uk
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Відкрити в Telegram

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Assaye Derbie

Канал Assaye Derbie (@asayede) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 14 346 підписників, посідаючи 2 649 місце в категорії Блоги та 2 354 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 14 346 підписників.

За останніми даними від 24 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -112, а за останні 24 години на -7, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 39.43%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 12.21% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 656 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 752 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 33.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 25 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Блоги.

14 346
Підписники
-724 години
-387 днів
-11230 день
Архів дописів
መዓዛ መሐመድ ወደ ጠባቡ እስር ቤት ተመልሳለች። እኔ እምለው ግን... በየወሩ ዩቲዩብ የሚከፍላት ገንዘብ በየወሩ ከእስር ቤት ለመውጣት ለምትከፍለው የዋስትና ብር ይበቃት ይሆን?
መዓዛ መሐመድ ወደ ጠባቡ እስር ቤት ተመልሳለች። እኔ እምለው ግን... በየወሩ ዩቲዩብ የሚከፍላት ገንዘብ በየወሩ ከእስር ቤት ለመውጣት ለምትከፍለው የዋስትና ብር ይበቃት ይሆን?

photo content

የአጤ ቴዎድሮስን ክንድ የወረሱ ጀግኖች የዶክተር ቴዎድሮስን ብርጌድ ደቁ*ሰው ለአንድ ዓመት በወራሪ እጅ የቆየችውን የማይጠብሪን ከተማ ነጻ አውጥተዋል። ዘላቂ ድል፦ ለኢትዮጵያ ጥምር ጦር
የአጤ ቴዎድሮስን ክንድ የወረሱ ጀግኖች የዶክተር ቴዎድሮስን ብርጌድ ደቁ*ሰው ለአንድ ዓመት በወራሪ እጅ የቆየችውን የማይጠብሪን ከተማ ነጻ አውጥተዋል። ዘላቂ ድል፦ ለኢትዮጵያ ጥምር ጦር

ኣይተ ጌታቸው ረዳ "እኔ ሙቼ የአማራና የትግራይ ሕዝብ ወንድማማችነት ይቀጥል" የሚል ምክረ ሐሳብ አቅርቧል። እናም ሟ*ች ሐሳቡን ቀይሮ ወንድማማች ማገዳደሉን ሳያጠናክር በፊት ለገ*መድ የሚያመች አን
ኣይተ ጌታቸው ረዳ "እኔ ሙቼ የአማራና የትግራይ ሕዝብ ወንድማማችነት ይቀጥል" የሚል ምክረ ሐሳብ አቅርቧል። እናም ሟ*ች ሐሳቡን ቀይሮ ወንድማማች ማገዳደሉን ሳያጠናክር በፊት ለገ*መድ የሚያመች አንገት እንደሌለው ታውቆ ከአንድ ጠርሙስ አረቄ ጋር ፈርፍሮ የሚጎነጨው እር*ሳስ ቢመቻችለት...😆

ከእጃችሁ የገባውን ሰነድ ለእራሳችሁ ጋብዘናል!! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ እኛ አማራዎች ባለፉት አራት ዓመታት መጠነ-ሰፊ አገራዊና መንግሥታዊ ጥቃቶችን ብናስተናግድም ያ ሁሉ ማለቂያ የለሽ ክህደት ግን በመንግሥት ላይ ያለንን እምነት ከመቀማት ባለፈ ከአንጋፋው ባላንጋራችን ጎን ተሰልፈን የእራሳችን አገር ላይ ጥቃት እንዲንከፍት ሊያደርገን አይቻለውም። ➔ለዚያም ነው የግብጽና የሱዳን ኃይሎች ጸረ አገር ድርጅት ፍለጋ ሩቅ መኼድ የተገደዱት፡፡ ➔ለዚያም ነው ጦር መሣሪያ የጫኑ አንቶኖቮች በእኛ ጠፈር ላይ ተራምደው ከሌላ ምድር ሲያርፉ የሚታዩት፡፡ ➔ለዚያም ነው ጌታቸው ረዳ ‹‹ከመንግሥት በላይ የአማራ ኤሊት ላይ የምናወራርደው ሒሳብ አለን›› እያለ ሲዝት የኖረው፡፡ ያም የጌታቸው ረዳ ዛቻ በአመራር እጦት እውን ሆኖ በርካታ ጥቃት ብናስተናግድም ሊያጠነክረን እንጂ ሊሰብረን ባለመቻሉ ባሁኑ ዙር ወረራ ታደሰ ወረደ እና ጌቾ ከተብታባ አንደበታቸው በሚፈልቁ ለስላሳ ቃላት የአማራን ኤሊት አንጀት ለመብላት ሞክረዋል። ይሄንንም ከእባ*ብ አንደበት የተሰማን የእርግብ መልዕክት ከማጣጣል ባለፈ ለመቀበል የሞከረ አማራ ባልታየበት ሁኔታ "ኢመደበኛ" እና "ጽንፈኛ" በሚል ፍረጃ መንግሥት አዘጋጅቶት የአማራን ወጣት ሲያጠቃበት የከረመውን ሰነድ ባለቤቱን ቀይራችሁ መልቀቅ አይጠበቅባችሁም፡፡ ምክንያቱም በባለፉት ሁለት ዙር ዘመቻዎች የተገኘውን የድል ጅማሮ ወደ ትግል ሲቀይር፣ ለአሸባሪዎች ያዘጋጀውን አፈሙዝ ወደ አማራ ፋኖዎችና አንቂዎች ሲያዞር እንዲሁም ከጠላት ጋር ሲደራደር የታየው መንግሥት እንጂ የአማራ ኤሊት አይደለም፡፡ በዚህኛው ዘመቻም ቁጥሩ ቀላል የማይባል የአማራ ኤሊት እንደ ቀድሞው ከመንግሥት ጎን ተሰልፎ በገንዘብ ከሚዘወሩ አክቲቪስቶች ጋር ለማረብረብ ባይደፍርም ከጥምር ጦሩ ሠራዊት ጎን ተሰልፎ ትግሉን እየደገፈ ነው፡፡ መላው የአማራ ሕዝብም በደጀንነት ሲሳተፍ፣ ፋኖው እና ሚኒሻው ደግሞ በቅሬታ ውስጥ ሆኖም ቢሆን ወደ ወራሪው ምሽግ ቃታውን እየሳበ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ግን ዛሬ ሥጋታቸውን የሚገልጹትንም ሆነ ዝምታን የመረጡትን ወገኖች በሽብር ድርጅት ተላላኪነት እየወነጀሉ እንዲሁም ‹‹ዋናውን አሸባሪ ደምስሰን ስንመለስ አንለቃችሁም›› እያሉ በድል ጎዳና የሚረማመዱ አክቲቪስቶች ጥቅማቸው እስካልተቋረጠ ድረስ የትኛውም ስፍራ ላይ ዘመቻው ቢቋረጥ ግድ ስለማይሰጣቸው... መንግሥት ጅምሩን ድል ወደ ሌላ ዙር ትግል ቀይሮት ወደ ኋላ መመለስ የጀመረ ቀን ደግሞ ‹‹ትግሉ በድል መቋጨት አለበት›› የሚሉ ወገኖችን ስውር ፍላጎት እና የድርድርን አስፈላጊነት እያብራሩ መመለሳቸው አይቀርም። በተረፈ የጠላትን እኩይነት በመረዳትና ለትግሉ ታማኝ ሆኖ በመገኘት ረገድ ሕዝባዊ ክፍተት ስለሌለ ከእጃችሁ የገባውን ሰነድ ከመንግሥታችሁ ጋር ቁጭ ብላችሁ ብታነቡት ጥሩ ነው፡፡ ወይም ደግሞ የአሸባሪው አጋሮች አማርኛ ጠል ስለሆኑ በሌላ ቋንቋ ብታዘጋጁት ይሻላል። ድል ለኢትዮጵያ ጥምር ጦር‼️

ይቀላቀሉ

የሀገር መከላከያ ሠራዊት ደጀን ሆኖ በመገኘት ረገድ "የዓመቱ ብርቱ ሕዝብ" አማራ‼️
+4
የሀገር መከላከያ ሠራዊት ደጀን ሆኖ በመገኘት ረገድ "የዓመቱ ብርቱ ሕዝብ" አማራ‼️

ማታ 2:30

‼️‼️
‼️‼️

ባለ ሽርጣሙ ጄነራል ሃሰን ከረሙ ለከፋፋዮች ያስተላለፈው መልዕክት👇 “የምስራቅ አማራ ፋኖ እና የእኛ የወሎ ፋኖን ሊያጣሉን ወይም ደግሞ እርስ በእርስ ሊያጋጥሙን ይፈልጋሉ እንጂ እኛማ ጎን በጎን ተ
+1
ባለ ሽርጣሙ ጄነራል ሃሰን ከረሙ ለከፋፋዮች ያስተላለፈው መልዕክት👇 “የምስራቅ አማራ ፋኖ እና የእኛ የወሎ ፋኖን ሊያጣሉን ወይም ደግሞ እርስ በእርስ ሊያጋጥሙን ይፈልጋሉ እንጂ እኛማ ጎን በጎን ተሰልፈን እየተዋደቅን ነው። ከውስጣችን የበቀሉ ባንዳዎችና ጥቅመኞች እኛን ከፋፍለው ለማባላት ጥረት ቢያደርጉም እጅ ለእጅ ተያይዘን እየታገልን ነው። ባንድ ማዕድ በልተን፣ ባንድ ግንባር ተሰልፈን ባንድ ጉድጓድ እየተቀበርን ነው። እኛን በሥም ከፋፍለው አንዱን ፋኖ የሚያወድሱና ሌለኛውን የሚያንኳስሱ ከፋፋዮች እንደ ውሻ ሊያናክሱን ቢከጅሉም እኛ ግን የመጣብንን ወራሪ በመመከት ላይ እንገኛለን። ስለዚህ ልዩነቱን የሚዘሩት ሌሎች እንጂ እኛ በወንድማማች መንፈስ ተቃቅፈን አማራን ለማተራመስና አገር ለማፍረስ ከመጣው ወራሪ ጋር እየተፋለምን ነው።" 👏👏 "እልልታ የዋጠው እሪታ" በሚለው መጽሐፌ ላይ የሽርጥ ለባሹን ጄኔራል ገድል ስጽፍ በጦር ሜዳ ካደረገው መራር ትግል ባለፈ የከፋፋዮችን ተንኮል በማክሸፍ ረገድ ስለተጫወተው ሚና መተረኬ ልክ ነበር። ክብር ፥ ለሽርጥ ለባሹ የጦር ሜዳ አርበኛና ብልህ ፖለቲከኛ!!

‹‹ክልልን አገር ለማድረግ የወልቃይትን ምድር በኃይል መቆጣጠር ግድ ነው›› የሚል ውሳኔ ያስተላለፈው የሽብር ቡድን በሱዳን እና በእራሱ ምድር ሲያሰለጥነው የከረመውን ጦሩን ስምሪት ሰጠ፡፡ በዚህም መ
‹‹ክልልን አገር ለማድረግ የወልቃይትን ምድር በኃይል መቆጣጠር ግድ ነው›› የሚል ውሳኔ ያስተላለፈው የሽብር ቡድን በሱዳን እና በእራሱ ምድር ሲያሰለጥነው የከረመውን ጦሩን ስምሪት ሰጠ፡፡ በዚህም መሠረት እኩሉ ወራሪ ‹‹ኡዛዛ አሌና›› የሚለውን ሙዚቃ እያንጎራጎረ ከሱዳን መሬት ተነሳ፡፡ እኩሉ ደግሞ ‹‹እምበር ተጋዳላይ›› በሚለው ዜማ ተከዜን ተሻግሮ ነፍጡን አነሳ፡፡ ይሄውም ጥቃት እንደሚከሰት እርግጠኛ ሆኖ በንቃት ሲጠባበቅ የነበረው ጥምር ጦር ‹‹ወልቃይት ጠገዴ ፥ ሑመራና ዳንሻ፤ ተቆርሶ የሚሰጥ ፥ አይደለም አንባሻ›› በሚል ቁጣ ፈጣን እርምጃ መውሰድ ጀመረ፡፡ በተመሳሳይ ጊዜም የከባድ መሣሪያ እሩምታ የሰማው፣ በማይካድራ፣ በሑመራ አየር መንገድና በገሐነም የጅምላ ጉድጓድ ውስጥ ሲቀበር የኖረው የወልቃይት አማራም ነቅሎ በመውጣት ወራሪውን ወረ ረ፡፡ የሚገነጠል ምድር ፍለጋ የገባውን የሽብር ሠራዊትም እንደ ዶሮ ብልት መገነጣጠ ል ጀመረ፡፡ እናም… የኮንክሪት ምሽግ ገል ሆኖ በወገን ጦር ፈርጣማ ክንድ ተፈረካከሰ፡፡ አገር ለማፍረስና የንጹሐን ደም ለማፍሰስ ከሱዳን የገባው ወራሪም ከወልቃይት የእጣን ዛፍ የተለቀመ አድሩስ ሆኖ ምሽግ የሚል ሥም በሰጠው ምድጃው ውስጥ ጨሰ፡፡ እድለኛ የሆነው ደግሞ ክላሹን እና ሐሺሹን ጥሎ ስደተኛ በሚል ሥም ወደ ሱዳን ተመለሰ፡፡ እራሱን ለድል እንደተፈጠረ ሠራዊት ቆጥሮ የተከዜ ወንዝ የተሻገረው ወራሪ ኃይልም ወደ ሲ*ዖል የተወረወረ እንጨት መሆኑን በተረዳ ጊዜ ከእሳት ይልቅ በውሃ ሙላት መበላትን መርጦ እራሱን ወደ ተከዜ ወንዝ ወረወረ፡፡ በአጎናፍር የተሞላው የተከዜ ወንዝም የኢትዮጵያ ወታደር እና የግንብ አጥር ሆኖ አላሳልፈው ባለ ጊዜ በእራሱ እጅ እና በእራሱ ፈንጂ ባፈረሰው ድልድይ ፈንታ ከሰማይ የወረደ ጀልባ መፈለግ ጀመረ፡፡ ክብር ለወገን ጦር!

አራቱን ዞን ትተህ- አማራን አንድ በል አሳዬ ደርቤ ከሸዋ፣ ከጎንደርና ከወሎ ምድር የተነሱ የአማራ ፋኖዎች በወልድያ ግንባር ከመከላከያ ሠራዊቱና ከአማራ ልዩ ኃይል ጎን ተሰልፈው ወራሪውን ኃይል ሲለ
አራቱን ዞን ትተህ- አማራን አንድ በል አሳዬ ደርቤ ከሸዋ፣ ከጎንደርና ከወሎ ምድር የተነሱ የአማራ ፋኖዎች በወልድያ ግንባር ከመከላከያ ሠራዊቱና ከአማራ ልዩ ኃይል ጎን ተሰልፈው ወራሪውን ኃይል ሲለበልቡት የዋሉት እንዲህ የሚል ቅሬታ እያቀረቡ ነበር።፡ ‹‹ወሎ ደቦ ጠርቶ- ሲታጨድ አዝመራ ቀድሞ ካልደረሰ- የጎጃም አማራ ትግሉም አላማረ - ድሉም አልደመቀ ስልተ ምት ቀያሪው- በላይ ካልዘለቀ የየጁ ማዶ እህል - ከእኛ አልቢን ባያልፍም መች ሙሉነት አለ ፥ ያለ አረንዛው ጎጃም .......እናም በውጊያ መሀከል -ጉድለት ከሚሰማን ዘመነን ማስረሻ- አጃቢ ላክልን፡፡›› ሲሉ ውለው ነበር፡፡ ሹሞች ከፈጠሩበት ቅሬታ ይልቅ የወንድሞቹን ስሞታ ያስቀደመው የጎጃም አማራም እንዲህ ከሚል የአቋም መግለጫ ጋር አባይን ተሻግሮ መትመም ጀምሯል፡፡ ‹‹በታትነውኝ እንጂ- መዋቅሬ ፈርሶ መቼ እቆይ ነበረ- ሠርጌ ተደግሶ እናም... የታሰርኩበትን - ቀላድ በጣጣሼ ጉዞ ስለጀመርኩ- ካዝናዬን አጉርሼ ወንድምና ወንድም ፥ በጎጥ የምትከፍል አራቱን ዞን ትተህ- አማራን አንድ በል››

እንደ እሬት የሚመር እውነት ▬▬▬▬ በባለፉት ሁለት ዙር ዘመቻዎች አሸባሪውን ኃይል ከምት አፋፍ መልሶ ሕይወት የሰጠው... የአውሮፓ ሕብረት አይደለም። ግብጽ አይደለችም። ሱዳን አይደለችም። አየርላንድ አይደለችም። ምዕራባውያን አይደሉም። ብልጽግና አይደለም። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እንጂ!! አሁንም ቢሆን ወራሪውን ኃይል ከሞት አፋፍ ታድጎ ሌላ ዙር የጦርነት እድል የሚፈጥርልን ይሄው ጠቅላይ ሚኒስትር መሆኑን አልጠራጠርም።

ወልቃይት ጠገዴ ፥ ዳንሻና ሑመራ ሴቷም ታጥቃ ወጣች ፥ ሰርግ እንደተጠራ፡፡ ለሕግ እንቢ ያለ ፥ ለዳኛ ያልተገዛ ተከዜን ተራምዶ ፥ ጉራውን ሲነዛ በእናት አልቢን ታጭዶ ፥ እንደ ሳር ጠነዛ፡፡ ተው እ
+1
ወልቃይት ጠገዴ ፥ ዳንሻና ሑመራ ሴቷም ታጥቃ ወጣች ፥ ሰርግ እንደተጠራ፡፡ ለሕግ እንቢ ያለ ፥ ለዳኛ ያልተገዛ ተከዜን ተራምዶ ፥ ጉራውን ሲነዛ በእናት አልቢን ታጭዶ ፥ እንደ ሳር ጠነዛ፡፡ ተው እረፍ እያሉት ፥ የሰው ቀየ አትውረር በኮሪደር ፈንታ ፥ ሸለሙት መቃብር፡፡ አሳዬ ደርቤ

መከላከያን ማክበር ባሕላችን በመሆኑ ምክር አያስፈልገንም!! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ይህ ጦርነት የተጀመረው በአማራ እና በትግራይ ክልል መሀከል በተፈጠረ ጠብ ሳይሆን የአገር ኩራት የሆነውን የሰሜን እዝ
መከላከያን ማክበር ባሕላችን በመሆኑ ምክር አያስፈልገንም!! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ይህ ጦርነት የተጀመረው በአማራ እና በትግራይ ክልል መሀከል በተፈጠረ ጠብ ሳይሆን የአገር ኩራት የሆነውን የሰሜን እዝ በመደብደብ ነበር። በመከላከያ ሠራዊቱ ላይ የተፈጸመውን ክሕደት የሰማው የአማራ ሕዝብም ልዩ ኃይልና ሚኒሻ በሚል ሥም ከሌሎች የመከላከያ እዞች ጋር ተሰልፎ ሕይወቱን በመገበር አገሩን አሸናፊ አደረገ። ከስምንት ወራት ቆይታ በኋላም በራስ አሉላ ሥም በተሰየመ የክሕደት ኦፕሬሽን ያው ጠላት ያንኑ ጥቃት ሰነዘረ። የአማራና የአፋር ክልልም ተወረረ። ከዚያን ቀን አንስቶም የአማራ እና የአፋር ሕዝቦች መከላከያን ከመንከባከብ ባለፈ ከጎኑ ተሰልፈው በጥይት በመንገብገብ ላይ ይገኛሉ። እናስ ስለ ዘለፋ የምታወሩት ከየት አምጥታችሁ ነው? ለመሆኑ የኢትዮጵያን መከላከያ ሠራዊት በማክበርና በማስተናገድ ረገድ ከአማራ ወጣት/ኤሊት/አክቲቪስት የሚስተካከል አለ እንዴ? የአገሩ ሠራዊት ሲመጣ ታቦት የወጣ ይመስል እልልል የሚል ሕዝብ የሚታየውስ አማራ ክልል አይደለም እንዴ? እናም እላለሁኝ... አማርኛ ተናጋሪ ሁሉ አማራ ስላልሆነ ምክሩንም ሆነ ተግሳጹን ለሌሎች ብታደርጉት ነው የሚሻለው። እኛ ዘንድ መከላከያን ማክበር ባሕል ነው። ፋኖውና ልዩ ኃይሉም ከመከላከያው ጋር አብሮ ከመሰዋትና ሕይወቱን ከመገበር ባለፈ እራሱን ማነፃፀር አይሻም። ዘላለሚዊ ክብር እና ዘላቂ ድል ለመከላከያ ሠራዊታችን!!

መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች‼️ አሳዬ ደርቤ ➔ወራሪው ኃይል ወልድያን ባልተቆጣጠረበት ሁኔታ ደሴና ኮምቦልቻ ላይ ሆናችሁ የኤቲኤም ማሽኖቻችሁንና ካዝናዎቻችሁን አራቁታችሁ ሽብር የምትፈጥሩ ባንኮች እን
+2
መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች‼️ አሳዬ ደርቤ ➔ወራሪው ኃይል ወልድያን ባልተቆጣጠረበት ሁኔታ ደሴና ኮምቦልቻ ላይ ሆናችሁ የኤቲኤም ማሽኖቻችሁንና ካዝናዎቻችሁን አራቁታችሁ ሽብር የምትፈጥሩ ባንኮች እንደ ባለፈው በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ አስቀምጣችሁ ለወራሪዎች ማስረከብ ባይኖርባችሁም እንደ አባይ ባንክ ተገቢውን አገልግሎት ስጡ፡፡ ➔የብልጽግና ካድሬዎች በልባችሁ ውስጥ የሌለውን ሕዝባዊና አገራዊ ተቆርቋሪነት ማንጸባረቅ ቢሳናችሁ እንኳን ንቀታችሁን መደበቅ ብሎም ለሕዝብ ሞራል መጠንቀቅ ከባድ አይደለምና የአሸንዳ በዓሉን እና የሰብል ጉብኝቱን ተውት፡፡ ወይም ደግሞ በድብቅ አክብሩት፡፡ ➔የአማራ ክልል አመራሮች በየወረዳው የሚሰባሰቡ ፋኖዎችን በዐይነ ቁራኛ ከመከታተል ፈንታ ወራሪውን ለመከላከል ቅድሚያ ስጡ፡፡ ➔አሁናዊ የወረራ ስጋት ባለባቸው አካባቢዎች የምትኖሩ የአማራ ወጣቶች በየሰፈራችሁ የጸጥታ ግብረ-ኃይሎችን በማዋቀር ሕዝብን የማረጋጋትና አካባቢያዊ ችግሮችን የመፍታት ሥራ ስሩ፡፡ ➔የትኛውንም የአማራ ክልል ከተሞች ከወራሪዎች የመታደጊያ ስፍራው የጁ ላይ መሆኑን ተገንዝበን የመጣብንን ማዕበል ወደ ኩሬው እንመልስ፡፡