1 146
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1830 день
Архів дописів
1 146
ዕለተ ዓርብ ህዳር 13/2017ዓ.ም
"በ ISO 21001:2018 EOMS " ዕውቅና ለማግኘት የግንዛቤ መፍጠሪያ ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ "በISO 21001:2018 EOMS " እውቅና ለማግኘት የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸው ይታወቃል። ከዚህ ጋር ተያያዥነት ያለው እና እስከ አሁን ሲሰጡ ከነበሩት ስልጠናዎች በአቀራረቡ የተለየውና ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው ግምገማዊ ስልጠና የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች ፣ ዳይሬክቶሬት ተጠሪዎች፣ አካዳሚክ ኮሚሽን በአጠቃላይ በኦዲት ስራው ተደራሸ የሆኑ ክፍሎችን አሳትፏል።
ስልጠናው ለ ISO 21001 ትግበራ የተዘጋጁ ሰነዶች ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን ገለጻው በአስተባባሪው በአቶ ሚካኤል ጎኣ ቀርቦ በቡድን ውይይትና አስተያየት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሀገርህን እወቅ ክበብ ዓባል ለመሆን የምትፈልጉ የኮሌጀ ሰራተኞች በሙሉ የምዝገባ ቀን የፊታችን ሰኞ ከ4:00_6:00 እና ማክሰኞ ከ4:00_ 6:00 ማለትም (በ 16/2017 & 17/2017) በቻ ማነኛዉም ተመዝጋቢ በአካል በመገኘት መመዝገብ ይችላል።
መሳሰቢያ:- 1, ማነኛዉም ተመዝጋቢ በመመሪያዉ መሠረት በየወሩ መዋጮ ለመክፈል ፈቃደኛ የሆ ።
2, ሌላ ሰዉ ማስመዝገብ አይችልም በስልክም ቢሆን መመዝገብ አይቻልም
3, የምዝገባ ቦታ የተማሪ መማክርት ቢሮ ከክሊኒኩ ጎን በሚገኘዉ ቢሮ ብቻ ይሆናል።
1 146
+7
ህዳር 11/2017ዓ.ም
በረከት ለመቶኛ ዓመት በዓል አከባበር ።
የቀድሞ የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ማህበር የቦርድ አባላት ለመቶኛ ዓመት በዓል አከባበር ከተያዘው ዕቅድ አንዱ የህንጻ ግንባታ ሲሆን በዛሬው ዕለት ከኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ጋር የዲዛይን ግምገማ አደረጉ ።
ማህበሩ በስጦታ መልክ ለሚያበረክተው ባለ 4 ወለል ለመማሪያ ፣ለመሰብሰቢያ አዳራሽ በአጠቃላይ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውል መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል። በውይይቱ ጠቃሚና ለዲዛይኑ ግብአት የሚሆኑ ሃሳቦች ከሁለቱም ወገን መነሳቱና በቀጣይ በማህበሩ አባላት ባለሙያዎች እንደሚዳብር የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ይህ የፕሮጀክት ስራ ማህበሩ ሲያበረክታቸው ከቆዩት በጎ ተግባራት የቀጠለ መሆኑን ከማመላከቱም በላይ ድጋፉ ከግዜ ወደ ግዜ እያደገ መሄዱን የሚያሳይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ህዳር 11/2017ዓ.ም
21ኛው የፀረ-ሙስና ቀን "የወጣቶች ህብረት ሙስናን ለመግታት "በሚል መሪ ቃል ተከበረ ።
በፕሮግራሙ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በዛሬው ዕለት እዚህ የተሰባሰብንበት ፕሮግራ በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበር የቆየውን የስነምግባርና የፀረ-የሙስና ቀን የማጠቃለያ ፕሮግራም ሲሆን ሙስናን የሚጠየፍና በስነ-ምግባ የታነጸ ትውልድ በማፍራት ሂደት ከቤተሰብ እና ከማህበረሰብ ቀጥሎ ትምህርት ቤቶች ድርሻ ከፍተኛ ሲሆን እኛም ሠልጣኞቻችን በስነ-ምግባራቸው የታነጹ፣ ሙስናና ብልሹ አሰራርን የሚጠየፉ ሆነው እንዲወጡ የበኩላችንን እንድንወጣ ለማስቻል እና ወጣቶች በዚህ ረገድ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
በመቀጠልም የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ወ/ሮ ዝግጁ ግዛቸው በዓሉን አስመልክተው የተዘጋጀ ሰነድ አቅርበዋል። በሰነዱ መነሻነት የመወያያ ርእስ ቀርቦ ከቤቱ ሃሳብና አስተያየት ቀርቧል።
ዘወትር በኮሌጃችንም ሆነ ከኮሌጁ በተጠየቁበት ቦታ እንደየ ዝግጅቱ ይዘት ተዘጋጅተው የኮሌጁ ስም ከፍ እንዲል የሚያደርገው የኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ የሙዚቃና የቲያትር ጥበባት ሠልጣኞች እንደተለመደው የሙዚቃና የቲያትር ስራዎቻቸውን በማቅረብ የዕለቱን መልእክትና ሃገራዊ ስሜትን የሚገነቡ የሚዚቃ ስራዎችን በማቅረብ ታዳሚውን እያዝናኑ የዕለቱን መልዕክትም አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም ህዳር 5/2017ዓ.ም በነበረው የጥያቄና መልስ ውድድር ከ1ኛ -3ኛ ለወጡ ሠልጣኞች የምስክር ወረቀትና የሞባይል ካርድ ባለ200 ፣100፣50ብር በቅደም ተከተላቸው ተበርክቶላቸዋል ። በተመሳሳይ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከኮሌጁ ጋር በተባባሪነት የሚሰራው የመነነ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያና በኮሌጁ የተለያዩ ዳይሬክቶሬቶች ሃብት በማስመዝገብ ሂደቱ ለነበራቸው አስተዋጽኦ የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል ። የምስክር ወረቀቱን የሰጡት የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በአሉን ስናከብር ሙስናን ለመዋጋት በጋራ እንስራ ፣ሙስናን የሚጠየፍ ትውልድ እናፍራ በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈው ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+2
በኮሌጁ የሃገርህን ዕወቅ ክበብ ተመሠረተ።
ህዳር 10/2017ዓ.ም
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከረጅም ዓመታት በፊት የሃገርህን ዕወቅ ክበብ የነበረና የተጠናከረ ስራ በመስራት የሚታወቅ ክበብ እንደነበር ከተለያዩ ምንጮች ለማወቅ ተችሏል። ሆኖም ግን የነበረው ክበብ በህግና ደንብ ላይ ተመስርቶ ባለመቋቋሙና ክበቡን ይመሩት የነበሩ ጠንካራ አባላት በተለያዩ ምክንያቶች በመልቀቅ እና በህይወት ህልፈት ሲለዩ እየተዳከመ ሄዶ እስከ መክሰም መድረሱን ለማቅ ተችሏል ።
አሁን ላይ በከተማ አስተዳደሩ በምክር ቤት ደረጃ እስከ ክፍለ ከተማና ወረዳ ድረስ እንዲሁም በትምህርት ተቋማት በተመሳሳይ ተዋቅሯል ፤ ክበቡ በደንብ ቁጥር 32/1959 በ2010ዓ.ም የተቋቋመ መሆኑን ከቀረበው ሰነድ ለማወቅ ተችሏል። በዚህ መነሻነት የኮሌጁ የሃገርህን ዕወቅ ክበብ "ጥቂት ይቆጥቡ ብዙ ይጓዙ" በሚል መርህ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመስርቷል።
የክበቡ መመስረት በመደጋገፍ ወጪዎችን ለመሸፈን በጉዞ ሃገርን ለማወቅ ፣ እራስን ለማዝናናት፣ እርስ በርስ ለመግባባትና ለመከባበር ፣ ጥሩ ግንኙነትን ለማጠናከር የሚያግዝ/የሚያበረታታ ነው።
በመሆኑም የኮሌጁ ማህበረሰብ የዚህ ክበብ አባል እንድትሆኑ ጥሪያችንን እያስተላለፍን ።
" ኑ አብረን ጥቂት እንቆጥብ ብዙ እንጓዝ" ሃገራችንን እንወቅ !!!
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+4
ዕለተ ዓርብ ህዳር 6/2016ዓ.ም
Mohas Trading PLC ድርጅት ከኮሌጁ ጋር በጋራ
ለመስራት የመጣ መሆኑ ገለፀ።
Mohas Trading PLC ድርጅት ከኮሌጃችን ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችሉ ሃሳቦችን ይዞ የመጣ ሲሆን ለኮሌጁ የበላይ አመራሮች ፣ ለማኔጅመንቱ እና ለአካዳሚክ ጉዳዮች አባላት ስለ ድርጅቱ አመሠራረት፣ ዓላማ ፣ የሚያከናውናቸው ተግባራት ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል ፤ ማብራሪያውን የሰጡት የድርጅቱ ፕሮጀክት ማኔጀር አቶ አሸናፊ ሲሆኑ ድርጅታቸው በማማከር፣ በስራ ፈጣሪነት፣ በቴክኖሎጂ ልማት ፣ በGreen TVET ላይ የመስራት ልምዱም አቅሙም እንዳላቸው ገልጸው በቀጣይ ኮሌጁ የሚያከብረውን የ100ኛ ዓመት ክብረበዓል እና የኮሪደር ልማቱን ትሩፋት እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ከኮሌጁ ጋር በጋራ ስምምነት እና በጋራ ራዕይ ላይ የተመሠረተ ስራ እንደሚሰሩ አብራርተዋል ።
ኮሌጁና ድርጅቱ የጋራ አጋርነት/ህብረት በመፍጠር መስራት የሚችሉበትን አቅጣጫዎች በማማከር ፣ በስራ ፈጣሪነት ፣ በዲጂታል ቴክኖሎጁ ፣ የአቅም ግንባታ ስራዎች እና Green TVET ላይ እንደሚሰሩ ተጠቁሟል። እንደ ማኔጀሩ ገለጻ አብሮነታቸው
- ዓላማ መር
- በመተማመን ላይ የተመሠረተ
- በጋራ ዕቅድ የሚመራ
- በመደጋገፍ ላይ የተመሠረተ መርህን ያነገበ መሆኑም በማብራሪያው ተጠቅሷል።
በአጠቃላይ ድርጅቱ ወደ ስራ ሲገባ የኮሌጁን ተፈላጊነትና አቅም በማሳደግ የልህቀት ማእከል እንዲሆን ለማስቻል በጋራ መስራት የሚቻልባቸውን ሃሳቦች ይዞ የመጣ መሆኑ ተገልጿል።
በመጨረሻም ከቤቱ የተለያዩ ገንቢ ሃሳብ ፣ አስተያየትና ጥያቄዎች ቀርበው በድርጅቱ ባለሙያዎች እና በኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ተጨማሪ ማብራሪያ ተሰጥቶቷል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+2
ዕለተ ዓርብ ህዳር 6/2017ዓ.ም
ISo 21001:2018 EOMS " በአፈጻጸም ግምገማ ግብረመልስ ላይ ውይይት ተካሄደ።
ኮሌጁ ወጥ የሆነ የአሰራር ስርአትን በመዘርጋት ዓለማቀፍ እውቅና የሚያገኝበትን አሰራር ከጀመረ መሰነባበቱን ተከትሎ ስራዎች ከሚጠበቀው አንጻር ምን ያህል ተግባራዊ ሆነ ? ምንስ ቀረ ? የሚለው የተፈተሸ መሆኑ ይታወቃል። በአጠቃላይ የነበረው አፈጻጸም በባለሙያዎች እይታና ከስታንዳርድ አንጻር ተፈትሾ በቀረበው ግብረመልስ የኮሌጁ ማኔጅመንት እና አካዳሚክ ኮሚሽን በጋራ በተሰጡ አስተያየቶች ላይ በየደረጃውና በሚመለከተው አካል መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች በጥልቀት ተዳሰው በተቀመጠው የ15ቀን ገደብ የተሰጡ አስተያየቶችን ለማስተካከል ከጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
በመቀጠልም ኮሌጁ ያለውን የሰው ሃይልና ማቴሪያል በማቀናጀት እንደየ ዘርፉ ስራዎችን በማቀድ እና በመተግበር ተጨማሪ ገቢ ማስገኛ ስራዎችን በመስራት ኮሌጁንም ሆነ ሰራተኞችን ተጠቃሚ ሊያደርጉ የሚችሉ ተግባራትን ማከናወን ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ መሆኑ ተጠቆመ ። ከዚህም አንጻር በኮሌጁ የሚገኙ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በሚፈለገው ልክ በማስተካከልና ስርአት በማበጀት የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ይገባል። ይህን በውል ተግባራዊ ማድረግ ሲቻል ለኮሌጁ ተጨማሪ የገቢ ማስገኛ መሆኑም ይታመናል። ሆኖም ግን ይህን እውን ለማድረግ በተዘረጋው የአሰራር ስርአዓት ሊመሩና ሊተዳደሩ እንደሚገባ ከመግባባት ላይ ተደርሷል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የኮሌጁ የሥነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር አካሄደ
***
ህዳር 5/2017 ዓ.ም የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሥነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ በሀገራችን ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደ ።
በፕሮግራሙ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የስነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ዝግጁ ግዛቸው በስነ-ምግባር የታነፀ ዜጋ ማፍራት አሌ የማይባል ተግባራችን መሆኑን ጠቁመው ሙስናና ብልሹ አሰራርን በመታገል ከሙስና የፀዳ ዜጋ ለመፍጠር በስነ-ምግባር የታነፀ ፣ ሙስናን የሚፀየፍ ተተኪ ትውልድ ማፍራት የግድ ይላልም ብለዋል።
ዳይሬክቶሬቱ በተለያዩ ግዚያት በየደረጃው ለኮሌጁ ሰራተኞችም ሆነ ለሠልጣኞች የግንዛቤ መፍጠሪያ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይታወቃል ። በመሆኑም
በዛሬው ዕለትም በዓለማቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ግዜ በሃገራችንም ለ 20ኛ ግዜ የሚከበረው የፀረ-ሙስና ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበር ሲሆን የዚህ አካል የሆነው የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሂዷል። በውድድር መድረኩ የኮሌጁ ሠራተኞችና ሠልጣኞች ተሳታፊ ሆነዋል።
በፕሮግራሙ መዝጊያ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ሙስናን የሚጠየፍና በስነ-ምግባ የታነጸ ትውልድ ስናፈራ ሠልጣኞቻችን በኮሌጅ ስልጠና ቆይታቸውም ሆነ በትብብር ስልጠና ቦታዎች በስነ-ምግባራቸው መልካም የሆኑ፣ የተመሠከረላቸው ታማኝ በመሆን ስልጠናቸውን እንዲያጠናቅቁ በተለያየ ደረጃ የሚገለጽ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኮች ሊፈጠርላቸው ይገባልም ብለዋል ። በዛሬው ዕለት የተከናወነው ይህ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክም አንዱ በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መልእክታቸውን አስተላልፈው በውድድሩ ላሸነፉ በቀጣይ በሚኖረው የማጠቃለያ ፕሮግራም እውቅና የሚሰጥ መሆኑን የገለፁ ሲሆን በውድድሩ አንደኛ ለወጣችው ሠልጣኝ ርብቃ ሽፈራው የ200ብር የሞባይል ካርድ የማረታቻ ሽልማት አበርክተዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የኮሌጁ የሥነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር አካሄደ
** *********
ህዳር 5/2017 ዓ.ም የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሥነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ በሀገራችን ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሄደ ።
በፕሮግራሙ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የስነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ዝግጁ ግዛቸው በስነ-ምግባር የታነፀ ዜጋ ማፍራት አሌ የማይባል ተግባራችን መሆኑን ጠቁመው ሙስናና ብልሹ አሰራርን በመታገል ከሙስና የፀዳ ዜጋ ለመፍጠር በስነ-ምግባር የታነፀ ፣ ሙስናን የሚፀየፍ ተተኪ ትውልድ ማፍራት የግድ ይላልም ብለዋል።
ዳይሬክቶሬቱ በተለያዩ ግዚያት በየደረጃው ለኮሌጁ ሰራተኞችም ሆነ ለሠልጣኞች የግንዛቤ መፍጠሪያ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይታወቃል ። በመሆኑም
በዛሬው ዕለትም በዓለማቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ግዜ በሃገራችንም ለ 20ኛ ግዜ የሚከበረው የፀረ-ሙስና ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበር ሲሆን የዚህ አካል የሆነው የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሂዷል። በውድድር መድረኩ የኮሌጁ ሠራተኞችና ሠልጣኞች ተሳታፊ ሆነዋል።
በፕሮግራሙ መዝጊያ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ሙስናን የሚጠየፍና በስነ-ምግባ የታነጸ ትውልድ ስናፈራ ሠልጣኞቻችን በኮሌጅ ስልጠና ቆይታቸውም ሆነ በትብብር ስልጠና ቦታዎች በስነ-ምግባራቸው መልካም የሆኑ፣ የተመሠከረላቸው ታማኝ በመሆን ስልጠናቸውን እንዲያጠናቅቁ በተለያየ ደረጃ የሚገለጽ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኮች ሊፈጠርላቸው ይገባልም ብለዋል ። በዛሬው ዕለት የተከናወነው ይህ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክም አንዱ በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መልእክታቸውን አስተላልፈው በውድድሩ ላሸነፉ በቀጣይ በሚኖረው የማጠቃለያ ፕሮግራም እውቅና የሚሰጥ መሆኑን የገለፁ ሲሆን በውድድሩ አንደኛ ለወጣችው ሠልጣኝ ርብቃ ሽፈራው የ200ብር የሞባይል ካርድ የማረታቻ ሽልማት አበርክተዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
