ru
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

Открыть в Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

Больше
3 297
Подписчики
Нет данных24 часа
+127 дней
+9230 день
Архив постов
#Waldaan_Warra_Wangeela__Makaana_Yesuus_ Itiyoophiyaa_ Hawaasa _Misiyooni_Addunyaalessaa_sinoodosota_12_Kilaastara_Lixaatti_argamaniif_leenjii_guyyaa_lamaa_kenneera. Leenjichi Magaalaa Gimbiitti kan gaggeeffame yoo ta’u, pireezidaantotaa fi bakka bu’oonni tajaajila misiyooni irratti hirmaataniiru. Tajaajilaan Hawaasicha obbo Kasaahun Nigaatu fi Lubni Addisuu Malkaa leenjicha kennaniiru.

#የኢትዮጵያ_ወንጌላዊት_ቤተ_ክርስቲያን_መካነ_ኢየሱስየዓለም_አቀፍ_ሚስዮን_ማኅበር_በምዕራብ_ክላስተር_ለሚገኙ_12_ሲኖዶሶች_የሁለት_ቀናት_ስልጠና_ሰጠ። በስልጠናውም በጊምቢ ሲኖዶስ የተካሄደ ሲሆን ፕሬዚደንቶች እና የሚስዮን አገልግሎት ተወካዮች ተካፍለውበታል። የማኅበሩም አገልጋይ ካሳሁን ንጋቱና ቄስ አዲሱ መልካ ስልጠናውን ሰጥተዋል፡፡ _ _ _ _ _ _ ለተጨማሪ የቤተ ክርስቲያኒቱ መረጃ:- Telegram - t.me/EECMYeth YouTube News - https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=sKYiY4tgy3n6lErq YouTube Teaching - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=Flw2QQIBv5GDGUZL

#ለማዕከላዊ_ደቡብ_ኢትዮጵያ_ቤቴል_ሲኖዶስ_መሪዎች_እና_የልጆችና_ወጣቶች_አገልጋዮች_ስልጠና_ተሰጠ * * * * * * ልጆች እና ወጣቶች በሁለንተዊ መልኩ ታንጸው እንዲያድጉ የሚረዳ ስልጠና ለማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ቤቴል ሲኖዶስ አገልጋዮች በመምሪያው የወጣቶች አገልግሎት ክፍል አስተባባሪ አቶ ጋዲሳ ረጋሳ ተሰጥተዋል። ስልጠናውም ከሲኖዶሱ ጋር በትብብር የተካሄደ ሲሆን የሲኖዶሱ መሪዎች፤ ከፕሪስፕቴሪዎችና ማኀበራነ ምዕመናን የተወጣጡ የልጆች እና ወጣቶች መሪዎችና አገልጋዮች እንዲሁም ወንጌላዊያንና ቀሳውስት ተሳትፈውበታል። የሲኖዶሱ ፕሬዚዳንት ቄስ አዘነበ ዴሰኖ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ስልጠናው የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎትን ጊዜው በሚፈልግ መልኩ ለማሳደግ አስፈላጊ እና ወቅቱን ያገናዘበ መሆኑን ገልጸዋል። ሰልጣኞችም የወሰዱት ስልጠና ወደ ተግባር መቀየር እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው አሳስበዋል:: ለተቀሩት ሲኖዶሶችም ተመሳሳይ ስልጠና ከሲኖዶሶች ጋር በመተባበር እንደሚሰጡ መምሪያው ገልጿል። _ _ _ _ _ _ ለተጨማሪ የቤተ ክርስቲያኒቱ መረጃ:- Telegram - t.me/EECMYeth YouTube News - https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=sKYiY4tgy3n6lErq YouTube Teaching - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=Flw2QQIBv5GDGUZL

#የመካኒሳ_መካነ_ኢየሱስ_ማህበረ_ምዕመናን_ሥርዓተ_አምልኮን_እንዲያግዙ_በከፍተኛ_ወጪ_ከባህር_ማዶ_የመጡ_መሳሪያዎችን_አስመርቆ_ለአገልግሎት_አዋለ * * * * * * በመዲናችን አዲስ አበባ ላለፉት 50 ዓመታትና ከዚያም በላይ የወንጌልና ማህበራዊ አገልግሎቶችን በመሥራት ላይ ከሚገኙ ቀደምት የቤተ ክርስቲያኒቱ ማህራነ ምዕመናን መካከል የመካኒሳ ማ/ም ተጠቃሽ ነው። ማህበሩም ለምዕመናን አምልኮ አመቺ እንዲሆን መደበኛውን የአምልኮ አዳራሽ አድሶ ለአገልግሎት ክፍት ካደረገ ጥቂት ወራቶች መቆጠራቸው የሚታወስ ነው። እድሳቱንም ተከትሎ በምዕመናን፣ በአመራሮች እና ለዚሁ አገልግሎት በተቋቋመው ኮሚቴ በተሰራው ሰፊ ስራ እግዚአብሔር መከናወንን ሰጥቷቸው፤ ሥርዓተ አምልኮን የሚያግዙ መሳሪያዎች በከፍተኛ ወጪ መጥተው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል። ከነዚህም ቴክኖሎጂዎች፤ በድምሩ 20 ካሬ የሚሆኑ ሁለት ሰፋፊ እስክሪኖች፣ የሳውንድ ሲስተም፣ አገልግሎቶችን በምስል እና በድምጽ ለመቅረፅ እንዲሁም በቀጥታ ለማሰራጨት የሚያግዙ መሳሪያዎች ይጠቀሱበታል። ባሳለፍነውም ዕሁድ በመደበኛ የአምልኮ ፕሮግራም እነዚህን መሳሪዎች የማህበሩ ምዕመናን፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች እና አገልጋዮች በተገኙበት በታላቅ ምስጋና ተመርቀው ለአገልግሎት ውለዋል። መሳዎቹም በማኅበሩ ከሚሰጡት አገልግሎት ባሻገር ለወደፊት በኪራይ መልክ ለገቢ ማስገኛ እንደሚውሉ በአዕለቱ የተጠቀሰ ሲሆን አገልግሎቱን ላስተባበሩ አገልጋዮች እውቅና ተሰጥቷል። ምስል: መካኒሳ መካነ ኢየሱስ ማኅበረ ምእመናን ሚድያ አገልግሎት

#ዛሬ_በእንጦጦ_ማህበረ_ምዕመናን_ለ4_አገልጋዮች_የቅስና_ሹመት_ተሰጠ * * * * * * የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በአዲስ አበባ ሲኖዶስ ለቃሉ እና ቅዱሳት ሚስጥራት እንዲያግዝ ዛሬ ሚያዝያ 19 ቀን 2017 ዓ/ም ለ4 አገልጋዮች የቅስና ሃላፊነት ተሰጥቷል። የቅስና ሃላፊነቱን የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዘዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የሰጡ ሲሆን አገልጋዮቹ በቤተ ክርስቲያኒቱ አሰራር አስፈላስጊውን ዝግጅት ያጠናቀቁ መሆኑን በመግለጽ፤ ማወቅ የሚገናቸውን ብዙ ነገር ያወቁ፤ ገናም ግን እያደጉ የሚሄዱ ናቸው ብለዋል። በዛሬውም እለት በቡሌ ሆራ ስለሚካሄደው የቅስና ሃላፊነት የመስጠት መርሃ ግብር በመጥቀስ በመካነ ኢየሱስ እግዚአብሔር ብዙ በረከት እያደረገ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል። በስፍራውም የሲኖዶሱ አመራሮች፣ አገልጋዮች እና የቀደሙ ቀሳውስት የተገኙ ሲሆን ለእጩ ቀሳውስቱ እጅ በመጫን ፀልየዋል። ለመከሩ አገልግሎት እግዚአብሔር ብዙ አገልጋዮችን እያበዛልን ስለሆነ የተመሰገነ ይሁን። ምስል፡ አገልጋይ ግዛቸው አይካ

#ለ17_አገልጋዮች_የቅስና_ሹመት_ተሰጠ ‎* * * * * * የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ለ17 አገልጋዮች የቅስና ሹመት ዛሬ ሚያዝያ 19 ቀን 2017 ዓ/ም ተሰጥቷል። አገልጋዮቹም የቅስና ሃላፊነታቸውን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ታሪኩ ቶለሳ የተቀበሉ ሲሆን ምክትል ፕሬዚዳንቱ አገልጋዮቹ ከዚህ በፊት በተቀበሉት ተልዕኮ ላይ ተጨምሮ የተሰጣቸው መሆኑን ገልፀዋል። የሲዶሱም ፕሬዚዳንት ቄስ ደስታ ሀሮ ብዙ ከተቀበለ ሰው ብዙ እንደሚጠበቅ በማስታወስ ሀላፊነቱን የተቀበሉን አገልጋዮች ምዕመናን በፀሎት እና በምክር እንዲደግፏቸው አሳስበዋል። ሚያዝያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም፤ ቡሌ ሆራ ምስልና ዘገባውን ከሲኖዶሱ የማህበራዊ ሚድያ አገኘነው። _ _ _ _ _ _ Tajaajiltoota 17f muudamni lubummaa kenname ‎* * * * * * ‎WWWMYI Sinoodoosii kibba Itoophiyaatti tajaajiltoota 17f guyyaa har'aa, Ebla 19, 2017 muudamni lubummaa kennamee jira. ‎ ‎Tajaajiltootni kunneenis muudama lubummaa isaanii Itti Aanaa pirezdaantii waldaa Worra Wongeelaa Mekaanee Yesuusii Itoophiyaa Luba Dr Taarikuu Tolosaa irraa fudhatanii jiru. Lubni Dr. Taarikuunis Tajaailtoonni kun ergama duraan qaban irratti dabalataan kan itti kenname ta'uu himaniiru. ‎ ‎Pirezdaantin sinoodoosichaa lubni Dastaa Haroo nama baayyeen itti kenname irraa baayyeen akka eegamu yaadachiisuun amantoonni tajaajiltoota itti gaafatamummaa fudhatan kana gorsaa fi kadhannaadhaan akka deeggaran hubachiisanii jiru. ‎Eebla 19/8/2017 SKI, Bulee Horaa Gabaasnii fi suuraan midiyaa hawaasaa sinoodoosichaa irraa kana fudhatamee dha.

የአራተኛው ዓመት "የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንት" ብሔራዊ ክብረ በዓል ቅስቀሳ እና ግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በቢሾፍቱ ከተማ ተካሄደ * * * * * * ቤተ ክርስቲያኒቱ ስለምታካሂዳቸው የቋንቋ ልማት፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉምና ቅዱሳት መጽሐፍ አጠቃቀም አገልግሎቶች ምዕመናን ግንዛቤ እንዲኖራቸው እና ለአገልግሎቱ መስፋፋትና ተደራሽነች የግላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ታስቦ የሰኔ ወር ሁለተኛ ሳምንት በቤተ ክርስቲያኒቱ የጊዜ መቁጠሪያ ሰሌዳ "የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንት" ሆኖ እንከበር ተቀምጧል። የዘንድሮውም ዓመት ክብረ በዓል በአራቱም የሀገሪቱ መአዘናት በሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅሮች፣ ተቋማት ፣ ሴሚናሪዎች እና ማኀበራነ ምዕመናን "ሁሉም ለመጽሐፍ ቅዱስ" በሚል መሪ ቃል ከሰኔ 9-15 ቀን 2017 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ይከበራል። የዚህም ክብረ በዓል አካል በመሆን በቢሾፍቱ ከተማ ልዩ ሴሚናር፣ የደም ልገሳ፣ የከተማ ጽዳት እና የጎዳና ላይ ሩጫ ከሰኔ 13-14 እንዲካሄ ተወስኖ ዝግጅቶች ተጀምረዋል። ለበዓሉም ስኬታማነት በከተማው እና በአከባቢው የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሰበኮችና ከ100 በላይ የሚቆጠሩ ማኀበራነ ምዕመናን የዝግጅቱ ባለቤት ሆነው የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ይጠበቃል። ለዚሁ አላማ የቤተ ክርስቲያኒቱ የቅዱሳት መጽሐፍት አጠቃቀም ብሔራዊ አስተባባሪ የሆኑት ቄስ አለሙ ቡሳዋ በገላን በአደአ ሰበካ ከ28 ማኀበራነ ምዕመናን ለመጡ አገልጋዮችና ተወካዮች ገለፃ አድርገዋል። አገልጋዮቹም በተለዩት መርሃ ግብሮች ምዕመናንን አሳትፈው ለመካፈል ያላቸውን ተነሳሽነት የገለፁ ሲሆን የዚሁ አይነት ተመሳሳይ ቅስቀሳዎች በሌሎች ሰበኮች እንደሚቀጥል አገልጋይ ቄስ አለሙ ገልጸዋል።‌‌ - - - - - - - - - The fourth year national Bible Week celebration awareness raising and mobilization program was held at Bishoftu city. * * * * * * For giving awareness and increase engagements of members for the expansion and sustainability of the Church’s language development, Bible translation, and scripture engagement ministers, the third week of June is dedicated as a "Bible Week" on the church's calendar. This year's celebration will be held colorfully within the structure of the church, institutions, seminaries, and congregations in four directions across the country, under the overarching theme "All for the Bible" from June 16-22. As part of the celebration; a seminar, blood donation, city cleaning, and street running are organized at the city of Bishoftu, from 21-22 June 2024. The church’s national coordinator for Scripture engagement ministry, Rev. Alemu Busawa briefed ministers and representatives from the 28 congregations of the Gelan Ada Parishe. On the celebration, parishes in and around the city and the congregations that count more than 100 are expected to own and participate. Following the mobilization session, the ministers have expressed their commitment to mobilize and engage with members of their congregations on the celebration. This kind of session will also take place in other parishes, said Rev. Alemu. _ _ _  _ _ _ Telegram - t.me/EECMYeth YouTube News - https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=sKYiY4tgy3n6lErq YouTube Teaching - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=Flw2QQIBv5GDGUZL

Young missionaries from the Norwegian Lutheran Mission visited the Church's central office. * * After their two weeks visit in different part of the country, the missionaries were in preparation to return back when they visited the Church’s central office. During the visit, the president of the Church, Rev. Dr. Yonas Yigezu welcomed the young missionaries at his office. Following a brief conversation about their time here, the President prayed for the missionaries' safe return and a ministry ahead of them. The director for the Church’s Children and Youth Ministry, Mr. Wondmagegn Udessa presented about the background establishment history and current missial and development works of the Church. He also shared the experience of his department, from the accomplishments obtained as a result of statistical approaches to address children and youth of the Church. The Norwegian Lutheran Mission is one of the leading mission organizations within the nation and strong mission partners of the Church with active engagement since 1948. _ _ _  _ _ _ Telegram - t.me/EECMYeth YouTube News - https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=sKYiY4tgy3n6lErq YouTube Teaching - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=Flw2QQIBv5GDGUZL