uk
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Відкрити в Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Показати більше
1 162
Підписники
Немає даних24 години
+37 днів
+730 день
Архів дописів
"ሕልሜ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን መቀላቀል ቢሆንም ኒቃብን የሚከለክልን መመሪያ ማውጣቱ እና በኒቃቢስቶች ላይ የሚደርሰው እንግልት ግን ሌላን እንዳስብ እያደረገኝ ነው። ስለሆነም የሚመለከታችሁ አካላት መብታችንን አስከብሩና ሕልማችንን እናሳካ።" - ከ Moonlight አካዳሚ እንደ አጠቃላይ አንደኛ ወጥታ የወርቅ ተሸላሚ የሆነችው ኒቃቢስቷ አስማ አህመድ ዩኒቨርስቲው ያወጣው ጨቋኝ መመሪያ ተፅዕኖ በውስጡ ከሚማሩት ተማሪዎች አልፎ ሕልማቸውን በዩኒቨርስቲው ለመማር ለሚያደርጉት ጭምር ነው። "ኒቃብን ለብሶ መማር አይቻልም!" - የሚልን መመሪያ ሲያወጣ ኒቃባቸውን ለብሰው የሚማሩትን ሁሉ ወደ ዩኒቨርስቲው አትምጡ የሚል መከልከያ እያስቀመጠ ነው። ለዚህም ነው ጥያቄው የሁሉም ሙስሊም ማህበረሰብ የሆነው። ለዚህም ነው ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፤ ከወላጅ እስከ ሰራተኛ ስለ ሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጉዳይ መጠየቅ ያለበት። አንድም ተማሪ ቢሆን ሙስሊም ስለሆነ ከትምህርት ሊጨናገፍ አይገባም። አንድም ተማሪ ቢሆን በእስልምናው ምክንያት ከትምህርት ሊታገድ አይገባም። አንዲት እህትም ብትሆን በኒቃቧ ምክንያት ህልሟ ሊከስም አይገባም። መብቷ ተከብሮ እንድትማር ማድረጉ የመንግስት ግዴታ ነው። ኒቃቧን እንደለበሰች እንድትማር ማመቻቸቱ የመጅሊስ ሀላሊፊነት ነው። ምንም አይነት የመብት ጥሰት ሳይደርስባት በነፃነት እንድትማር ማድረጉ የእኔ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የሁላችን ሀላፊነት ነው። የዚህ ትውልድ፤ የጥዬቄ አለን ትውልድ ሀላፊነት ነው። በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚደርሰው የመብት ጥሰት ወደ ቀጣዩ ትውለድ አይሻገርም! ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

ግንቦት ሰባት ላይ ነበር ያ ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ የተጻፈበት የሙስሊም ተማሪዎች የፅናት እና የክብር ድምፅ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ደጅ በኃይል ያስተጋባበት እለት! "መብታችን ይ
+1
ግንቦት ሰባት ላይ ነበር ያ ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ የተጻፈበት የሙስሊም ተማሪዎች የፅናት እና የክብር ድምፅ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ደጅ በኃይል ያስተጋባበት እለት! "መብታችን ይከበር፣ ግፉ ይቋጭ፣ ጥያቄ አለን!" በማለት በቁርጠኝነት የተሰበሰቡት እነዚያ ጀግና ወጣቶች፣ የቀኑን አስገንጣይ ፀሐይና የምሽቱን ውሽንፍር ቅዝቃዜ በታላቅ ትዕግስት ተቋቋሙት። እስከ ምሽቱ 4:30 ድረስ የቆሙት ለአላማቸው በነበራቸው ጽኑ እምነት እንጂ በሰዎች ልግስና አልነበረም። ለአመራሮች ግዴለሽነትና ለፌደራሎች ማስፈራሪያ ሳይንበረከኩ፣ በሰላምና በስነ-ምግባር የታገዘ፣ ከደርዘን ጩኸቶች በላይ የሚናገር ታላቅ የዝምታ መልዕክትን ለአለም አስተላለፉ። ዛሬ ግንቦት አልፎ ሰኔ፣ ሰኔም ተሻግሮ ሐምሌ ሰባት ሆኗል። ያ ታሪካዊና አንገት የማያስደፋው የፅናት ውሎ ዛሬ ሁለተኛ ወሩን ሙሉ ደፍኗል። በዚያ ምሽት ከሰላም ሚኒስቴር፣ ከዩኒቨርስቲው አመራር፣ ከሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ፣ ከፀጥታ አካላትና ከመጅሊስ ተወካዮች ተማሪው ፊት ቆመው፣ ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ምድርና ሰማዩን እያማለሉ ቃል ገብተው ቢሄዱም፣ ያንን ቃላቸውን በድርጊት መተርጎም ግን አልቻሉም። ለሁለት ሙሉ ወራት ቃል-አባይ ሆነው ቢያልፉም፣ በተማሪው ልብ ውስጥ የተቀጣጠለው የፍትህ ሻማ ግን ቅንጣት ታህል አልፈዘዘም። ይልቁኑም የመብት ጥያቄያችን ይበልጥ ጎልቶ፣ ወኔያችን ታድሶና አንድነታችን ጠንክሮ “ጥያቄ አለን!” የሚለው የነፃነት ድምፅ ከምንጊዜውም በላይ እየደመቀ እንዲቀጥል አድርጎታል። ፍትሐዊና ዘላቂ መልስ እስኪመጣ፣ ሰብአዊና እምነታዊ መብቶቻችን ተከብረው በሰላም መማር እስክንችል ድረስ ይህ ድምፅ አይጠፋም!! ትግላችንም አይታጠፍም! ጥያቄ አለን ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ! ጥያቄ አለን መብቶቻችን ተከብረው መማር እስክንችል!! @aaumsu

👉Join us for an informative session! Here's the meeting link: https://meet.google.com/hvx-zvnd-uxy

Join the 5 Killo Jamma’ah Department Selection Orientation happening TONIGHT! 🗓️ Date: TODAY, July 14 ⏰ Time: 3:00 LT (9:00
Join the 5 Killo Jamma’ah Department Selection Orientation happening TONIGHT! 🗓️ Date: TODAY, July 14 ⏰ Time: 3:00 LT (9:00 PM EAT) 📍 Platform: Google Meet Don't miss out on crucial insights that will shape your engineering career. Click the link below to stay updated and grab the meeting link: 🔗 Join here: https://t.me/fivekjemaa

ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከኢትዮጵያ ሙስሊም ህግ ባለሙያዎች ማህበር ከሰብአዊ መብት ጋር በተያያዘ የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ! ሁላችሁም ሰብር አድርጋቹ ሙሉት👇
📢 Call for Participants | Addis Ababa University Female Muslim Students
  Assalamu alaikum warahmatullahi wabarakatuh. 🌿   As promised, the EMLA Human Rights Survey is now open. We kindly invite all female Muslim students of Addis Ababa University to participate in this important academic research on religious identity, equality, and inclusion within the university. ⏱️ The survey takes only 10–15 minutes to complete. Your responses are anonymous, confidential, and will contribute to evidence-based recommendations that reflect the experiences of our community. 🔗 Survey Link: https://ee.kobotoolbox.org/x/mW1YBEzG. We would greatly appreciate it if you could complete the survey and share it with other eligible AAU female Muslim students. Jazakum Allahu Khayran for your valuable time and support.   #EMLAHumanRightsSurvey#AddisAbabaUniversity #FemaleMuslimStudents #HumanRights #ReligiousFreedom #AcademicResearch @aaumsu

🚀 THE WAIT IS ALMOST OVER, PRE-ENGINEERING STUDENTS! 🚀 The crossroads of choosing your department can be overwhelming, but
🚀 THE WAIT IS ALMOST OVER, PRE-ENGINEERING STUDENTS! 🚀 The crossroads of choosing your department can be overwhelming, but you don’t have to navigate it alone! 🧭✨ Our highly anticipated Department Selection Orientation Session is officially happening! Whether you are leaning towards Electrical, Biomedical, Software, Civil, Mechanical, or Chemical Engineering, this is your ultimate chance to get the real, unedited breakdown of what to expect by your seniors. 🗓️ Date: Tuesday, July 14, 2026 ⏰ Time: 3:00 LT in the evening 📍 Platform: Google Meet (Online) 🔗 How to join? The official Google Meet link will be dropped right here in our channel exactly at 3:00 LT. Make sure your notifications are turned ON so you don't miss the link! See you all there! 👉 t.me/fivekjemaa

🔹 Narrated Al-Aswad: That he asked `Aisha, "What did the Prophet ﷺ use to do in his house?" She replied, "He used to keep himself busy serving his family and when it was the time for prayer he would go for it." «كَانَ يَكُونُ فِي مِهْنَةِ أَهْلِهِ – تَعْنِي خِدْمَةَ أَهْلِهِ – فَإِذَا حَضَرَتِ الصَّلَاةُ خَرَجَ إِلَى الصَّلَاةِ» 📖 Reference: Sahih al-Bukhari 676 @fivekjemaa

🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا
🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ ﷺ 🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟 ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት "ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።" ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልባችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው። ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️ اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

🚨COMING SOON....
🚨COMING SOON....

🚨COMING SOON......
🚨COMING SOON......

🌟 ቁርዓንን ዘውትር አንብበው! ከአቡ ሙሳ አል‐ዓሸዓሪ (ረ.ዐ) ተይዞ፡ ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿تَعاهَدُوا هذا القُرْآنَ، فَوالذي نَفْسُ مُحَمَّدٍ بيَدِهِ لَهو أشَدُّ تَفَلُّتًا مِنَ الإبِلِ في عُقُلِها﴾ “ይህንን ቁርዓን አዝውትሩት። የሙሐመድ ነፍስ በእጁ በሆነችው ጌታ እምላለሁ! ከታሰረች ግመል ወይም በእስሯ ውስጥ ካለች ግመል የበለጠ የማፈትለክ ባህሪ አለው።” 📚 ቡኻሪ (5033) ሙስሊም (791) ዘግበውታል

🌟 ቁርዓንን ዘውትር አንብበው! ከአቡ ሙሳ አል‐ዓሸዓሪ (ረ.ዐ) ተይዞ፡ ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿تَعاهَدُوا هذا القُرْآنَ، فَوالذي نَفْسُ مُحَمَّدٍ بيَدِهِ لَهو أشَدُّ تَفَلُّتًا مِنَ الإبِلِ في عُقُلِها﴾ “ይህንን ቁርዓን አዝውትሩት። የሙሐመድ ነፍስ በእጁ በሆነችው ጌታ እምላለሁ! ከታሰረች ግመል ወይም በእስሯ ውስጥ ካለች ግመል የበለጠ የማፈትለክ ባህሪ አለው።” 📚 ቡኻሪ (5033) ሙስሊም (791) ዘግበውታል

🔵 የሚገርም ነው ነገሩ እንዲህ ነው ✴️ ​በአንድ ቀበሮ ጭራ ላይ ከባድ ድንጋይ ወድቆ ጭራውን ቆረጠው። ✨ ​ሌላ ቀበሮ አየውና፦ “ጭራህን ለምን ቆረጥከው?” ብሎ ጠየቀው። ✨ ​እርሱም፦ “በአየር ላይ እንደምበር ያህል ይሰማኛል፤ ምንኛ ታላቅ ደስታ መሰለህ!” አለው። 🔴 ​ይህንን ሲሰማ (ሁለተኛውም) ጭራውን እንዲቆርጥ አደረገው! ​ነገር ግን ብርቱ ሕመም በተሰማውና እንደተባለውም ምንም ዓይነት ደስታ ባላገኘ ጊዜ፦ “ለምን ዋሸህብኝ?” ሲል ጠየቀው። ✨​የመጀመሪያው ቀበሮ እንዲህ ሲል መለሰ፦
“ለሌሎቹ ቀበሮዎች ስለ ሕመምህ ከነገርካቸው ጭራቸውን አይቆርጡም፤ በእኛም ላይ ያፌዙብናል።”
⚫️ ​በመሆኑም ያገኙትን ቀበሮ ሁሉ ስለሚያገኙት (የሐሰት) ደስታ መናገራቸውን ቀጠሉ፤ ይህም በመሆኑ አብዛኞቹ ቀበሮዎች ጭራ አልባ እስኪሆኑ ድረስ ሆነ! ​ከዚያ በኋላ ጭራ ያለው ቀበሮ ባዩ ቁጥር ያፌዙበትና ይንቁት ጀመር!
(ብልሽት (ፈሳድ) በሰፈነ ጊዜ፣ ሰዎች ደጋግ ሰዎችን በበጎነታቸውና በደግነታቸው ማነወሪያ ያደርጓቸዋል! መሃይማንና ሞኞቹም መሳለቂያ ያደርጓቸዋል።)
🔵 ​ኢማም ሹረይሕ (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፦
“በሰዎች ላይ አንድ ዘመን በእርግጥ ይመጣል፤ ዛሬ አመጸኛ (ፋጂር) በአመጽነቱና በክፋቱ እንደሚነቀፈው ሁሉ፣ አማኝም በእምነቱ የሚነቀፍበት፤ እንዲያውም አንድን ሰው ለማጣጣል ሲባል ‘አንተ እኮ አማኝና አሊም ደረሳ ነህ’ እስኪባለው ድረስ።”
🔷​ብልሹ ማኅበረሰብ ለሚያስተካክሉና ለሚገሥጹ  ሰዎች የሚለጥፍላቸው መጥፎ ነገር በታጣ ጊዜ፣ በእነርሱ ውስጥ ባለው እጅግ ውብና መልካም በሆነው ነገር ያነውራቸዋል... ✴️(​የሉጥ ሕዝቦች):- የሉጥን ቤተሰቦች ከመንደራችሁ አስውጡ፤ እነሱ ንጽሕናቸውን የሚጠብቁ ሰዎች ናቸው አሉ  ንፅህናቸውን በመጠበቃቸው ብቻ በአካባቢው ባይተዋር ተደረጉ 🔴 ​ዛሬም ወደ እርቃንነት (መገላለጥ) መጣራትና መሸፈኛን(ኒቃብን)ና ጥንቁቅነትን (ዒፋን) ወደ መጣል ከሚደረገው ጥሪ ጋር እየሆነ ያለው ነገር በትክክል ይህንን ነው። ⚫️ ​ነገሩማ አማኝ ሴትን በመሸፈኗና በጥንቁቅነቷ ወደ ማስወለቅና መውቀስ ደረጃ ይደርሳል፤ ሒጃቧንና ጠንካራ መሸፈኛዋን አጥብቃ ስትይዝ ባዩዋት ጊዜ በኋላቀርነት፣ በመሀይምነት፣ በትዕቢትና በስነ-ልቦና መዛባት ይፈርጇታል። ✴️ እንዲሁም ብልሁ፣ ጥንቁቁና አማኙ ወንድ በጥንቃቄው፣ በብልህነቱ፣ በእምነቱና አላህን በመፍራቱ ይወቀሳል። ​በዚያን ጊዜ “(ዲኑን አጥብቆ የያዘ ሰው ልክ የጋለ ፍም እንደጨበጠ ነው)” የሚለውን ሐዲሥ እውነተኛ ትርጉም ትረዳለህ፤ ✨ ምክንያቱም ከዚህች የስቃይ ምድር በኋላ ስፋቷ እንደ ሰማያትና ምድር የሆነች፣ ለአላህ እሱን ለሚፈሩት የተዘጋጀች ጀነት እንዳለች ያውቃልና። 📝 ​ወንድሞቼ  እና እህቶቼ ሆይ ✴️​ሐራም  የሆነ ነገር ሰዎች ሁሉ ቢፈጽሙትም እንኳ ዘላለም ሐራም ሆኖ ይቀጥላል፤ ✴️​ሒጃብ ሴቶች ሁሉ ቢያወልቁትም እንኳ ግዴታ  ሆኖ ይቀጥላል፤ ✴️​ሞት በሕይወት ያሉ ሁሉ ቢረሱትም እንኳ እውነት ሆኖ ይቀጥላል፤ ✴️ በመጨረሻም የተውበት በር አንድ ባሪያ ወደ ወንጀል ሺህ ጊዜ ቢመለስም እንኳ ክፍት ሆኖ ይቀጥላል። ​✨ አላህ ሆይ! ጥራት ይገባህ፣ ክብርህ ምንኛ ታላቅ ነህ © 📝إبن أبي الدنيا الحبشي : محرم  ١٤٤٨ @fivekjemaa

🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا
🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ ﷺ 🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟 ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት "ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።" ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልባችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው። ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️ اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

ነፍሷን አሸንፋ እርቃኗን ከመሆን: ራሷን አብቅታ ለመትረፍ ለወገን:: መማርን ፈልጋ ልታለማ አገሯን: በእውቀት አለንጋ አባራ ጅህልናን: ለሃገር ግንባታ ለማስቀመጥ ጡቧን:: ተፍ ተፍ ስትል ለመሻት እውቀትን: ከሐገር ለማጥፋት ችግር ድህነትን:: የሰው ቀዬ ሳትደርስ ሳትጋፋ ሌላን: መራቆትን ጠልታ በመያዟ እምነቷን:: የእህቴን ክብር የዛች የጥብቋን: በ'ምባ እየተሞላች ገፈፏት ሑርማዋን::                          ⭐️⭐️⭐️ « አላ ሹለት የዱን » እህቴን የነካች: የንፅህናን ልክ በቅጥ ያልተረዳች: በጥላቻ ሰክራ ድንበር የዘለለች: የእህቴን ካባ ክብሯን የደፈረች:: ያቺ እጅ ትረገም ሐቅን የረገጠች: ኒቃብን አውልቃ እርቃን ያነገሰች:: የእህቴን ካባ ክብሯን የደፈረች: ራቁት አስፈትና ለባሽ ያባረረች: ፍትህን በመጣስ ሚዛን ያጓደለች::         ⭐️⭐️⭐️ ሁሉ ሲሰለጥን ሗላ የዘገዩ : በክፋት ጥላቻ ተነክረው የቆዩ: ቀለም መንካት እንጂ መማርን ያላዩ:: በ'ድሜ ቢሆን እንጂ ከልጅ ያልተለዩ: ከሽበት በስተቀር ክፋ ደግ ያልለዩ:: በየ ሴክተሩ ላይ ተሰግስገው ያሉ: ስንት ሰዎች አሉ አድገው ያልበሰሉ:: የተቀመጡበት ከስር ያለው ወንበር: ከነሱ ይሻላል በግልጋሎት ግብር::            ⭐️⭐️⭐️ ምን ይሆን ክሳችሁ ከቶ ምን አጠፋች?! ራሴን ጠብቄ እማራለሁ ባለች: ለ'ምነቷ ዘብ ሆና ፀንታ ስለቆመች:: ጨርቃቸውን ጥለው ሲቆዝሙ ሌሎች: ክብሯን ችላ ብላ ልብሷን ስላልጣለች:: የቱ ነው ጥፋቷ መብቷን በጠየቀች?: የራሷን ነው እንጂ የሰው መብት አልነካች:: ከጥላቻ በቀር ምክንያት ካላችሁ: አይዟችሁ ንገሩኝ በሉ እስኪ ልስማችሁ: ንገሩን ሰበቡን ድምፅ ከፍ አርጋችሁ:: የክልከላው ምክንያት ከተዋጠላችሁ: ኑ እስኪ ተናገሩት ካላሳፈራችሁ::            ⭐️⭐️⭐️ የኔው ነው ጥፋቱ የኔው ነው ስህተቱ: ይሰማኝ ይመስል ሙታን መጣራቱ:: መንቃት ያልፈለገን አውቆ የተኛን ሰው: እሳት ቢሆን እንጂ ውሃ ላያነቃው:: ያፄዎቹን ትርክት ጠጥቶ የሰከረን: ወደ ፊቱን ትቶ ሗላ ላይ የቀረን:: እውነታውን ገፍቶ መረዳት ዘመኑን: በጨለማው ዘመን ሰምጦ የቀረውን:: ቅን መሆንን ትቶ ጥላቻን ያዘለን: ጭቆናን እንደ ድል ስኬት የቆጠረን:: ምን ብዬ ልንገረው እንዴትስ ላስረዳው?! የጥላቻ ቆፈን ሐቅን ከጋረደው:: የሰው ልጅ ወቃሹ የገዛ ህሊናው: እሱ የሌለውን ሰው ብለህ አትጥራው::              ይህን ለመረዳት ካልሆነህ ትምርትህ: ጥላቻን ካስቀደምክ አመክንዮን ትተህ: ጥቅሙ ምኑ ላይ ነው ቀለም የመንካትህ:: ፕሮፌሰር : ዶክተር : ምሁራን መባልህ: Master , phD , degree መሸከምህ:: @aaumsu

"መጅሊስ በሂጃብ ጉዳይ ከ Retroactive( እሳት አጥፊነት) ነፃ የሚሆነው መች ነው?" - (ጠበቃ ሙስጠፋ ሺፋ እንደፃፈው) የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሸሪዓ ፍርድ ቤትን አ
"መጅሊስ በሂጃብ ጉዳይ ከ Retroactive( እሳት አጥፊነት) ነፃ የሚሆነው መች ነው?" - (ጠበቃ ሙስጠፋ ሺፋ እንደፃፈው) የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሸሪዓ ፍርድ ቤትን አዋጅ ለማሻሻል ከመንግሰት ጋር በመቀናጀት አንድ እምርታ እንዳስመዘገበው ሁላ ስለ ሂጃብ ኢ ህገ መንግስታዊ ብሎም የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሲፈፀም በተለይ የፈተና ወቅትን እየጠበቁ ባልተፃፈ ህግ የሙስሊም ተማሪዎችን ስነ ልቦና ለመጉዳት ሆን ተብሎ በጥቂት የመንግስት ተሿሚዎች ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም በአንደኛ ደረጃ፣ በሁለተኛ ደረጃና በከፍተኛ የትምህርት ተቋም እየተፈፀመ ያለውን በደል መጅሊስ ልክ ድርጊቱ ሲፈፀም መግለጫ ከማውጣትና ድርጊቱ ወደ ተፈፀመበት ስፍራ አቅንቶ ለዛሬ ይሁን ዓይነት ሽንገላ ተነጋግረናል ተወያይተናል ይባልና ጉዳዩ ችላ እንደተባለ ከሆነ ጊዜ ቆይታ በኋላ አሁንም ሲያገረሽ መጅሊስ retroactive ( እሳት ማጥፋቱ) ይቀጥላል። ግን እስከ መቼ? ሒጃብ ሃይማኖታዊ ነው። ይህን ሃይማኖታዊ መብት ከኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 27(1) አኳያ እንዲከበርና እንዲጠበቅ ዘንድ በደንብና በመመሪያ ጥሰት ፈፃሚዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ ሃይማኖታዊ መብትን ብሎም ህገ መንግስታዊ ጥበቃ የተሰጠውን መብት በዘለቄታነት ተከብሮ እንዲዘልቅ መጅሊስ ስር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ዘንድ ጥሰት ሲፈፀም ለጊዜያዊነት ማስታገሻ እየወሰዱ ከመዝለቅ ይልቅ ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት ህግ እንዲከበር አበክሮ ካልሰራ ትላንትም፣ዛሬም ነገም ስለ ሂጃብ ክብር እየተደፋፈነ እንግልቱ ወደ ትውልድ መቀባበሉ ይቀጥላል። መጅሊስ በአዋጅም ሆነ በህገ መጅሊሱ የህዝበ ሙስሊሙን ሃይማኖታዊ መብት ማስከበርና ማስጠበቅ አበይት ተግባሩ ነው። @aaumsu

"እምነቴን ልተው? ወይስ ትምህርቴን?" - አቡ አብደላህ እንደፃፈው ይህ ዛሬ ብዙ የሙስሊም ሴት ተማሪዎች የሚጠየቁት ከባድ ጥያቄ ሆኗል። ኒቃብ ለብሳ መማር የፈለገች ተማሪ ከትምህርት ክፍል ውጭ ስት
"እምነቴን ልተው? ወይስ ትምህርቴን?" - አቡ አብደላህ እንደፃፈው ይህ ዛሬ ብዙ የሙስሊም ሴት ተማሪዎች የሚጠየቁት ከባድ ጥያቄ ሆኗል። ኒቃብ ለብሳ መማር የፈለገች ተማሪ ከትምህርት ክፍል ውጭ ስትቀር፣ ፈተና እንዳትፈተን ስትከለከል፣ የሚጎዳው አንድ ግለሰብ ብቻ አይደለም፤ የሀገራችን ፍትሕ፣ እኩልነት እና የሕግ የበላይነትም ጭምር ነው። እኛ የምንጠይቀው ልዩ መብት አይደለም። ሕገ መንግሥቱ የሚያረጋግጠው የእምነት ነፃነት እና የትምህርት መብት በአንድነት እንዲከበሩ ብቻ ነው። የደኅንነት ወይም የማንነት ማረጋገጫ ካስፈለገ፣ ያንን የሴት ሠራተኛ በሚያረጋግጥበት ሥርዓት መፈጸም ይቻላል። ነገር ግን በኒቃብ ምክንያት ትምህርትን መከልከል ተገቢ መፍትሔ አይሆንም። ለመንግሥት ያለን ጥሪ፦ የሁሉንም ዜጎች መብት በእኩልነት የሚያስከብር፣ የእምነት ነፃነትንና የትምህርት መብትን የሚያጣጥም ግልጽ መመሪያ እንዲወጣ እንጠይቃለን። ለመጅሊስ ያለን ጥሪ፦ ይህ የብዙ ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን የሚመለከት ጉዳይ ነው። ከመንግሥት፣ ከትምህርት ተቋማት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት ሕጋዊ፣ ሰላማዊ እና ዘላቂ መፍትሔ እንዲገኝ የሚጠበቅበትን ሚና እንዲወጣ እንጠይቃለን። የሙስሊም ሴት ተማሪ ኒቃብ የትምህርቷ ጠላት አይደለም። እምነትም ሆነ ትምህርት ሁለቱም መብቶች ናቸው፤ አንዱ ሌላውን ሊያስቀር አይገባም። #ኒቃብ_ወንጀል_አይደለም #የትምህርት_መብት #የእምነት_ነፃነት #ፍትሕ_ለሁሉም @aaumsu

"ክብሯን አስወለቋት!" የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ኒቃቡን ካላወለቃችሁ ተብለው ማውለቅ ጀመሩ። በአደባባይ ክብራቸውን እንዲያወልቁ ተደረጉ። እስካሁን ባለው መፍትሔ ተብሎ የተሰጠው ማስክ ለብሰው መግባትን ነው። ኒቃብም ማስክም ፊትን ይሸፍናሉ። ኒቃቡን አስወልቀው ማስክ ማስለበስን ለምን ፈለጉ? ማስክ አስለብሰው ኒቃቡን ማስወለቅ ለምን ፈለጉ?! ጥላቻ! ለኢስላማዊ እሴት ያለ ጥላቻ!! ሌላ ምንም ምክንያት የለም። አሁንም ቢሆን ተማሪዎች ክብራቸውን በአደባባይ ሳይጥሉ፤ ከእነ ኒቃባቸው እንዲፈተኑ መጅሊስ እና የሚመለከተው የመንግስት አካል ይስራ። አሁንም ቢሆን ይህንን ውንብድና የፈፀሙ አካላት ተጠያቂ እንዲደረጉ መንግስት እና መጅሊስ ይስሩ። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

ዛሬም ኒቃባቸውን በአደባባይ አውልቀው እንዲገቡ ተገደዋል! በትላንትናው እለት የ12ተኛ ክፍል ኢንትራንስ ተፈታኝ ተማሪዎች በአብርሆት ቤተመፅሐፍት እየተፈተኑ ባለበት ከ20 በላይ ሙስሊም ተማሪዎችን "ኒቃባችሁን ካላወለቃችሁ አትገቡም!" - ተብለው ጓደኞቻቸው ውስጥ እየተፈተኑ እና በትምህርት ሚኒስቴሩ ሚንስትር ብርሃኑ ነጋ እየተጎበኙ ለ3 ሰዓታት ያክል ከውጪ እንዲሆኑ ተደርጎ ነበር። የሗላ ሗላ እንዲገቡ ቢደረግም ኒቃባቸውን አውልቀው እና ጥለው በማስክ ነበር። መፍትሔ እንደሚመጣ የተገለፀ ቢሆንም በዛሬው እለትም በተመሳሳይ ኒቃባቸውን በአደባባይ እያወለቁ እንዲገቡ ነው የተደረጉት። ይህ ግልፅ የሆነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው። ይህ ግልፅ የሆነ የሀይማኖት መብት ጥሰት ነው። ይህ ግልፅ የሆነ የነፃነት መብት ጥሰት ነው። ኒቃብን መልበስ መብት ነው። መብት ስለሆነም ለብሳው ስትማር ነበር። አሁን ላይ እየተፈፀመ ያለው ውንብድና ተማሪዎችን የስነ-ልቦና መቃወስ ውስጥ እየከተታቸው ነው። ተማሪዎችም አስቸኳይ መፍትሔ እንዲመጣላቸው እየጠየቁ ነው። መጅሊስ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ይስራ። መንግስት ተጠያቂ መደረግ ያለባቸውን አካላት ተጠያቂ ያድርግ። ዘላቂ መፍትሔም ይምጣ!!! @aaumsu

ይህ ምስል፣ ልብን በሀዘንና በቁጭት የሚሰብር የታሪክ ጠባሳ ነው! (በኡስታዝ ነስሩ ኸዲር) መሬት ላይ ተጥሎ የሚታየው ተራ ጨርቅ አይደለም፤ የአንዲት እህታችን ክብር፣ ማንነት እና የእምነት መብት እ
ይህ ምስል፣ ልብን በሀዘንና በቁጭት የሚሰብር የታሪክ ጠባሳ ነው! (በኡስታዝ ነስሩ ኸዲር) መሬት ላይ ተጥሎ የሚታየው ተራ ጨርቅ አይደለም፤ የአንዲት እህታችን ክብር፣ ማንነት እና የእምነት መብት እንጂ! ተማሪዎች ነገ ሀገር ለመረከብ በሚፈተኑበት አዳራሽ ደጃፍ ላይ እምነታቸውን በግድ እንዲያወልቁ መገደዳቸው እጅግ አሳዛኝ ሥርዓት አልበኝነት ነው። ሂጃብ ለሙስሊም ሴት ልጅ ውጫዊ ጌጥ ሳይሆን፣ የማንነቷ አካልና የእሴታችን መገለጫ ነው። ​ይህ ድርጊት በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት ላይ ሲፈጸም፣ የሚመለከታቸው የመፍትሄ አካላት እስካሁን ድረስ ግልጽና የማያሻማ እርምጃ አለመውሰዳቸውና በዝምታ ማለፋቸው ተጠያቂነትን ያጠፋ የተቋማት ዳተኝነት ነው። ትምህርት ቤት የነፃነትና የእኩልነት ማዕከል መሆን ሲገባው፣ የተማሪዎችን ስነ-ልቦና የሚሰብር አግላይ መድረክ ሊሆን አይገባም። ይህንን በደል ዝም ብሎ ማየት አብሮነትን ማፍረስ በመሆኑ፣ የሚመለከተው አካል አስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግና ጥፋተኞችን ተጠያቂ እንዲያደርግ በጽኑ እንጠይቃለን። @aaumsu