1 146
Підписники
Немає даних24 години
-37 днів
-1830 день
Архів дописів
1 146
ህዳር 02 ቀን 2017 ዓ.ም
ለአዲስ ገቢ ሰልጣኞች የአቀባበል መርሃግብር
ተከናወነ።
በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ስልጠናቸውን በተለያዪ የሙያ መስኮች ለመከታተል ለተመዘገቡ አዳዲስ ሰልጣኞች 'የእንኳን ደህና መጣችሁ' መርሃ-ግብር ተዘጋጅቶላቸዋል ።
መርሃ ግብሩ በስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች፣ የስነ - ምግባርና ጸረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ፣ የኮሌጁ ህንጻ አስተዳደር ጽ/ቤት እና የኮሌጁ የሰልጣኝ ካውንስል በጋራ ያዘጋጁት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
መርሃግብሩ በኢትዮጵያ ብሄራዊ መዝሙር የተጀመረ ሲሆን በዕለቱም የሬጅስትራር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ስመኝ ሜደቅሳ ሰልጣኞችን እንኳን ደህና መጣችሁ ካሉ በኋላ ስለምዝገባው ሂደት እና የሬጅስትራር አሰራሮች ለሰልጣኞች አብራርተዋል። በንግግራቸውም ሰልጣኞች አሳማኝ ምክንያት ካቀረቡ ዲፓርትመንት ለመቀየር የሚያስችል ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል ጠቁመዋል።
በዕለቱ የተገኙት የኮሌጁ የሥነ ምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ዝግጁ ግዛቸው ደግሞ አዲስ ሰልጣኞች ሊኖራቸዉ ስለሚገባው የሥነ -ምግባር ደንብ እንዲሁም በቆይታቸዉ ሰልጣኞች ስለሚኖራቸው መብት እና ግዴታ ገለጻ አድርገዋል። ዳይሬክተሯ አያይዘዉም ሰልጣኞች በኮሌጁ ዉስጥ ባሉ ክበባት እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል ።
በተመሳሳይ የስልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ለሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸዉን ካስተላለፉ በኋላ ስለ አዲሱ የቴ/ሙ የስልጠና ካሪኩለም ረዘም ያለ ገለጻ አድርገዋል።ከተናገሯቸዉ መካከልም በየደረጃዉ የነበረዉ ምዘና ቀርቶ አጠቃላይ ምዘና (Holistic Asssessment) እንደሚሰጥ ፣ የትብብር ስልጠናን በተመለከተ እንደ እስከ ዛሬው ሰልጣኞች በራሳቸዉ ፈልገው የሚሰሩት ሳይሆን ከኮሌጁ ጋር የትብብር ስምምነት (memorandum of agreement ) ከፈረሙ ኢንዱስትሪዎች ጋር ከስልጠና ባለፈ ሰልጣኞች በኢንዱስትሪው እንዲቀጠሩ ወይም በመደራጀት የራሳቸውን ስራ እንዲፈጥሩ የማስቻል ስራን ኮሌጁ እንደሚሰራ አመልክተዋል።
የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በከተማም ሆነ በሃገር አቀፍ ደረጃ ከከሌሎች የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ለየት የሚያደርገው እና የኮሌጁ ፈርጥ በሆነው በኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ የሙዚቃ ት/ክፍል ሰልጣኞች እንኳን ደህና መጣችሁ መርሃግብሩ ላይ ለታዳሚዎች 'የሙዚቃ ድግስ' አቅርበዋል።
በመጨረሻም ሰልጣኞች በየተመዘገቡበት ዘርፍ ከስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎቻቸው እና ከአሰልጣኞቻቸው ጋር የስልጠና ወርክ ሾፖችን ጉብኝት አካሂደዋል ፡፡
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+9
ዕለተ ሐሙስ ጥቅምት 28/2017ዓ.ም
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንቦት 29/2016ዓ.ም የተጀመረው ISO 21001:2018 Educational quality management system" እውቅና የማግኘት እንቅስቃሴን ተከትሎ የትግበራ ሂደቱ ያለበትን ደረጃ ለማወቅ የሚረዳ የውስጥ ኦዲት ስራ በዛሬው ዕለት ጥቅምት 28/2017ዓ.ም በይፋ ተጀምሯል።
በኦዲት ስራ ማስጀመሪያ ስነ-ስርአት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ እና ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢኒስቲትውት የመጡ ከፋተኛ ባለሙያ አቶ አሸናፊ በቀለ የውስጥ ኦዲት ዓላማውን ሲገልጹ በኮሌጁ የISO ትግበራ አፈጻጸሙን በመፈተሽ ለ3ኛ ወገን ኦዲት ቅድመ ሁኔታ ማመቻቸት ነው ብለውታል።
በዛሬው ዕለት የተጀመረው የውስጥ ኦዲት እስከ ህዳር 2/2017ዓ.ም የሚቀጥል መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። በመጨረሻም የመረጃ ትንተናና ትርጉም ተሰርቶ ለተመረመሩት የስራ ክፍሎች ግብረ መልስ እንደሚሰጥ ከስራ ሃላፊዎቹ ማብራሪያ ለማወቅ ተችሏል።
በውስጥ ኦዲት ክንውኑ በኮሌጁም ሆነ ሌሎች የበላይ አካላት የተዘጋጀ የፖሊሲ ሰነዶች ትግበራ፣ የማስፈጸሚያ ሰትራቴጂዎች አጠቃቀም፣ አደረጃጀት እና የአሰራር ሂደት እንደዚሁም የዕቅድ ክንውን ሪፖርቶች ከISO አፈጻጸም መመዘኛ አንጻር እንደሚፈተሹ ከሱፐርቫይዘሮቹ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።
በዚህ የውስጥ ኦዲት ክንውን ስራ ላይ የኮሌጁ ISO ቡድን፣ የየስልጠና ዘርፉ እና የስራ ክፍል ፎካሎች
ከኢትዩጵያ ደረጃዎች ኢኒስቲትዩት ከመጣው የሱፐር ቫይዘር ቡድን ጋር በመቀናጀት እየተሰራ ነው።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+2
ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም
ኮሌጁ የህንጻ እድሳት ስራዎችን አስጀምሯል።
በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ ለረጅም ጊዜ ያለ እድሳት የቆዩ ሕንጻዎች ዉብና ማራኪ እንዲሁም ለስራ አመቺ እንዲሆኑ ለማድረግ በሕንጻ አስተዳደር ጽ/ቤት አማካኝነት የእድሳት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ የጽ/ቤቱ ሃላፊ አቶ አላዬ ጉችዬ ለክፍላችን ተናገረዋል ።
ሃላፊዉ እንደገለጹት በአሁኑ ሰአት በግቢዉ ዉስጥ የሚገኙ ሁለት ሕንጻዎች ማለትም የፋይናንስ ፣ሬጂስትራር እና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ ት/ክፍል ያለበት ሕንጻ (ቢጫ ሕንፃ በመባል ይታወቅ የነበረዉ ) እንዲሁም የሌክቸር መስጫ ሕንጻ (NCR) በኮሌጁ የራስ አቅም ደረጃዉን በጠበቀ መልኩ የቀለም ቅብ እና የፍሳሽ ጥገና እና እድሳት እየተደረገለት ይገኛል ብለዋል።
የኮሌጁ ሕንጻ አስተዳደር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አላዬ ጉችዬ የኮሌጆችን 100ኛ አመት ምክንያት በማድረግ በኮሌጁ ዉስጥ የሚገኙ 27 ህንጻዎችን ለማደስ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸዉ ከጉለሌ ክ/ከተማ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ክፍል ጋር እየሰሩ እንደሚገኙም አስታዉቀዋል። አያይዘውም በዚሁ የእድሳት ስራ ላይ ሁሉም የኮሌጁ አሰልጣኞች እና ሰራተኞች በሙያቸዉ እንዲያግዙ ጥሪ አስተላልፈዋል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ዓርብ ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም
በእንጦጦ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሙያ ስነ-ምግባር እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ዙሪያ የስልጠና መድረክ ተካሄደ።
ስልጠናውን የሰጡት የስነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ወ/ሮ ዝግጁ ግዛቸው እና የመነን ፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ ባለሙያዎች ሲሆኑ የጥበቃ ፣ የጽዳቱ ስራም ሆነ ሌሎች ስራዎች የኮሌጁን ዓላማና ራዕይ እውን ለማድረግ በመሆኑ ባለሙያዎቹ ራዕዩን እና ተልእኮውን በውል በመረዳት ተግባራዊ ለማድረግ ግንባር ቀደሙ የኮሌጁን ደህንነት፣ ንጹህና ምቹ የስራ አካባቢ መፍጠር እንዲሁም ፈጣን አገልግሎት መስጠት ቀዳሚው ሲሆን ይህን ሃላፊነት ለመወጣት ሙያዊ ስነምግባር የተላበሰ ባለሙያ ማብቃት አሌ የማይባል ተግባር ነው ።
በመሆኑም ባለሙያው በየግዜው ወቅቱ የሚፈልገውን ዝግጁነት ተላብሶ ቁመናው የተስተካከለ ሙያዊ ስነምግባር የተላበሰ እና በንቃት ነገሮችን የሚያጤን በትጋት ኃላፊነቱን የሚወጣ ሆኖ መገኘት ይጠበቅበታል ። በዚህም ተግባሩ በኮሌጁ የሚፈጠሩ ብልሹ አሰራሮችን በመከላከሉ ረገድ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርግም ይጠበቃል ። ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ከሚያስችሉ ተግባራት አንዱ ሃብትን ማሳወቅ/ማስመዝገብ አንዱ ነው ።
ከጥቅምት 15 - 19/2017ዓ.ም ከየስራ ክፍሉ ለተውጣጡ ባለሙያዎች የተሠጠው ስልጠና እነኝህን መሠረት በማድረግ በመሆኑ እያንዳንዱ ሠራተኛ የተጣለበትን ኃላፊነት እንዲወጣ እና ለስራው መሳካት ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት መልእክት ተላልፏል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን በተነሱ ሀሳቦች ላይ የስነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ወ/ሮ ዝግጁ ግዛቸው እና የህንጻ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አላዩ ጉችዬ በጋራ የማጠቃለያ ሃሳብ እና መደረግ ስላለባቸው የጥንቃቄ ስራዎች አቅጣጫ የሰጡ ሲሆን የሚያጋጥሙ አንዳንድ ችግሮችን ዳይሬክቶሬቱ ባመቻቸው የተዋረድ አሰራር ማሳወቅ እንደሚጠበቅባቸው አቅጣጫ አመልክተው ውይይቱ ተጠናቋል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+6
ጥቅምት 20/2017ዓ.ም
የበጀት ዓመቱ የአዲስ ገቢ ሰልጣኞች ቅበላ
ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች የ2017የትምህርት ዘመን የአዲስ ገቢ ሰልጣኞች ቅበላን በተሳካ ሁኔታ ለማከናወን ያስችል ዘንድ ከስልጠና ዘርፎች እና ከሚመለከተው አካል የተውጣጣ ኮሚቴ አዋቅሮ የቅድመ ዝግጅት ስራው ላይ ከስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች እና ከተዋቀረው ኮሚቴ አባላት ጋር በጋራ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል።
ተያይዞም ከይፋዊ የመቁረጫ ነጥብ ውሳኔ በኋላ ዓርብ ጥቅምት 15/2017ዓ.ም ጀምሮ የምዝገባ ስራው የተጀመረ ሲሆን በስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የእንኳን ደህና መጣችሁ እና አጠቃላይ ስልጠናውን አስመልክቶ ገለጻ ተደርጎላቸዋል ። በተመሳሳይ ስልጠና ዘርፎች በትምህርት ክፍላቸው የሚሰጡ የስልጠና መስኮችን አስመልክቶ፣ የወርክ ሾፖቻቸውን አደረጃጀት፣በገበያ ላይ ያላቸውን ተፈላጊነት በማስረዳት ሰልጣኞች ዘርፉን እንዲቀላቀሉ ገለጻዎችን በማድረግ ምርጫቸውን በዕውቀት ላይ ተመስርተው እንዳመርጡ ስለሚመርጡት ዘርፍ ኖሃው እንዲኖራቸው በማድረግ የምዝገባ ስራው በመከናወን ላይ ነው።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ጥቅምት 18/2017ዓ.ም
ቀጣይነት ላለው ድጋፍ የምክክር ስብሰባ ተካሄደ።
በዛሬው ዕለት የቆዳ ስልጠና ዘርፍ እና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችን ያካተተ የምክክር ስብሰባ ተካሂዷል።
ስብሰባውን የጠራው CVM/community volunteers for the world/የተሰኘ ድርጅት በአዲስ አበባ ከሚገኙ የቆዳ ስራ ስልጠና ከሚሰጡ ኮሌጆች ጋር የነበረውን ከ2ዓመት በላይ የዘለቀ የትብብር ግንኙነትን የበለጠ ለማጠንከር ታልሞ የተዘጋጀ መሆኑ በምክክር ስብሰባው ተወስቷል። በነበረው ግንኙነት በሁለቱም አካላት በተለዩ ክፍተቶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመሙላት በሙያው ብቃት ያላቸው ሠልጣኞችን ለስራ ገበያው ማቅረብ ላይ አስተዋጽኦ ማድረግ ስለመሆኑም በምክክር ስብሰባው ተብራርቷል ።
በተለየው ክፍተት መሠረትም ለቆዳ ስራ ስልጠና ዘርፍ አሰልጣኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና ከመስጠቱ በላይ ለማሰልጠን ስራው የሚጠቀሙባቸውን ማሽኖች ባለሙያ በመመደብ የጥገና ድጋፍ አገልግሎት እና የመለዋወጫ መሳሪያ ድጋፍ ለሁለተኛ ግዜ አበርክቷል። ከክህሎት ክፍተት ስልጠናው በተጨማሪ 5/አምስት የጥገና ማንዋል ተዘጋጅቶ የተሰጠ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል።
የዛሬው ምክክር ስብሰባ ከካሁን ቀደሙ የተለየ የሚያደርገው እንደዚህ አይነት የትብብር ድጋፍ በውጭና በውስጥ ያሉት ባለድርሻ አካላት ተገቢ መረጃ አግኝተው ቀጣይነት ላለው ድጋፍ እና በመስኩ የሚደረገውን ትብብር ለማጠናከር እንዲረዳ የየኮሌጁ የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችም 'በአድቮኬሲ' / ስራዎቹን በማስተዋወቅ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ታስቦ የተከናወነ በመሆኑ ነው።
በዛሬው ዕለት ለኮሌጃችን የተበረከተው ጥቅል የማሽኖች መፍቻ /kit/ እና 24 ዓይነት የመለዋወጫ ድጋፍ በብር 400,756.60 /አራት መቶ ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ስድስት ከስልሳ ሳንቲም/መሆኑን ከመረካከቢያ ሰነዱ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።
ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናችን የላቀ መሆኑን ስንገልጽ ትብብሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና ኮሌጃችንም ብቁ ባለሙያዎችን አሰልጥኖ ለገበያ የማቅረቡ ስራ የተሳካ እንዲሆን እንደነዚህ ዓይነት ትብብሮችን የበለጠ በማጠናከር ቢሰራበት እንላለን ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
