uk
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Відкрити в Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Показати більше
1 161
Підписники
Немає даних24 години
+37 днів
+730 день
Архів дописів
ለ5 ኪሎ ካምፓስ የ2018 ዓ.ል ተመራቂ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ! 🎓 ​ቀደም ሲል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በኩል ልዩ የምረቃ ሪቫን እና ባይንደር  ስታዙ ለነበራችሁ የ5 ኪሎ ካምፓስ ተማሪዎች በሙሉ፤ ህብረቱ ያዘጋጃቸውን ውብና ጥራት ያላቸውን መለያዎች የ5 ኪሎ ጀምዓ በይፋ ተረክቧል። ​የምረቃ ቀናችሁን በጀምዓችን መለያ ይበልጥ ደምቃችሁ ለመገኘት ያዘዛችሁትን ሪቫን እና ባይንደር ከታች በተቀመጠው ስልክ ቁጥር እየደወላችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑንም እናበስራለን። ​ቀድማችሁ ላላዘዛችሁ ተማሪዎች ደግሞ አሁንም ቢሆን ጥራት ያለው ሪቫን እና ባይንደር መግዛት እና መረከብ የምትችሉ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን ። ​ሌላ ቦታ በመሄድ ሳይንገላቱ የራሳችንን መለያ ይዘን ውብ በሆነ መንገድ ደስታችንን እናከብራለን! 🎉 ​📞 ለማዘዝ ወይም ለመረከብ በዚህ ስልክ ቁጥር ይደውሉ፡ ​🔖 ወንዶች ╰┈➤• 0905877461 Mesud (@savior78) ​🔖 ሴቶች በዚህ ቦት ማዘዝ ወይም መረከብ ትችላላችሁ ╰┈➤• @fivekjemaa_bot ​አላህ መልካም የምረቃ ዕለት እንዲያደርግላችሁ እና ለቀጣዩ ህይወታችሁም ስኬትን እንዲለግሳችሁ የጀምዓችን የዘወትር ምኞት ነው‼️ ​@fivekjemaa

abdul-wadood-haneef-018.mp329.05 MB

🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ ﷺ 🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟 ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት "ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።" ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልባችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው። ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️ اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

عن سلمان - رضي الله عنه - قال: قال رسول الله - صلى الله عليه وسلم -: «لا يغتسل رجل يوم الجمعة، ويتطهر ما استطاع من طهر، ويدهن من دهنه، أو يمس من طيب بيته، ثم يخرج فلا يفرق بين اثنين، ثم يصلي ما كتب له، ثم ينصت إذا تكلم الإمام، إلا غفر له ما بينه وبين الجمعة الأخرى» . رواه البخاري. ሰልማን -ረዲየላሁ ዐንሁ- እንደዘገበው ፡- የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ​​ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- “አንድ ሰው በጁምዓ ቀን የቻለውን ያህል ራሱን በማጥራት አይታጠብም፣ ከቅባት ወይም ከቤቱ ካለው ሽቶ አይቀባም፣ ከዚያም በሁለት ሰዎች መካከል ሳይለያይ መስጂድ አይመጣም ፤ ከዚያም ለርሱ የተጻፈውን ያክል አይሰግድም፤ ከዚያም ኢማሙ ሲናገር አያዳምጥም፣ በዚህ እና  ባለፈው ጁምአ መካከል የነበረው (ወንጀል) ይቅር የተባለ ቢሆን እንጂ።" (ቡኻሪ ዘግበውታል) @fivekjemaa

The Virtue of Friday: An Hour When Du’a Is Accepted Shaykh Abdus-Salam As-Shuway’ir حفظه الله https://t.me/fivekjemaa

📢 ልዩ የፓነል ውይይት በቲክቶክ ! ! ! 📢 ድምፃችንን ከፍ አድርገን የምናሰማባቸውን መድረኮች አብዝቶ ለፈጠረው አምላክ ምስጋና የተገባው ይሁንና በዕለተ እሁድ ሰኔ 7፣ 2017 ዓ.ል የመሰብሰብ
📢 ልዩ የፓነል ውይይት በቲክቶክ ! ! ! 📢 ድምፃችንን ከፍ አድርገን የምናሰማባቸውን መድረኮች አብዝቶ ለፈጠረው አምላክ ምስጋና የተገባው ይሁንና በዕለተ እሁድ ሰኔ 7፣ 2017 ዓ.ል የመሰብሰብ እና የመወያየት መብታችንን በመነፈጋችን ምክንያት፣ በሰፊው ተደራሽ ወደ ሆነው የቲክቶክ መድረክ ያዞርነውን ታሪካዊ የፓናል ውይይት ዝርዝር መረጃ ይዘን መጥተናል! 📌 ርዕስ፡- "በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሙስሊም ተማሪዎች መብት" 🎙 በዚህ አንገብጋቢ እና ወቅታዊ ርዕስ ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ የሚሰጡን እና ውይይት የሚያደርጉልን ልዩ የክብር እንግዶች ጋብዘናል... እንግዶቻችን ማን ይሆኑ? 🤔 በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል፤ ዝግጅታችንን ይጠብቁ! 🗓 ቀን፡ ሰኞ፣ ሰኔ 22 (Monday, 29 June) ⏰ ሰዓት፡ ከምሽቱ 03፡00 ሰዓት ✨ "እውቀትን መፈለግ መብት ነው፤ እምነትንም በክብር መተግበር እንዲሁ!" በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ያላችሁ ተማሪዎች እና መላው ሕዝበ ሙስሊም በያላችሁበት ሆናችሁ በቲክቶክ ገፃችን ላይ እንድትታደሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። እስከዚያው ይህን መልዕክት ለሁሉም በማጋራት የድምፃችን አካል ይሁኑ! የቲክቶክ ገፃችንን Follow በማድረግ ዝግጅቱን ይጠብቁ፦ https://www.tiktok.com/@aaumsu ✊ እወቅ፤ ጠይቅ፤ አስከብር። @aaumsu

ከዚህን በፊት በህብረታችን በኩል ሪቫንና ባይንደር እንዳዘጋጀን ገልፀንላቹ እንደነበር ይታወሳል። አሁን ላይ ተሰርቶ ስለተጠናቀቀ ኢንሻአላህ አዛቹ ለከፈላቹ እህትና ወንድሞች ነገ በየግቢዎቻቹ እንዲደርሳችሁ የምናደርግ ይሆናል። በተጨማሪም ለመውሰድ ተመዝግባቹ ክፍያ ላልከፈላቹ እህትና ወንድሞች ክፍያውን አጠናቃቹ እንድትወስዱ ለማስታወስ እንወዳለን። በተጨማሪ አሁንም መውሰድ የምትፈልጉ እህትና ወንድሞች የተዘጋጀው ባይንደርና ሪቫን በእለቱ ደምቀንና እሴቶቻችንን የምናሳይበት ልዩ ሪቫንና ባይንደር ስለሆነ ስማችሁን ከነ አባት ስም ጋር፣ ካምፓሳችሁን እና ስልክ ቁጥራቹን በቴሌግራም ቦታችን @Niqab_issueBot በመላክ በምንልክላቹ አካውንት ክፍያ ፈፅማቹ መቀበል እንደምትችሉ በደስታ ለማሳወቅ እንወዳለን። @aaumsu

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته የነገውን ፆም መፆም እንዳይረሳ 🔵 አቡ ሰዒድ አል-ኹድሪይ(ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተዘገበው:- ረሱል() እንዲህ ብለዋል-
የዓሹራእን ቀንም የጾመ ሰው የአንድ ዓመት ወንጀሉ ይማርለታል።»
​📚ኢብኑ ዐሳኪርም በ«ታሪኽ ዲማሽቅ» (43/230)ዘግበውታል። 🔷 ​አቡ ሰዒድ አል-ኹድሪይ(ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተዘገበው:- አንድ ሰው ነቢዩን ﷺ እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፦
"የአላህ መልክተኛ ሆይ! የዓሹራእን ቀን ስለሚጾም ሰው ምን ይላሉ?" እሳቸውም«አስረኛውን ቀን መፆም ከአንድ ዓመት ጾም ጋር እኩል ነው » አሉ።
📚​ ኢብኑ ሒባን( 394) ላይ ዘግበውታል። 🔵 ዐብዱላህ ኢብን ኢማሚ አህመድ እንዲህ ብለዋል፦ አባቴ(አህመድ ቢን ሀንበል) እንዲህ ሲሉ ሰማኋቸው፦
«ዐብዱረሕማን ቢን መህዲን በሕልሜ አየሁትና፦ "አላህ ምን አደረገህ?" አልኩት። እርሱም፦ "ማረኝ፣ ወደ እሱ አቀረበኝ፣ ማዕረጌንም ከፍ አደረገው" አለ። እኔም፦ "በምን ምክንያት?" አልኩት። እርሱም፦ "የዓሹራእን ቀን፣ ከእሱ በፊት ያለውን ቀንና ከእሱ በኋላ ያለውን ቀን አዘውትሬ በመጾሜ ምክንያት ነው" አለ።»
📚 ​"አል-ለፍዘል ሙከረም ቢፈድሊ ዓሹራኢል ሙሐረም" ሊኢብኑ ዘይድ (ረሂመሁ ላህ)

10ኛውን ብቻ መፆም ይቻላል። ~ ‏ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ رَحِمَهُ اللهُ እንዲህ ይላሉ፦ * وَصِيَامُ يَوْمِ عَاشُورَاءَ كَفَّارَةُ سَنَةٍ ، * وَلَا يُكْرَهُ إفْرَادُهُ بِالصَّوْمِ. * "የዓሹራእ ቀን ፆም የአንድ አመት ወንጀል የሚያሳብስ ነው። * (እለቱን) በፆም መነጠል አይጥጠላም።" 📕 [አልፈታወል ኩብራ፡ 5/378] = የቴሌግራም ቻናል፡- ©IbnuMunewor

የንፅፅር ስልጠና ለ5 ኪሎ ተማሪዎች‼️ ቀደም ሲል ለ6 ኪሎ ግቢ ተማሪዎች ብቻ ተወስኖ ተዘጋጅቶ የነበረው ልዩ የክረምት ኦንላይን የንጽጽር ትምህርት ስልጠና፤  ከተማሪዎች ከፍተኛ ፍላጎት በመነሳት ከኢርሻድ የንፅፅር ቡድን ጋር ውይይት ተደርጎ ምዝገባው ለሁሉም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ክፍት እንዲሆን ተወስኗል!! በመሆኑም 5 ኪሎ ጀምዓ ለ5ኪሎ ተማሪዎች በዚህ የንጽጽር ትምህርት ስልጠና መውሰድ ለሚፈልጉ ከፍተኛ ፍላጎት ላላቸው ፤ ተመዝግበው ማጣሪያውን ለሚያልፉ 5 ወንድ እና 5 ሴት ተማሪዎች አወዳድሮ ይህንን ዕድል እንዲጠቀሙ አመቻችቷል። ምዝገባው እስከ ነገ ይቆኛል ስለዚህ ​የምዝገባው ማብቂያ  ከመድረሱ በፊት ይህንን ወርቃማ የዕውቀት ማዕድ በመቀላቀል የክረምት ጊዜዎን በቁምነገር እንዲያሳልፉ ጥሪያችን ነው ። ማሳሰቢያ ፦ ​ማጣሪያው የሚካሄደው ፎርም ላይ በሚሞላው መረጃ መሰረት ስለሆነ ተመዝጋቢዎች በጥንቃቄና በታማኝነት እንድትሞሉ በጥብቅ እናሳስባለን። ጊዜው ሳይረፍድ አሁኑኑ ተመዝገቡ! ​🔖 መመዝገቢያ ፎርም፦ ╰┈➤• የንፅፅር ስልጠና መመዝገቢያ @fivekjemaa

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ነገ ፆም እንዳይረሳ 🔵 ከዐብዱላህ ቢን ዐባስ እንደተዘገበው:- ✨ ​«የአላህ መልእክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይሁን) ዘጠነኛውን ቀን (የሙሐረም ወር ዘጠነኛውን ቀን/ታሱዓእን) ይጾሙ ነበር።» 📝 ሶሒሕ  (صحيح) ​ 📚 ኢማም ሙስሊም (1133)፣ አቡ ዳውድ (2446) እና ቲርሚዚይ (754) 👉ለሚፆሙ ሁሉ ጠቃሚ ማስታወሻ❗️ ~ የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለምእንዲህ ብለዋል፡- ❝ሱሁርን መብላት በረካ አለው፤ ስለዚህ ከእናንተ አንዳችሁ አንዲት ጉንጭ ውሃ እንኳን ቢሆን ሳይጎነጭ እንዳይተወው። ምክንያቱም አላህና መላኢካዎቹ ሱሁር በሚበሉ ሰዎች ላይ ሰለዋት ያወርዳሉ (ዱዓ ያደርጋሉ)።❞ @fivekjemaa

እስክርቢቶውን የጣለ እስክርቢቶ ተሸለመ ! ! ! ከ39 ቀናት በፊት ... በጁምዓ ቀን ... ሙስሊም ተማሪዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ፊት ለፊት ጥያቄያቸውን የሚሰማ አካል ካለ
+3
እስክርቢቶውን የጣለ እስክርቢቶ ተሸለመ ! ! ! ከ39 ቀናት በፊት ... በጁምዓ ቀን ... ሙስሊም ተማሪዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ፊት ለፊት ጥያቄያቸውን የሚሰማ አካል ካለ በማለት ተሰባስበው ነበር። አቤት የሚል ጠፍቶ ባለበት ፀሐይ ለምሽት ቦታዋን ለቀቀች። የፌደራል ፖሊሶችም ተማሪዎች ከቦታው ተነስተው እንዲገቡ ግፊት ማድረግ ጀመሩ። ማስፈራሪያዎች እና ዛቻዎችም ቀጠሉ። በዚህ መሐል በአምስት ኪሎ ፍሬሽማን ተማሪ የነበረ "እስክርቢቶ የጣለ አለ?!" - ሲል ጠየቀ። ተማሪውም በዝምታ ውስጥ "ሊያስጥሉኝ ይሞክራሉ፤ ግን አልጣልኩም፤ አልጥልምም።" - የሚልን መልዕክት ካለበት በፅናት በመቆም አስመሰከረ። በዚያን ሰዓት ይህንን ጥልቅ መልዕክት ያስተላለፈውን ተማሪ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች እና በሕብረቱ የ5ኪሎ ጀመዓ እስክርቢቶ እና ሁለት መፅሐፍ ሸልመውታል። እስክርቢቶ የጣለ አለ?! እስክርቢቷችንን አንጥልም። @aaumsu

✴️ ኢንሻአላህ የቂርአት ፕሮግራም የሚሆነው ✨ ሰኞ እና ማክሰኞ ከዒሻ በኋላ ማታ 2:45 ✨ እሮብ እና ሀሙስ ከፈጅር በኋላ 12:10 🔵 የቂርዐት ቻናል https://t.me/Qirat4k 🔴 ሀሳብ እና አስተያየት እና ኪታብ ያልደረሳችሁ ልጆች 👇 @FourkiloAnswerbot

السلام عليكم POLL እኩል ስለሆነ 1ኪታብ ከፈጅር በኋላ 1ኪታብ ከዒሻ በኋላ ታስቧል።

የአንድ ዓመት ወንጀል ማበሻው ወርቃማ ዕድል! 🥣 ሙሀረም 9...የአሹራ ፆም ነገ ይጀምራል‼️ሁላችንም የሰው ልጆች ነን፤ እንሳሳታለን፣ እንዘነጋለን። አንዳንድ ጊዜ በትናንትናው ማንነታችን ውስጥ የሰራናቸው ስህተቶችና ትናንሽ ወንጀሎች በትከሻችን ላይ ከብደው ሲሰሙን፣ "እንዴት ይሆን ከዚህ ሸክም የምገላገለው?" ብለን ልባችን ይጨነቅ ይሆናል። ነገር ግን የጌታችን አላህ እዝነትና ቸርነት ከእኛ ድካም በላይ ሰፊ ነው። የከበደንን የወንጀል ሸክማችንን ሊያቀልልን፣ አዲስ የሕይወት ገጽ እንድንከፍት ድንቅ ዕድሎችን አዘጋጅቶልናል።           አሹራ 🤩 ውዱ ነቢያችን ﷺ ልብን የሚያረሰርስና ተስፋን የሚዘራ ታላቅ ብስራት ሲነግሩን እንዲህ ብለዋል፦
​﴿صيامُ يومِ عاشوراءَ፣ إنِّي أحتَسِبُ على اللَّهِ أن يُكَفِّرَ السَّنةَ الَّتي قبلَهُ﴾ ​“የአሹራ ቀን ፆም ያለፈውን አመት ኃጢአት እንደሚያብስ ከአላህ እጠብቃለሁ።” (ሙስሊም ዘግበውታል: 1162)
አስቡት! የአንድ ቀን ፆም… የጥቂት ሰዓታት ትዕግስት… ሙሉ የ365 ቀናት ስህተቶቻችንን፣ ድክመቶቻችንን እና በወንጀል የቆሸሸውን የልብ ገጻችንን ያጥበዋል። ይህ ለነፍሲያችን የተሰጠ እንዴት ያለ ታላቅ ስጦታ ነው? 🥰 ይህንን ታላቅ ፈዳኢል ለማግኘት ፣ የነቢያችንን ﷺ ፈለግ ሙሉ በሙሉ ለመከተልና የላቀ ደረጃ ላይ ለመድረስ ከ10ኛው ቀን (#ከአሹራ) በፊት ያለውን 9ኛውን ቀንም አብረን እንድንፆም አሳስበውናል። ከመሞታቸው በፊት በነበረው ዓመት ያንን ትልቅ ናፍቆት እንዲህ ሲሉ ገልጸውት ነበር፦ ​﴿فَإِذَا كَانَ الْعَامُ الْمُقْبِلُ - إِنْ شَاءَ اللَّهُ - صُمْنَا الْيَوْمَ التَّاسِعَ﴾ ​“የሚቀጥለው ዓመት ከደረስኩ በአላህ ፍቃድ የአሹራን ቀን ፆም ዘጠነኛውን ጨምሬ እፆማለሁ።” (ሙስሊም ዘግበውታል: 1134) ስለዚህ አህባቢ ይህ ወርቃማ ዕድል እንዳያመልጠን ዛሬውኑ ራሳችንን እናዘጋጅ። ዱንያ በሩጫዋ ብታደክመንም፣ እንዲህ ባሉ የኢባዳ ቀናት ላይ ቆም ብለን ነፍሲያችንን ማደስ ይኖርብናል። ​👤 የመልካም ስራ አስተዋሽ እንሁን! ሌሎች ወንድም እህቶቻችንን በማስታወስ የሰዎችን መፆምና ወንጀላቸው መማር ሰበብ እንሁን ። መልካምን ነገር ያመለከተ ሰው ልክ እንደሰራው ይቆጠራል! ©Ke_quran_ayah @fivekjemaa

የንፅፅር ስልጠናውን ለሁሉም! ቀደም ሲል ለ6 ኪሎ ግቢ ተማሪዎች ብቻ ተወስኖ ተዘጋጅቶ የነበረው ልዩ የክረምት ኦንላይን የንጽጽር ትምህርት ስልጠና፤ ከሌሎች ካምፓሶች በደረሱን በርካታ ጥያቄዎችና ከተማሪዎች ፍላጎት በመነሳት ከኢርሻድ የንፅፅር ቡድን ጋር ውይይት ተደርጎ ምዝገባው ለሁሉም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ክፍት እንዲሆን ተወስኗል! ​የምዝገባው ማብቂያ ሰዓት ከመድረሱ በፊት ይህንን ወርቃማ የዕውቀት ማዕድ በመቀላቀል የክረምት ጊዜዎን በቁምነገር ያሳልፉ። ማሳሰቢያ፦ ​ማጣሪያው የሚካሄደው ፎርሙ ላይ በሚሞላው መረጃ መሰረት ስለሆነ ተመዝጋቢዎች በጥንቃቄና በታማኝነት እንድትሞሉ በጥብቅ እናሳስባለን። ጊዜው ሳይረፍድ አሁኑኑ ተመዝገቡ! ​🔖 መመዝገቢያ ፎርም፦ ╰┈➤• የወንዶች መመዝገቢያ            ∘₊✧──────✧₊∘ ╰┈➤• የእህቶች መመዝገቢያ ለማንኛውም ጥያቄ በዚህ ቦት ያናግሩን @Valid_Qireat_bot @AAU6kilojemea

🚨 1 ቀን ብቻ ቀረው! 🚨 የታላቁ እና አጓጊው የ ንጽጽር ትምህርት ዕድል ምዝገባው ሊጠናቀቅ 1 ቀን ብቻ ቀረው! እስካሁን ያልተመዘገባችሁ እህት ወንድሞች በሙሉ፥ ይህ ድንቅ ዕድል በድጋሚ ላይገኝ
🚨 1 ቀን ብቻ ቀረው! 🚨 የታላቁ እና አጓጊው የ ንጽጽር ትምህርት ዕድል ምዝገባው ሊጠናቀቅ 1 ቀን ብቻ ቀረው! እስካሁን ያልተመዘገባችሁ እህት ወንድሞች በሙሉ፥ ይህ ድንቅ ዕድል በድጋሚ ላይገኝ ስለሚችል ፈጥናችሁ በመመዝገብ ይህንን የዕውቀት እና የልምድ ማዕድ እንድትቀላቀሉ እና እንድትጠቀሙበት አጥብቀን እናሳስባለን። በልዩ ሁኔታ  የተዘጋጀ   "የሚዲያ አጠቃቀም ለዳዕዋ"የሚል እጅግ ወሳኝ እና ወቅታዊ ስልጠና እንዳለው እንዳትረሱ! ታዲያ ምን ትጠብቃላችሁ? 🤔 ጊዜው ሳይረፍድ አሁኑኑ ተመዝገቡ! 👇 ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ 👇 ➤• የወንዶች መመዝገቢያ            ∘₊✧──────✧₊∘ ╰┈➤• የእህቶች መመዝገቢያ ⏳ ፈጥነው ይመዝገቡ! ለበለጠ መረጃ @Valid_Qireat_bot @AAU6kilojemea

በእውነቱ የዩኒቨርሲቲያችን አስተዳደር ሁሉንም የዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ አካታች የሆኑ፣ የተማሪዎችን ሁለንተናዊ አቅም የሚያሳድጉ እና ጠቃሚ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት እንዲሁም የተማሪዎችን መብት ማክበርና
በእውነቱ የዩኒቨርሲቲያችን አስተዳደር ሁሉንም የዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ አካታች የሆኑ፣ የተማሪዎችን ሁለንተናዊ አቅም የሚያሳድጉ እና ጠቃሚ  ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት እንዲሁም የተማሪዎችን መብት ማክበርና ማስከበር  ላይ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ፤ እንዲህ ባሉ የሙዚቃና የጭፈራ ድግሶች ላይ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ መገኘቱ በእጅጉ ያሳዝናል። ​ውድ የግቢያችን ሙስሊም ተማሪዎች (በተለይም ተመራቂዎች)፤ ​እኛ ሙስሊሞች ነን! በእስልምናችን ደግሞ ከእንዲህ ያሉ አላህ ከማይወደዳቸው፣ ለጊዜያዊ ስሜት ተብለው ኢማንን ከሚያዳክሙና የጭፈራ ስፍራዎች ራሳችንን እንድንጠብቅ ታዘናል። ለአመታት የደከማችሁበትን እና የለፋችሁበትን ይህንን ታላቅ የምርቃት ስኬት በአላህ እገዛ እዚህ ስላደረሳችሁ ልታመሰግኑትና በሀላል መንገድ ልታከብሩት ይገባል እንጂ፤ ስኬታችሁን በወንጀልና በጭፈራ ማክበር የለባችሁም። ​ስለሆነም ማንም ሙስሊም ተማሪ በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ እንዳይገኝና ራሱን ከእንዲህ አይነት ቦታዎች እንዲያርቅ እናሳስባለን። በምትኩ ጊዜያችንን ጠቃሚ በሆኑ ነገሮች እና ለቀጣዩ ህይወታችን ዱዓእ በማድረግ እናሳልፍ። @aaumsu

Notice❗️ Exit exam results are out for some departments, while others are still pending. You can use this link to check your results https://result.ethernet.edu.et If you get a "404 Not Found" error, it is likely due to server overload. Share @AAUMEREJA

✴️ «የዐሹራ ፆም» ​📚 ትርጉም እና አዘጋጅ፦ ኢብን አቢ ዱንያ ​📝 ቅንብር፦ አቡ ኡሳማ ዘይድ 🔵የዘንድሮ ዐሹራእ የሚፆሙት ቀናት ✨ሙሀረም  9 = እሮብ ✨ሙሀረም  10 = ሀሙስ ✨ሙሀረም   11 = ጁምዓ ነው፡፡ t.me/ibnabidunyaa

5killo Jem'a official Channel - Статистика та аналітика Telegram каналу @fivekjemaa