Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Відкрити в Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
Показати більше3 588
Підписники
+224 години
-17 днів
+4230 день
Архів дописів
ለልማት ሲባል የሚለቀቅ የመሬት ይዞታን በተመለከተ:-በግለሰቦች የተያዘን የመሬት ይዞታ ለሕዝብ ጥቅም ሲባል ወይም ለሌላ ሰፊ ልማት ግንባታ ተብሎ ይዞታው እንዲለቀቅ ሲፈለግ የሚለቀቅበትን መንገድ፣ ካሣ የሚከፈልበት እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን በ2011 ዓ.ም በአዋጅ ቁጥር 1161/2011 ቁጥር የተመዘገበ ሕግ ወጥቶ ነበር። በዚህ ዓመት ደግሞ (ታህሳሥ 2016 ዓ.ም) ያንን ሕግ ለማሻሻል ረቂቅ አዋጅ የጸደቀ ሲሆን በዚህ ረቂቅ አዋጅ ላይ የሚከተሉት ነጥቦች ተነስተውበታል። 1) መሬት እንዲለቀቅለት የተወሰነለት አካል ለሥራው የሚፈለገውን መሬት መጠንና የሚገኝበትን ትክክለኛ ስፍራ የሚያሳይ ውሳኔ የተሰጠበት ማስረጃ ቢያንስ ሥራው ከመጀመሩ ከአንድ ዓመት በፊት ለከተማው ወይም ለወረዳው አስተዳደር ማቅረብ አለበት። 2) መሬት የሚለቀቅለት አካል መንግሥታዊ ተቋም ከሆነ የአካባቢው የመንግሥት ክፍል (የልማት ስራው የሚካሄድበት የክልል፤ የወረዳ ወይም የከተማ አስተዳደር) ለባለይዞታዎች የሚከፈለውን የንብረት ካሳ፤ የልማት ተነሺ ድጋፍ፤ የኢኮኖሚ ጉዳት ካሳ፤ የማህበራዊ ትስስር መቋረጥ እና የስነ ልቡና ጉዳት ካሳ ወጪ የመክፈል ግዴታ አለበት። የመሬት ይዞታው እንዲለቀቅለት የተወሰነለት ከመንግሥታዊ መዋቅር ውጪ ከሆነ ግን መሬቱ እንዲለቀቅ የተወሰነለት አካል የተዘረዘሩትን ካሳዎች እና የመቋቋሚያ ወጪ ለከተማው ወይም ለወረዳው አስተዳደር ገቢ አድርጎ በአስተዳደሩ በኩል ተፈጻሚ ይሆናሉ። 3) የካሣ ገንዘቡ ለልማት ተነሺው ካልተከፈለ አስተዳደሩ ከመሬቱ አያስለቅቀውም። 4) ይግባኝ ማቅረብ የሚፈልግ የልማት ተነሺ (በተሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ወገን) አቤቱታውን ለይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ውሳኔው በጽሁፍ ከደረሰው ቀን ጀምሮ በ፴ (ሰላሳ) ቀናት ውስጥ ማቅረብ አለበት። 5) ይግባኝ ሰሚ ጉባኤው በሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ወገን ውሳኔው በጽሁፍ ከደረሰው ቀን ጀምሮ በ፴ (ሰላሳ) ቀን ውስጥ ይግባኝ ለክልል ከፍተኛው ፍርድ ቤት፣ በአዲስ አበባ እና በድሬደዋ ከተሞች ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ማቅረብ ይችላል። ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ ይግባኝ ማለት የሚፈልግ ከሆነ ልማቱ እንዲይጓተት ቦታውን አስረክቦ ክርክሩን የመቀጠል መብት አለው። 6) ተነሺው ንብረቱን በማስረከቡ እና በቅሬታ ምክንያት ካሳውን ባለመውሰዱ ለይግባኙ ክርክር የሚሆን በቂ ገንዘብ ከሌለው እና በዚህ ምክንያት የሚቸገር ከሆነ መንግስት ነፃ የህግ አገልግሎት የሚያገኝበትን ሁኔታ ያመቻቻል።
እንኳን አደረሳችሁ!እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ: የሰላም የፍቅር የደስታ የመረዳዳት የመከባበር እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!
ከግንባታ ስራ ጋር ቀጥተኛተያያዥነት ያላቸው ከ100,000 ሺ' በላይ አባሎች ያሉበት የቴሌግራም የግንባታ ግብዓት ንግድ ግሩፕ ላይ ምርትና አገልግሎትዎን ያስተዋውቁ!
በትብብር በተዘጋጀው የቴሌግራም "ዩ ኒ ቲ ፕላትፎርም ላይ ይቀላቀሉ! ይጠቀሙበትለበለጠ መረጃ ስልክ: 📞+251-989-999-001 | +251- 707-999-001 | 09-12-815619 ቴሌግራም: በ t.me/unitysupplydbot ላይ መልዕክት ቢልኩልን እናስተናግዳለን
ዒድ ሙባረክ!🙏ዩ ኒ ቲ ኮን.ካታሎግ ሰርቪስ ድህረ-ገፃችን: t.me/UnitySupplierdb1 ☜|]ያጋሩ! በቀላሉ በእጅ ስልክዎ መረጃ ይከታተሉ
እንኳን አደረሳችሁ!እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ: የሰላም የፍቅር የደስታ የመረዳዳት የመከባበር እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!
ከግንባታ ስራ ጋር ቀጥተኛተያያዥነት ያላቸው ከ100,000 ሺ' በላይ አባሎች ያሉበት የቴሌግራም የግንባታ ግብዓት ንግድ ግሩፕ ላይ ምርትና አገልግሎትዎን ያስተዋውቁ!
በትብብር በተዘጋጀው የቴሌግራም "ዩ ኒ ቲ ፕላትፎርም ላይ ይቀላቀሉ! ይጠቀሙበትለበለጠ መረጃ ስልክ: 📞+251-989-999-001 | +251- 707-999-001 | 09-12-815619 ቴሌግራም: በ t.me/unitysupplydbot ላይ መልዕክት ቢልኩልን እናስተናግዳለን
ዒድ ሙባረክ!🙏ዩ ኒ ቲ ኮን.ካታሎግ ሰርቪስ ድህረ-ገፃችን: t.me/UnitySupplierdb1 ☜|]ያጋሩ! በቀላሉ በእጅ ስልክዎ መረጃ ይከታተሉ
አዲሱ የቤት ሽያጭ ዋጋ ተመን አሰራር እና ታክስ አገልግሎት ክፍያ ማንዋል ቁጥር 01/2016በአዲስ አበባ ከተማ ለአፓርትመንት ቤቶች እና ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ወይም ኮንዶሚኒየም ቤቶች አማካኝ የሽያጭ ዋጋ ተመን በ34 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል። በተሻሻለው የቤት ሽያጭ ዋጋ ተመን መሰረት ከኮንደሚንየም እና አፓርትመንት ውጪ ለሆኑ ግንባታዎች፦ የግንባታ ነጠላ ዋጋ በጭቃ የተሰራ ቪላ ቤት (G+0) ነጠላ ዋጋ በካሬ 15,000 ብር፣ በብሎኬት የተሰራ የቪላ ቤት (G+0) ነጠላ ዋጋ በካሬ 20,000 ብር፣ የህንጻ ወለላቸው ከG+1 እስከ G+5 25,000 ብር እና፣ G+6 እና በላይ የሆኑ ቤት ወይም ህንጻ ነጠላ ዋጋ በካሬ 30,000 ተደርጓል፡፡ የቦታው መገኛ ዋጋ ('location value') ለከተማው የቦታ ደረጃ የጸደቀው ወቅታዊ አማካይ የሊዝ ጨረታ ዋጋ እንዲሆን መደረጉም ተገልጿል። የቤት ስም ንብረት ዝውውር ክፍያ ማለትም አሹራ 4 በመቶ እና የቴምብርአገልግሎትን ቀረጥ 2 በመቶ ከጠቅላላ የቤቱ ሽያጭ ዋጋ ተሰልቶ ከ ከመጋቢት17 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ እንዲከፈልም ታዟል። ይህ ማሻሻያ መምሪያ ከመውጣቱ በፊት የስም ንብረት ዝውውር አገልግሎት ጠይቀው በሂደት ላይ ሆኖ ክፍያ የፈጸሙ ተጋልጋዮች በቀድሞ አሰራር በከፈሉት ክፍያ መሰረት ይስተናገዳሉ ተብሏል። ግንባታቸው ያልተጠናቀቁ ህንፃዎች የትመና ስራ የሚሰራላቸው ግንባታው በደረሰበት ወይም አሁን ላይ ባለበት ግንባታ ደረጃ እንደሚሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ያሳውቃል።
ዲዛይን ስታረጉ ማስታወስ ያለባችሁ ህግ1. መስኮት ስታበጁ ከ አጎራባች 2 ሜትር ገባ በሉ 2. ለ ሽንትቤት ከ 60 ሳንቲም በታች የሆነ መስኮት ስታበጁ 1.5 ሜትር ገባ በሉ
Here is some tips you need to remember designing in Addis Ababa1. To provide a window you need to offset 2 meter from your boundary line 2. To provide bathroom window <60 cm you need to offset 1.5 meters
በፓናል ውይይት ላይ እንዲሳተፉ ስለመጋበዝ🙏ለአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኀበራት ምክር ቤት አባላት በሙሉ ከአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ዓላማ፣ ተግባራትና ከአባላት ጥያቄዎች በመነሳት "የብድር አቅርቦት እና ተጽዕኖው በቢዝነስ ላይ" በሚል ርዕሰ የፓናል ውይይት የተዘጋጀ ሲሆን ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግሥት፣ የንግዱ ማሕበረሰብ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ አካላት የሚሳተፉበት ይሆናል፡፡ የፓናል ውይይቱ በዋናነት በሶስት አበይት ነጥቦች፡- 1) "በኢትዪጵያ - የብድር አቅርቦት መመሪያዎች ሚና በሁለንተናዊ ሀገራዊ ልማት ላይ" 2) "ለግሉ ዘርፍ፡ የብድር ተጠቃሚነት ሁኔታና የሚታዩ ተግዳሮቶች" 3) "የንግድ ባንኮች የብድር አቅርቦትና አሰጣጥ ላይ ያጋጠሟቸው ዋና ዋና ችግሮች እና መፍትሔዎቻቸው" ላይ የሚያተኩር ሲሆን ሐሙስ ሚያዝያ 03 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 - 7፡30 በሚካሄደው በዚህ የፓናል ውይይት ላይ እንዲገኙ በአክብሮት ተጋብዘዋል፡፡ ለመመዝገብ ይህንን ፎርም ሞልተው፡- 1. የድርጅት ስም፡ ___ 2. የተሳታፊ ስም፡ ___ 3. ሃላፊነት፡ ___ 4. ስልክ ቁጥር፡ ___ 5. ኢሜይል፡ ___ በኢሜይል፡ membership.addischamber@gmail.com or addischamber@gmail.com. ይላኩልን በምዝገባ ወቅት የፓናል ውይይቱ የሚከናወንበት ቦታ እናሳውቃለን፡፡ ለተጨማሪ መረጃ በ0911-376543/0115-519817 ይደውሉ፡፡ ከሰላምታ ጋር Source: CCAOE
*ማስታወቂያ* ለተከበራችሁ የማኅበራችን አባላት!የአምስተኛ ዙር የHealth and Safety in Construction ስልጠና የሚሰጠው በሚቀጥለው ሳምንት ሐሙስ (03/08/2016 ዓ/ም) እና አርብ (04/08/2016 ዓ/ም) ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ሙሉ ቀን ቦሌ ሜጋ ህንፃ ፊት ለፊት በሚገኘው ሀንሰም ህንፃ ላይ በሚገኘው የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት 8ተኛ ፎቅ ላይ ባለው የስልጠና አዳራሽ ይሆናል፡፡ ለአምስተኛ ዙር ስልጠና ያልተመዘገባችሁ የማኅበራችን አባላት ምዝገባው እስከ አርብ መጋቢት 27 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ብቻ በመሆኑ የማህበሩ አባላት ባሉን ውስን ቦታዎች እንድትመዘገቡ ማኅበራችን ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ስልጠናውን ለአባሎቶቻችን ለማዳረስ እንዲቻል ከ100 በላይ ሰልጣኞችን ለማሰልጠን ቦታዎችን ያመቻቸን ስለሆነ አባላት በቶሎ እንድትመዘገቡ እንጠይቃለን፡፡ በስዚህበስልክ ቁጥሮች 0115-52-56-31/0941-80-87-88 ደውላችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ 🚧 "Think safety, work safely."ደህንነትን አስብ ፤ በጥንቃቄ ስራ"🚧 የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማኅበር
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
