uk
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Відкрити в Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Показати більше
1 161
Підписники
Немає даних24 години
+37 днів
+730 день
Архів дописів
ከታሰሩት ወንድሞች መካከል ከአንዱ የተላለፈ መልዕክት፦   "አልሐምዱሊላህ! የማይረሳን የምርቃት ፕሮግራም አሳለፍኩ። የምቆጥረው፣ የማስታውሰው፣ ለልጆቼ የምነግረውን ታሪክ አገኘሁ። አላህ ሙዚቃ እና ጫጫታ ከበዛበት መድረክ አርቆ ስለመብቴ፤ ስለአኼራዬ እየተሟገትኩ እንድውል አደረገኝ። አዲስ አለም፤ አዲስ ልምድ እንዳገኝ አደረገኝ። "የምትለብሱት ሪቫን ላይ የፈለኩት መልዕክት መቀመጥ አለበት።" - በሚል ክስ መታሰራችን ስላቅ ቢሆንም ከሐቅ ጎን ሆነን ስለታሪካዊው ሀላፊነታችን መቆማችን ደግሞ መታደል ነበር። አላህ ፍትሁን ያምጣ። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!" @aaumsu

ኒካህ፤ ምርቃት እና እስር በአንድ ቀን!! በዛሬው እለት 20/10/2018 ዓ,ል  ወንድማችን ፋህሚ ናሲር…ከኢኮኖሚክስ ዲፓርትመንት በተመረቀበት እለት በጌታችን አላህ ፈቃድና ውዴታ ከዚሁ ዲፓርትመንት ተመራቂ ከሆነችው እህታችን ኢክራም ሱለይማን ጋር ኒካሃቸውን አድርገዋል። ወንድማችን በዛሬው ዕለት "ሪቫናችሁ ላይ ሎጎዬ የለም" በሚል ዩኒቨርሲቲው እንዲታሰሩ ካደረጋቸው ወንድሞች ነበር። በአንድ ቀን ምርቃትንም፤ ትዳርንም፤ እስርንም አስተናግዷል። አሏህ ትዳራችሁን የኸይር ሁሉ መፍለቂያ ያድርገው። ለኢስላም መስዕዋት በመሆን እንደተጀመረው በዚህ ትዳር የሚወለዱ ልጆች የዑመር አይነት የዲን ታጋዮች ያድርጋቸው። 🎉بارك الله لكما وبارك عليكما وجمع بينكما في خير 🎉 @aaumsu

ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ደረሰ _ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ! ! ! ስለኒቃብ መጠየቅ በምርቃት ቀን እስከ ማሳሰር ከመድረሱ በፊት ጀምሮ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ
ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ደረሰ _ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ! ! ! ስለኒቃብ መጠየቅ በምርቃት ቀን እስከ ማሳሰር ከመድረሱ በፊት ጀምሮ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ በሰፊው ይዳሰሳል። ሕገ- መንግስቱን ጥሰው ስለሚጥሱት መብት ሕጋዊ ቦታ በሰፊው ይተነተናል። ከእኛ ስለሚጠበቀው ነገርም በደንቡን ውይይት ይደረጋል። ሙባረክ አደም፦ በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ፈርቀዳጅ ታጋይ፤ አክቲቪስት፤ ቲክቶከር፤ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና፤ የሂባ ፋውንዴሽን መስራች ነው። ፕሮግራማችንን በመድረክ መሪነት የሚያስተናብርልን ይሆናል። ሙስጠፋ ሺፋ፦በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ወቅት ለታሰሩት ጠበቃ ሆኖ አገልግሏል፤ አሁንም በጥብቃና ሙያው አንቱታን ካተረፉ ባለሙያዎች መካከል ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ሕጋዊ መሠረት ያብራራልናል። የሕያ ኢብኑ ኑሕ፦የንፅፅር ትምህርት መምህር፤ የሒዳያ ኢስላማዊ ማህበር መስራች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ ያብራራልናል። ሁሴን ዩሱፍ፦የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፀሐፊ ሲሆን ከማን ምን ይጠበቃል የሚለውን በዝርዝር ያስቀምጣል። መቅረት አይታሰብም። ጀመዓዎች በቻናሎቻችሁ ላይ አሰራጩት። ሁሉም ለሁሉም ያድርስ። በአንድነት በአንድ መድረክ ተሰባስበን ስለመብቶቻችን እውቀትን እንጨብጥ። 🗓 ቀን፡ ሰኞ፣ ሰኔ 22 (Monday, 29 June) ⏰ ሰዓት፡ ከምሽቱ 03፡00 ሰዓት እውቀትን መፈለግ መብት ነው፤ እምነትንም በክብር መተግበር እንዲሁ! የቲክቶክ ገፃችንን Follow በማድረግ ዝግጅቱን ይጠብቁ፦ https://www.tiktok.com/@aaumsu ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

አሶሳ ላይ መብት የሆነው ኒቃብ አዲስ አበባ ላይ ወንጀል የሚሆነው በምን አግባብ ነው?! አሶሳ ዩኒቨርስቲ ኒቃብ ለብሰው ተምረው ከፍተኛ ውጤት ያመጡትን ተማሪዎች ኒቃባቸውን እንደለበሱ ያስመርቃል፤ ይ
+1
አሶሳ ላይ መብት የሆነው ኒቃብ አዲስ አበባ ላይ ወንጀል የሚሆነው በምን አግባብ ነው?!    አሶሳ ዩኒቨርስቲ ኒቃብ ለብሰው ተምረው ከፍተኛ ውጤት ያመጡትን ተማሪዎች ኒቃባቸውን እንደለበሱ ያስመርቃል፤ ይሸልማል። አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ደግሞ ኒቃብ ለብሰው ሲማሩ ችግር ይፈጥራል፤ ሊመረቁ ሲመጡ ያሳስራል። በአሶሳ ዩኒቨርስቲ ዩኒቨርስቲ ከHealth Science ከፍተኛ ውጤት ያመጣችዋ ኢማን ዲልሰባ በወርቅ ሜዳልያ ስትመረቅ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያሉ ኒቃቢስቶች ደግሞ ኒቃብ መብት ነው ብላችሗል ተብለው ከእስር ቤት ውለዋል። አሶሳ ላይ መብት የሆነ አዲስ አበባ ላይ ወንጀል የሚሆነው በምን አግባብ ነው?! ምንም ልዩነት የለውም። ልዩነት የአመራሮቹ ነው። የአመራሮቹ አስተሳሰብ፤ የአመራሮቹ ሙስሊም ጠልነት ነው። ሆኖም ግን አይቀጥልም። ፍትሕ ይሰፍናል። @aaumsu

የታሰሩት ሙሉ ለሙሉ ተፈተዋል። ዝርዝሩን ይዘን እንመለሳለን። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች ታሰሩ ! ! ! አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ምረቃ ፕሮግራምን እያካሄደ ባለበት ወቅት በምርቃታቸው ቀን የመረጡትን፤ የሚያስደስታቸውን፤ የምርቃ
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች ታሰሩ ! ! ! አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ምረቃ ፕሮግራምን እያካሄደ ባለበት ወቅት በምርቃታቸው ቀን የመረጡትን፤ የሚያስደስታቸውን፤ የምርቃት ቀኔ መልዕክት ይሁን ያሉትን በሪቫን እና ባይንደር ላይ አሳትመው ባሉበት እና የደስታ ቀናቸውን እያሳለፉ ባለበት ወቅት የግቢ በር አካባቢ ላይ ሳሉ 10 ገደማ ልጆችን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋል። እንደ ምክንያትም "ሪቫኑ ላይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሎጎ የለም!" - የሚልን አቅርበዋል። ይህ ፈፅሞ ትክክል ያልሆነ፤ የተማሪዎችን ነፃነት የሚጋፋ፤ የደስታ ቀናቸውን የሚያደፈርስ እና ከአንድ አንጋፋ ዩኒቨርስቲ የማይጠበቅ እኩይ ተግባር ነው። መሠል የሙስሊም ተማሪዎችን ነፃነት የሚጋፋ ተግባር ኒቃብ መልበስን በመመሪያ ከመከልከል ጀምሮ እየተደጋገመ ያለና ጥሩ ወዳልሆነ አቅጣጫ የሚያመራ ነው። ስለሆነም የታሰሩት ሙስሊም ተማሪዎች በቶሎ ተፈተው ወደ ቤተሰባቸው እንዲመለሱ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !!! @aaumsu

ይህ የጥያቄ አለን ትውልድ ነው። የሙስሊም ተማሪዎች መብት እስኪከበር ላያርፍ ቃልኪዳን ያሰረው። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu
ይህ የጥያቄ አለን ትውልድ ነው። የሙስሊም ተማሪዎች መብት እስኪከበር ላያርፍ ቃልኪዳን ያሰረው። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

We have a question! We want an answer!! @aaumsu
+1
We have a question! We want an answer!! @aaumsu

Look at the image በዛሬው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምርቃት ፕሮግራም ላይ ነው ሪባኑን ተመልከቱት ባይንደሩን ተመልከቱት "She will wear her niqab, She will also att
Look at the image በዛሬው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምርቃት ፕሮግራም ላይ ነው ሪባኑን ተመልከቱት ባይንደሩን ተመልከቱት "She will wear her niqab, She will also attend her education --- እንደለበሰች ትማራለች። We have a question, and we want an answer --- ጥያቄ አለን መልስም እንፈልጋለን።" - የሚል መልዕክት ነው። በሁሉም ቦታ ስለመብታችን እንጠይቃለን። መጠየቅም ሆነ መልበስ መብታችን ነው። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣም እንጠይቃለን። @aaumsu

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ! እስካሁን ከኖራችሁት አብዛኛውን ሀያታችሁን ያሣለፋችሁበትን መንገድ ፍሬውን ለማየት በመብቃታችሁ አልሀምዱሊላህ! በነገራችሁ ላይ አሁን ምጠቅሳቸውን ሁሉንም በዚህ አመት ነው ያወቅኳቸው፣ "ቀድሜ ባወቅኳቸው!" ያስባሉኝና በህይወቴ ላይ ጉልህ አሻራን ያሳረፉ የውብ ስነምግባር ባለቤቶች ናቸው:: አሚር ማህፉዝ(5 ኪሎ):- ያወቅኩት ከኒቃብ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ቢሆንም የተረጋጋ ባህሪይ ያለዉ፣ እንዲሁም ድርጊቱ ከቃላቱ በላይ ጎልተው የሚያስተምሩ መሆናቸውን ለመመስከር ብዙ ጊዜ አይፈጅም። አሚር ዘይድ(4ኪሎ)፦ በተመሳሳይ በኒቃብ እንቅስቃሴ ያወቅኩት ወንድም ነዉ:: አንተ የመራሃቸውን ሹራዎች መታደም መቻል ትልቅ ክብር ነበር:: የመሪ quality ምን መምስል እንዳለበት፣ ለቆሙለት አላማ ዋጋ መክፈል ምን ማለት እንደሆነ በተግባር አሣይተኸናል:: አንዋር (5ኪሎ):- የአካዳሚክ ሴክተር አባት ነው ብል ይቀላል:: ተማሪው እውቀትን ፍለጋ ወደሌላ እንዳይሄድ፣  እዚሁ ከወንድም እህቶቹ እንዲያገኘው፣ አካዳሚክስ ላይ ሙስሊሙ ከማንም በላይ እንጂ በታች እንዳይሆን  የለፋኸው ልፋት Legacy ሆኖ ይቀጥላል፣ የ5ኪሎ ተማሪ በዚህ በኩል ውለታህ አለበት:: ዕውቀትን ለመሻት ያለህ ቁርጠኝነትና ለዛም የሰዋኸው ጊዜ ለዚች የክብር ቀን አድርሶሃል። አብዱልፈታህ (5ኪሎ):- በጀምአችን finance ውስጥ ጀምው ራሱን እንዲችል በማድረግ ሂደት ውስጥ የነበረህ ጉልህ ሚና፣ ጀምአው ቋሚ ገቢ እንዲኖረው ኢሽራፍ ን በማቋቋም ላይ የነበረህ አስተዋፅዖ እጅግ አስደናቂና ሁሌም የሚታወስ  ነው።  ምንም ፕሮግራም በFreedom የሚዘጋጀው የናንተ ምርጥ economic management  ከጀርባው ስለሚኖር ነው:: ሀያት (5ኪሎ)፦ በብዙ ፈተና ውስጥ ብታልፊም ለጀምአችን ብዙ አበርክተሻል። የelec ታላቅ እህት፣ ሰብሳቢ፣ መካሪያችን፣ personal ሜንተሬ፣ እኔ በደከምኩ ሰአት ከጀርባዬ ሆነሽ ከአላህ በታች ያፀናሺኝ፣ አዳማጬ፣ ውድ እህቴ...each Conversation with you is precious, እንኳን ደስታሽን ለማየት አበቃኝ:: ሀሊ (ሰፈረሰላም):- አሁንም በኒቃብ እንቅስቃሴ ያተረፍኳት ሌላ ውድ እህት። እርጋታሽ ወደሌላው ይጋባል:: ታናሾችሽ ስናስቸግር እኛን handle የምታደርጊበት መንገድ ሁሌም ያስገርመኛል:: ለመንገዱ የከፈልሽው አንድ ሁለት ብዬ የምጨርሰው አይደለምና አላህ ውለታቸውን እጥፍ ድርብ አድርጎ ከሚመነዳቸው ያድርግሽ:: በመብታችን እንቅስቃሴ ላይ ተሳትፎ የነበራችሁ ምርጥ ወንድም እህቶቼ እንኳን ለዚህ ቀን አበቃችሁ! የ5 ኪሎ MDC ሜንተሮች በሙሉ፣ ሀናን፣ ሆሬኑስ፣ ኢማን፣ ፈቲ፣ ፎዚ፣ አህመድ፣ ፈይሰል፣ አብዱልሙኢን፣ አብዱልሙኒም፣ ስማችሁን ያልጠቀስኳችሁ በሙሉ:- ከአመታት ልፋትና ጥረት በኋላ እንኳን ለዚህ ቀን አበቃችሁ! ይሄ batch 5ኪሎ ውስጥ ያለው ቦታ ይለያል... በጣም ደስ ያለኝ፣ ኡኹዋችንን ያየሁበት አጋጣሚ:- exit exam result ከተለቀቀ በኋላ፣ የ5ኪሎ ተማሪዎች "ሁሉም የ 5k ሙስሊም አልፏል! መብሩክ!" ስንባባል ነበር። ይሄን የመሰለ መተሳሰብ፣ መዋደድ እና በሌላችን ደስታ መደሰትን ላደለን አላህ ምስጋና ይገባው! ምረቃታችሁ ኡማውን የሚጠቅም እንዲሆን ዱአዬ ነው፣ እናንተም ጊቢ የቀረነውን ታናሾቻችሁን በዱአችሁ አስታውሱን እያልኩ አበቃለሁ፣ አልፍ አልፍ መብሩክክክ!!!!!🎓🎓🎓

የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ማስተላለፍ የምትፈልጉ በ @fivekjemaa_bot በኩል ላኩልን።

اسلام عليكم ورحمة الله وبركاته ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት 5 ኪሎ ጀምዓ የተላለፈ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት 🎓🎉 ​የዓመታት ጥረትና በትዕግስት የታለፉት ፈታኝ ጊዜያት አምረውና አጊጠው ለዚህ ውብ የድል ቀን በቁ። ዛሬ ፍሬያችሁን የምታዩበት፣ የወላጆቻችሁንና የጀምዓችሁን ልብ በደስታ የምታሞቁበት ታላቅ ዕለት ነው። ለዚህ ታላቅ ክብርና ስኬት የበቃችሁ ውድ ተመራቂ ወንድሞችና እህቶች ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ‼️🎓🎉 ከብዙ ልፋትና ጥረት፣ ከስንት የእንቅልፍ ማጣት ሌሊቶች እና ከሐሳብና ጭንቀት ዓመታት በኋላ፣ ለዚህች በናፍቆት ስትጠብቋት ለነበረችው የድል ቀን ደረሳችሁ ‼️🎓🎉 የአመታት ልፋታችሁ ፍሬ አፍርቶ በዛሬው ዕለት በራሳችሁ የምትኮሩበት፣ ለዚህ ስላበቃችሁም አላህን የምታመሰግኑበት ታላቅ ቀን ነው። 🌟 በተለይም ደግሞ ከትምህርታችሁ ጎን ለጎን  በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ላይ ስትሳተፉ ለነበራችሁ በይበልጥ ደግሞ በፕሬዝዳንትነት ስታገለግል ለነበርከው በፅናትህ፣ በእርጋታህ እንዲሁም ኒቃብ ለባሽ እህቶቻችን በገጠማቸው ፈተና ወቅት ከፊት ሆነህ በመታገል ላይ ለነበርከው ውድ ወንድማችን መህፉዝ ነጋሽ እንዲሁም በካምፓስ ጀመዓ ላይ ጊዜያችሁን፣ ጉልበታችሁንና እውቀታችሁን መስዋዕት በማድረግ ለዲናችሁ ስታገለግሉ ለነበራችሁ ብርቅዬ  ወንድም እና እህቶች፤ አላህ (ሱ.ወ) ልፋታችሁን በጀነትል ፊርደውስ ይመንዳችሁ። በዱንያም በአኼራም አላህ ከፍ ያድርጋችሁ፤ ለዲኑ የደከማችሁትን አላህ በእጥፍ ድርብ አጅሩን ይፃፍላችሁ። ዲናችን ምሉዕ ነውና በደስታም ሆነ በችሮታ ጊዜ እንዴት መሆን እንዳለብን ግልጽ መመሪያዎችን አስቀምጦልናል። እናም አደራ፣ በዚች የልፋታችሁን ፍሬ በምታዩባት የደስታ ቀን አላህን ከማመጽ እንጠንቀቅ። 🤲 እህቶች አለባበሳችሁን በመጠበቅና ከወንዶች ጋር ባለመቀላቀል፣ ወንድሞችም እይታን በመስበርና ለአንተ ተገቢ ካልሆነች ሴት ጋር ባለመገኘት እንዲሁም አላስፈላጊ ከሆኑ ስብስቦች በመራቅና በሰላተል-ጀማዓህ ላይ ሁላችሁም አደራችሁን እንድትወጡና የአላህን ድንበሮች እንድትጠብቁ እናሳስባለን። 🕌✨ ይህ የጉዟቹ መጀመሪያ እንጂ መጨረሻው እንዳልሆነም አውቃችሁ፣ የሙስሊሙን ዑማ ችግሮች ለመፍታትና በየሙያችሁ ለመታገል በበለጠ ወኔና ጥንካሬ እንደምትጓዙ ባለሙሉ ተስፋ ነን። ምርቃታችሁ የኸይር በር መክፈቻ ቁልፍ፣ ቀጣዩ የሕይወት ምዕራፋችሁም የተሳካና የሰመረ እንዲሆን ከልብ የመነጨ ዱዓችን ነው፤ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ! መብሩክክክ‼️ አልፍፍፍ መብሩክክክ‼️ እንኳን ደስ አላችሁ ‼️ CONGRATULATIONS TO OUR GRADUATING BROTHERS AND SISTERS 🎉🎉🎉🎆🎆🎆🎆🎆🎉🎉🎉🎓🎓🎓🎓🎓🎓 @fivekjemaa 🌟✨

ድምፃችን አይታፈንም! በመጪው ሰኞ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት የቲክቶክ ገፅ ( https://www.tiktok.com/@aaumsu ) ላይ Live እንገናኝ። ድምፃችንን ለማፈን መድረክ ቢነፍጉንም ስለመብቶቻችን ለመወያየት፤ ከምሁራን አንደበት እውቀትን ለመቅሰም በበይነመረብ ቀጠሮ ይዘናል። ቀጠሯችንን ቀጠሯችሁ አድርጉ። ለሌሎችም አሰራጩ። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን በደል የትም ብንሆን አንረሳውም። ተማሪ ሆነን አንረሳውም! ተመራቂ ሆነን አንረሳውም!! ወላጅ ሆነን አንረሳውም!!! ከስራ ገብተን አንረሳውም!!! በዳዮች ሁለንታናዊ እድገታችንን ለማቀጨጭ ሲሉ እየበደሉን ባለበት ሰዓት ልንዘናጋ የምንችልበት ምክንያት የለም። ደስታ ውስጥ ሆነን አንረሳውም! ሐዘን ውስጥም ሆነን አንረሳውም!! የትላንቱ፣ የዛሬው፣ ብሎም የነገው ትውልድ አማና ነውና ባለንበት ቦታም ሆነ ባለንበት ሁኔታ ውስጥ ሆነን ጥያቄ አለን እንላለን። ስለ ሰብዓዊ መብታችን _ ስለሐይማኖታዊ መብታችን _ ስለመማር መብታችን _ ስለዜግነት መብታችን --- ጥያቄ አለን እንላለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

"ፍትሕ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች!" - በሰመራ ዩኒቨርስቲ የዋንጫ ተሸላሚ የሆነው ዶክተር ሙሐመድ ሐሰን በሰመራ ዩኒቨርስቲ የወርቅ ሜዳልያ እና ዋንጫ ተሸላሚ ሆኖ የተመረቀው ዶክተር
"ፍትሕ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች!" - በሰመራ ዩኒቨርስቲ የዋንጫ ተሸላሚ የሆነው ዶክተር ሙሐመድ ሐሰን በሰመራ ዩኒቨርስቲ የወርቅ ሜዳልያ እና ዋንጫ ተሸላሚ ሆኖ የተመረቀው ዶክተር ሙሐመድ ሐሰን በሐይማኖታቸው ምክንያት በደል እየደረሰባቸው ላሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች እና ለአክሱም ሙስሊሞች በምርቃቱ ቀን ድምፁን አሰምቷል። "ኒቃብ ፀጉርን እንጂ አዕምሮን አይፈንም!" - የሚልን መልዕክት ያስተላለፈው የዋንጫ ተሸላሚው ዶክተር ሙሐመድ ሙስሊም ተማሪዎችን የማያገል፤ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በእኩልነት የሚያስተዳድር፤ ፍትሕን የሚያሰፍን መመሪያ እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል። በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጀምሮ እየደረሱ ያሉ የመብት ጥሰቶች ቆመው ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ የሚመለከታቸው አካላት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርቧል። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! ©️ EHEMSU @aaumsu

ለ5 ኪሎ ካምፓስ የ2018 ዓ.ል ተመራቂ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ! 🎓 ​ቀደም ሲል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በኩል ልዩ የምረቃ ሪቫን እና ባይንደር  ስታዙ ለነበራችሁ የ5 ኪሎ ካምፓስ ተማሪዎች በሙሉ፤ ህብረቱ ያዘጋጃቸውን ውብና ጥራት ያላቸውን መለያዎች የ5 ኪሎ ጀምዓ በይፋ ተረክቧል። ​የምረቃ ቀናችሁን በጀምዓችን መለያ ይበልጥ ደምቃችሁ ለመገኘት ያዘዛችሁትን ሪቫን እና ባይንደር ከታች በተቀመጠው ስልክ ቁጥር እየደወላችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑንም እናበስራለን። ​ቀድማችሁ ላላዘዛችሁ ተማሪዎች ደግሞ አሁንም ቢሆን ጥራት ያለው ሪቫን እና ባይንደር መግዛት እና መረከብ የምትችሉ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን ። ​ሌላ ቦታ በመሄድ ሳይንገላቱ የራሳችንን መለያ ይዘን ውብ በሆነ መንገድ ደስታችንን እናከብራለን! 🎉 ​📞 ለማዘዝ ወይም ለመረከብ በዚህ ስልክ ቁጥር ይደውሉ፡ ​🔖 ወንዶች ╰┈➤• 0905877461 Mesud (@savior78) ​🔖 ሴቶች በዚህ ቦት ማዘዝ ወይም መረከብ ትችላላችሁ ╰┈➤• @fivekjemaa_bot ​አላህ መልካም የምረቃ ዕለት እንዲያደርግላችሁ እና ለቀጣዩ ህይወታችሁም ስኬትን እንዲለግሳችሁ የጀምዓችን የዘወትር ምኞት ነው‼️ ​@fivekjemaa

abdul-wadood-haneef-018.mp329.05 MB

🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ ﷺ 🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟 ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት "ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።" ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልባችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው። ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️ اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

عن سلمان - رضي الله عنه - قال: قال رسول الله - صلى الله عليه وسلم -: «لا يغتسل رجل يوم الجمعة، ويتطهر ما استطاع من طهر، ويدهن من دهنه، أو يمس من طيب بيته، ثم يخرج فلا يفرق بين اثنين، ثم يصلي ما كتب له، ثم ينصت إذا تكلم الإمام، إلا غفر له ما بينه وبين الجمعة الأخرى» . رواه البخاري. ሰልማን -ረዲየላሁ ዐንሁ- እንደዘገበው ፡- የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ​​ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- “አንድ ሰው በጁምዓ ቀን የቻለውን ያህል ራሱን በማጥራት አይታጠብም፣ ከቅባት ወይም ከቤቱ ካለው ሽቶ አይቀባም፣ ከዚያም በሁለት ሰዎች መካከል ሳይለያይ መስጂድ አይመጣም ፤ ከዚያም ለርሱ የተጻፈውን ያክል አይሰግድም፤ ከዚያም ኢማሙ ሲናገር አያዳምጥም፣ በዚህ እና  ባለፈው ጁምአ መካከል የነበረው (ወንጀል) ይቅር የተባለ ቢሆን እንጂ።" (ቡኻሪ ዘግበውታል) @fivekjemaa