uk
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

Відкрити в Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

Показати більше
3 315
Підписники
+724 години
+267 днів
+11030 день
Архів дописів
የአስተምህሮ እና የምዕመናን ጥበቃ ስልጠና ተሰጠ × × × × “አስተምህሮ እና የምዕመናን ጥበቃ” በሚል አርዕስት በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተሞች ለሚገኙ አፋን ኦሮሞ ተናጋሪ የአዲስ አበባ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ማኅበራነ ምዕመናን ቄሶች፣ ወንጌላዊያን እና የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች ከጥር 14–15/2016 ዓ.ም ጉለሌ በሚገኘው የፊንፊኔ ኦሮሞ ማህበረ ምዕመናን ለሁለት ቀናት ስልጠና ተሰጥቷል። የቤተ ክርስቲያኒቱም ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶሎሳ በስልጠናው ላይ በመገኘት ለአገልጋዮች ቃለ እግዚአብሔር አስተምረው፣ ሰላምታ በማቅረብ የቤተ ክርስቲያኒቱን መልዕክት አስተላልፈዋል። በስልጠናው ተሳታፊ የሆኑትም አገልጋዮች በነበራቸው ውይይት ጊዜ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና በየደረጃው የሚገኙ የክርስቲያን ተማሪ ህብረቶች ለስህተት ትምህርት እና ልምምዶች ተጋላጭ ስለሆኑ ማኅበራነ ምዕመናኑ ልዩ ትኩረት ሰጥተው መስራት በሚችሉባቸው ስልቶች ዙሪያ መክረዋል። “የስህተት ትምህርት በመጽሐፍ ቅዱስ ብርሐን ሲፈተሽ” በሚል ርዕስ በቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌል ተልዕኮና ቲኦሎጂ ዲፓርትመንት የተዘጋጀ መጽሐፍ ለስልጠናው ተሳታፊዎች እንዲቀርብ ተደርጓል። Leenjiin "Barsiisaafi Eegumsa Amantootaa" irratti Xiyyeeffatu Kenname × × × × Mata duree "barsiisaa fi eegumsa amantootaa" jedhu irratti Luboota, H/Wangeelaa, Jaarsolii fi tajaajiltoota Oromoo Waldoota Amantootaa Magaalaa Finfinnee fi Shaggar keessa jiraniif Sinoodosii Giddu Galeessa Itiyoophiyaa fi Sinoodosii Addis Ababaa irraa kan waltti qabamaniif leenjiin guyyaa lamaa (Amajjii 14 fi 15, bara 2016) Gullalleetti kan argamu Waldaa Amantoota Oromoo Finfinneetti kennameeraaf. Itti A/Pirezedaantii Waldatti Lubni Dr. Taarikuu Tolosaa leenjii kana irratti argamuudhaan tajaajiltoota kana dubbii Waaqayyoo barsiisanii, nagaa gaafachuudhaan ergaa Waldaa Kiristiyaanaa dabarsaniiru. Tajaajiltootni lernjicha irratti hirmaatan yeroo maree isaanii keessatti haala yeroo Ammaa barattootni sadarkaa ol-aanaa irratti baratan keessa jiranii fi tokkummaa barattoota Kiristiyaanaa Oromoo barsiisa sobaa fi shakkallii hin barbaachifnee saaxilamaa waan jiraniif Waldaan Amantootaa xiyyeeffannaa godhanii akka irratti hojjetan, tajaajila mucaalii fi karaa ittiin dargaggootaa jabeessuudanda'an bu'uura godhatanii akka hojjetan irratti maree bal'aa geggeessaniiru. "Barsiisni sobaa ifaa Wangeelaatiin Yeroo Sakkatta'amu" mata duree jedhu irratti Dippaariimentiin Ergaa Wangeelaa fi Ti'ooloojii Waldatti leenjicha qopheessee hirmaattotaaf dhiyeessera. Doctrine and believers' retention training was given × × × × Under the title of “Doctrine and believers retention” a two days fruitful training was given for Afaan Oromo speaking congregations Pastors, Evangelists and Elders within the Addis Ababa and Central Ethiopia Synod from January 23-24, 2024 at Finfine Oromo Congregation. The church’s vice president, Rev Dr Tariku Tolessa, conveyed the church’s message after sharing the word of God with participants. During discussion times, the ministers consulted on the possible strategies to counter false teachings that are entertained and practiced in the higher educational institution, christian students' fellowships. A book that was prepared by the Department of Mission and Theology, under the title "False Teaching examined under the Light of Scripture," was also made available.

የሚስዮን ቀን ጥር (2).png2.87 MB

የሚስዮን ቀን ጥር (2).png3.05 MB

የኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢየሱስ በደቡብ ኢትዮጵያ የሮቦት ሲኖዶስ በገረሴ ዙርያ ወረዳ በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው አርሶ አደሮች ድጋፍ አደረገ። ** የኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢየሱስ በደቡብ ኢትዮጵያ የሮቦት ስኖዶስ ፕረዝዳንት ቄስ ከተማ ካምሌ እና ዋና ፀሐፊ ቄስ ደመቀ ጩራቀ በገረሴ ዙርያ ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት ተገኝተው ለገረሴ ዙርያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሳሁን ካማ በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው 28 አባወራ አርሶ አደሮች ድጋፍ አደርጓል። አቶ ካሳሁን ካማ ስረከቡ እንደተናገሩት ስኖዶሱ ገና የተመሠረተ ለጋ ስኖዶስ እንደመሆኑ ድጋፍ አልጠየቅንም። ነገር ግን ፈጣሪ አሳስቦአቸው ይህንን በጎ ተግባር ድጋፍ ስላደረጉ በፈጣሪና በወረዳው ህዝብ ስም አመሰግናለሁ ብለዋል። ለድሃ የሰጠ ለእግዚአብሔር ያበድራል እንደሚባለው የስኖዶሱ መልካም ተግባር እኛ እርስ በርሳችን እንድንረዳዳና እንድንደጋገፍ መልካም ተሞክሮ ነው ብሏል። ስኖዶሱ በዚህ ብቻ ሳይሆን ለበርካታ መታከም ለማይችሉ የማህበረሰብ ጤና መድህን ፈንድ በመግዛት እንደዚሁም ለተቸገሩት በመርዳት ከማህበረሰቡ ጎን የቆመ ስለሆነ ለቀጣይ በማናቸውም ሁኔታ ከስኖዶሱ ጎን በመቆም የወረዳው መንግስት ተደጋግፈው እንደሚሠሩ ተናግሯል። ዶ/ር ቦርሴ ቦታ የገረሴ ዙርያ ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ በበኩላቸው የገረሴ ዙርያ ወረዳ የመሬት አቀማመጥ ወጣ ገባ በመሆኑ ለተፈጥሮ አደጋ ተጋላጭ በመሆኑ በርካታ አርሶ አደሮችን ለጉዳት እየተዳረጉ መሆኑን ተናግሯል። ባለፈው ወቅቱን ባልጠበቀ ዝናብ አኳያ በተፈጥሮ ናዳ አደጋ የደረሰባቸው ከጋርባንሳ ሦሮጌ፣ ከጋርባንሳ ካርቼ፣ ከመሌ ጋጉሌ እና ካምኣለ ባርኤ ኦሮ ቀበሌ ለመጡ 28 አባወራ አርሶ አደር ቤተሰቦች 14 ኩንታል የምግብ እህል ስኖዶሱ ድጋፍ ማድረጋቸውን በመግለጽ አመስግኗል። በወረዳው በተፈጥሮ አደጋ እና አየር መዛባት ምክንያት ለችግር የተጋለጡ በርካታ አርሶ አደሮች መኖራቸውን ኃላፊው ተናግረው ስኖዶሱ ከወንጌል ሥራ ጎን ለጎን በመንግሥት ልሸፈኑ ያልቻሉ በርካታ የልማት ሥራዎችን ከጎናችን ሆነው እንዲደግፉ ስሉ ጥሪ አቅርቧል። የኢ/ወ/ቤ/ክ/መ/ኢየሱስ በደቡብ ኢትዮጵያ የሮቦት ስኖዶስ ፕረዚዳንት ቄስ ከተማ ካምሌ በበኩላቸው ስኖዶሱ አድስ ነው፣ ቀጣይ ከወረዳ፣ ከዞንና ከክልሉ መንግሰት ጋር አብረን ለመሥራት ዕቅድ አለን ብሏል። እስከአሁን ባለን ሂደት ከወረዳም ይሁን ከቀበሌ መንግስት ለእኛ ሥራ እንቅፋት የሆነ ነገር የለም በማለት ቀጣይ አብረን ተባብረን ለመሥራት እግዚአብሔር እንዲረዳን እንለምናለን ስሉ አስታወቋል። ገረሴ፣ ጥር 8/2016 ዓ.ም(የገረሴ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት) መረጃውን ከየገረሴ ዙርያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን የፌስቡክ ገፅ አገኘነው።

በማዕከላዊ ስምጥ ሸለቆ፣ ኮንሶ ሰበካ፣ አዲስ ከተማ ማህበረ ምዕመናን ከጥር 3-5/ 2016 ዓ.ም ታላቅ መንፈሳዊ ኮንፍራን ተካሄደ። ለሶስት ቀናት በቆየው ኮንፍራንስ የእግዚአብሔር ቃል በኋይልና በሙ
+9
በማዕከላዊ ስምጥ ሸለቆ፣ ኮንሶ ሰበካ፣ አዲስ ከተማ ማህበረ ምዕመናን ከጥር 3-5/ 2016 ዓ.ም ታላቅ መንፈሳዊ ኮንፍራን ተካሄደ። ለሶስት ቀናት በቆየው ኮንፍራንስ የእግዚአብሔር ቃል በኋይልና በሙላት ተሰብኳል እንዲሁም ልዮ የአምልኮ እና የፀሎት ጊዜ እንደነበረ ከማህበረ ምዕመኗ ማህበራዊ ድህረ ገፅ የተገኘው መረጃ ያስረዳል። 📸 - አዲስ ከተማ ማህበረ ምዕመናን የሚድያና ኮሚኒኬሽን አገልግሎት

የኖርዌጂያን ሉተራን ሚሲዮን መሪዎች የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት ጎበኙ። በቆይታቸውም የቤተክርስቲያኒቱን ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ተሾመ አመኑ እና የልጆችና ወጣቶች
+7
የኖርዌጂያን ሉተራን ሚሲዮን መሪዎች የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት ጎበኙ። በቆይታቸውም የቤተክርስቲያኒቱን ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ተሾመ አመኑ እና የልጆችና ወጣቶች መምሪያ ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሳን አግኝተው አነጋግረዋል። ** ** ** Norwegian Lutheran Mission (NLM) leaders visited the Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus, central office. During their time at the office, the leaders met with the general secretary, Rev Teshome Amenu, and children and youth department director, Wondmagegn Udessa.

“አስተምህሮ እና የምዕመናን ጥበቃ” በሚል አርዕስት ለማኅበራነ ምዕመናን መሪዎችና አገልጋዮች ስልጠና በመሠጠት ላይ ይገኛል * * * * * * በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተማ ለሚገኙ የማህበራነ ምዕ
+9
“አስተምህሮ እና የምዕመናን ጥበቃ” በሚል አርዕስት ለማኅበራነ ምዕመናን መሪዎችና አገልጋዮች ስልጠና በመሠጠት ላይ ይገኛል * * * * * * በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተማ ለሚገኙ የማህበራነ ምዕመናን ቄሶች፣ ወንጌላዊያን እና ሽማግሌዎች በአዲስ አበባ ማህበረ ምዕመናን ለሁለት ቀናት የተዘጋጀው ስልጠና ዛሬ ጥር 7/ 2016 ተከፍቷል። ስልጠናው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶሎሳ በማለዳው የፀሎት ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል አስተምረው ስልጠናውን ከፍተዋል። በወቅታዊነት በወንጌላዊያን አማኞች ዙሪያ እየተነሱ ያሉ ሀሰተኛ አስተምህሮና ልምምዶችን በእግዚአብሔር ቃል መሠረት መከላከል እና ምዕመናንን መጠበቅ የሚቻልበትን ሰፊ ግንዛቤ ለአገልጋዮች የሚያስጨብጥ ስልጠና መሆኑ በስልጠናው የተመላከተ ሲሆን የስልጠናው ተሳታፊ አገልጋዮችም በአገልግሎት ስፍራዎቻቸው ያሉ ተግዳሮቶችን በማንሳ ተወያይተውባቸዋል። ስልጠናውም ነገ ቀጥሎ የሚውል ሲሆን በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተማ ለሚገኙ አፋን ኦሮሞ ተናጋሪ ማህበራነ ምዕመናን ተመሳሳይ ይዘት ያለው ስልጠና ጉለሌ በሚገኘው ፊንፊኔ ኦሮሞ ማህበረ ምዕመናን በቀጣይ ሳምንት እንደሚሰጥ አገልግሎቱን ከሚመራው የቤተክርስቲያኒቱ የወንጌል ተልዕኮ እና ቲኦሎጂ ዲፓርትመንት መረዳት ተችሏል።

"ልጆች ወደ ኢየሱስ ይምጡ" በሚል መሪ ሃሳብ በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማኅበራነ ምዕመናን የልጆች ቀን በህፃናት አገልግሎት፣ በግጥም፣ በድራማ፣ በስነ ጽሑፍ እና ለልጆች በመ
+9
"ልጆች ወደ ኢየሱስ ይምጡ" በሚል መሪ ሃሳብ በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማኅበራነ ምዕመናን የልጆች ቀን በህፃናት አገልግሎት፣ በግጥም፣ በድራማ፣ በስነ ጽሑፍ እና ለልጆች በመፀለይ ዛሬ ተከብሮ ውሏል። ከማ/ምዕመናን አስከ ዋናው የቤተክርስቲያኒቱ ጽሕፈት ቤት ያለውን የልጆች አገልግሎት ለማጠናከር ያስችል ዘንድ ገቢ የማሰባሰብ ስራዎች ተሰርተዋል። _ _ _ “ ...ሕፃናትን ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተዉ አትከልክሉአቸው፤ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደነዚህ ላሉት ናትና።" ማርቆስ 10:14 * * * * Today, Under the theme "Let Children come to Jesus", congratulations of The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus celebrated Children's day with the services given by children, poetry, drama, literature and prayer for children. In order to enhance children ministry from congregation level to the central office, fundraising was also held. _ _ _ “Let the little children come to me, and do not hinder them, for the kingdom of God belongs to such as these." Mark 10:14 #የልጆች_በዓል #guyyaa_ayyaana_ijoollee MY Sunday School EECMY Youth Ministry

!ነገ! #Tomorrow!
+1
!ነገ! #Tomorrow!

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምስራች ድምጽ የመገናኛ ዘዴዎች አገልግሎት ፥ የንዋየ ቅዱሳት ማከፋፈያ ** ** ** ** EECMY Yemisrach Dimth Communications Servicer, Vestment Distribution Center