሉ ለመንከባከብ በአገልግሎት ዘመናቸው ያሳዩትን ያለሰለሰ ትጋት አስታውሰዋል።
እንዲሁም ለአለም አብያተ ክርስቲያናት ስላሳዩት አባትነት የዚህ ሀዘን ተካፈይ መሆናቸውን ገልፀዋል።
_ _ _ _ _ _
Telegram - t.me/EECMYeth
YouTube News - https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=sKYiY4tgy3n6lErq
YouTube Teaching - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=Flw2QQIBv5GDGUZL
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
