Joseph Math Tutor
Відкрити в Telegram
Hello, welcome to Joseph Math Tutor channel! https://youtu.be/D8K0MVqynVA?si=y_uFeHG7awC1oX9Y Subscribe our youtube channel On tiktok : josephmathtutor Owner: Yosef Adefris @yosef_2580
Показати більше1 763
Підписники
+324 години
+387 днів
+9030 день
Архів дописів
1 767
እንኳን አደረሳችሁ
ዛሬ እንደሚታወቀው የመስቀል በዓልን እያከበርን ነው። እናም ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁንና ሁላችንም በቤታችን እያከበርን ነው ኖረንም አልኖረንም ተሰባስበን እያከበርን ነው። ነገር ግን በዚህ ሰዓት ምንም ደጋፊ የሌላቸው ወገኖቻችን አሉ ምን በላችሁ? ምን ጠጣችሁ? ምን ለበሳችሁ? ብሎ የሚጠይቃቸው ወገን የሌላቸው አሉ እናም ሰሞኑን ያቋቋምነው #Charity ለዚህ ጊዜ የሚሆን ነው። እኛ ካለን ብር አሰባስበን ወስደን ስናግዛቸው የሚሰማቸው ደስታ እና ተስፋ ለካስ ሰው አለኝ የሚል ስሜት አስቡት እስቲ?!
በዚህ ዓመት ከመስከረም 30 ጀምሮ በየወሩ እየሰበሰብን አቅመ ደካማዎችን ልንረዳ ዝግጅታችንን ጨርሰናል እስካሁንም ከ40 በላይ ሰው ተመዝግቧል።
የምንረዳው ለሁሉም ነው እምነት ዘር ቀለም ሳንለይ Charity ውስጥም ሁሉም ሰው መሳተፍ ይችላል።
ለመመዝገብ የሚያስፈልገው ቅን ልብ ብቻ ነው። እኔ መቼ ራሴን ቻልኩና፤ መቼ ከቤተሰብ ተላቀኩና ፤ ከየት አምጥቼ ነው የምረዳው የሚሉ የሰነፍ ሰው ሀሳቦችን አስወግዱ ለመርዳት ከታሰበ ቀላል ነው ደግሞም የሚረዳው በገንዘብ ብቻ ሳይሆን በሀሳብም ነው።
"ለችግረኛ የሚያስብ ብጹዕ ነው"
መዝ 40÷1
መልካም በዓል
1 767
#ASTU/AASTU
በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፣
በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብታችሁ በአፕላይድ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የሚሰጠዉ ማክሰኞ መስከረም 20/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
➫ ተፈታኞች ለፈተናው መመዝገባችሁን የሚገልፅ ከሲስተም ላይ በማወረድ ፕሪንት አድርጋችሁ መያዝ ያስፈልጋል፡፡
➫ ተፈታኞች ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያና የአድሚሽን ካርዳችሁን በመያዝ በምዝገባ ወቅት በመረጣችሁት የፈተና ማዕከል ከተጠቀሰው ሰዓት ቀደም ብላችሁ መገኘት አለባችው፡፡
➫ ተፈታኞች ሞባይል ስልክ እና ስማርት ሰዓት ይዞ ወደ ፈተና ማዕከል መምጣት የተከለከለ ነው፡፡
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
1 767
ማስታወቂያ
በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፣
በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብታችሁ በአፕላይድ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የሚሰጠዉ ማክሰኞ መስከረም 20/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
ተፈታኞች ለፈተናው መመዝገባችሁን የሚገልፅ ከሲስተም ላይ በማወረድ ፕሪንት አድርጋችሁ መያዝ ያስፈልጋል፡፡
ተፈታኞች ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያና የአድሚሽን ካርዳችሁን በመያዝ በምዝገባ ወቅት በመረጣችሁት የፈተና ማዕከል ከተጠቀሰው ሰዓት ቀደም ብላችሁ መገኘት አለባችው፡፡
ተፈታኞች ሞባይል ስልክ እና ስማርት ሰዓት ይዞ ወደ ፈተና ማዕከል መምጣት የተከለከለ ነው፡፡
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
@Joseph_maths_tutorial
1 767
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ።
መልካም የደመራ በዓል ❤️
1 767
#ASTU ለምትገቡ ተማሪዎች የተከፈተ አዲስ ግሩፕ
በግሩፑ ውስጥ
✅ ስለ ግቢው አጠቃላይ ሁኔታ
✅ የሁሉንም Freshman course Material
✅ በ Joseph Math Tutorial የሚሰጡ Tutorial sessionoch
✅ ያላችሁን ጥያቄ የምትጠይቁበት ነው።
#Share it for your partners
1 767
#Registration
የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2018 ዓ.ም መግቢያ ፈተና የምዝገባ ጥሪ
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለአገራችን ሁለንተናዊ ዕድገት መሳካት በሳይንስና ቴክኖሎጂ የሰለጠነ የሰው ሀይል ፍላጎትን ለማሟላት የበኩላቸዉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ በመንግስት ልዩ ተልዕኮ ተሰጥቷቸው የተደራጁ ሲሆን በዘርፉ ብቃት ያላቸውን ሙያተኞችን በማፍራት ላይ ይገኛሉ፡፡
በመሆኑም በ2018 ዓ.ም. በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በአፕላይድ ተፈጥሮ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ የተወሰነውን 50% እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተጨማሪ የመግቢያ ፈተና በበይነ-መረብ (online) በመስጠት የዩኒቨርሲቲዎቹን መስፈርት የሚያሟሉ ተማሪዎችን ተቀብለን በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ለማስተማር እንፈልጋለን፡፡ በየዩኒቨርሲቲዎቹ የሚሰጡ ትምህርቶችን ዝርዝር ከታች ተያይዟል፡፡
የምዝገባ ጊዜ፡-
• ከመስከረም 13 እስከ መስከረም 18 ቀን 2018 ዓ.ም
ምዝገባው የሚጠናቀቀው፡-
• መስከረም 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ይሆናል፡፡
የምዝገባ ቦታ፡
• የምዝገባ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች በማንኛውም ስፍራ በኢንተርኔት (online) በ https://stuexam.astu.edu.et/ ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ፡፡
• ፈተናው የሚሰጥበት ቀን፡ በድረ-ገጻችን የምዝገባው ቀን ካበቃ በኋላ እናሳውቃለን።
ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ፡-
• በምዝገባ ወቅት በመረጡት ዩኒቨርሲቲ (የፈተና ጣቢያ) በአካል በመቅረብ ይሆናል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
• አመልካቾች የሀገር አቀፍ ፈተና አድሚሽን ቁጥራቸውንና ሌሎች መረጃዎችን በትክክል መሙላታቸውን ማረጋገጥ አለባቸው ፡፡
• የፈተና ጣቢያዎቹ ያላቸው የመፈተኛ ቦታ ውስን በመሆኑ ይህንኑ አውቃችሁ ቅድሚያ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን፡፡
• በቂ አመላካቾች የሌሉባቻው የፈተና ጣቢያዎች በቅርበት ወደሚገኙ የፈተና ጣቢያዎች ሊታጠፉ እንደሚችሉ እናሳውቃለን፡፡
• ለምዝገባና ለፈተና ምንም አይነት ክፍያ አይጠየቅም፣
• ከሚመዘገቡት አመልካቾች ውስጥ ለፈተና የሚቀርቡት ስም ዝርዝራቸው እና የፈተና ጣቢያዎች በሚከተሉት ድረ-ገፆች፡- www.astu.edu.et: www.aastu.edu.et እንደአስፈላጊነቱም በe-mail የሚገለፅ ይሆናል፡፡
• አመልካቾች ከወዲሁ ፈተናው በሚሰጥባቸው የትምህርት ዓይነቶች፣ ማለትም (ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል) ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስ፣ ሂሳብና እንግሊዝኛ እንዲዘጋጁ ይመከራል፡፡
• ፈተና የሚሰጠው በበይነ-መረብ (online) ስለሆነ አመልካቾች በፈተና ጊዜ ሊያጋጥም የሚችል ግራ መጋባትን ለማስቀረት በምዝገባ ጊዜ ከመመዝገቢያ ፎርማቱ ጋር ተያይዞ የቀረበውን የሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ ይመከራል፡፡
• አመልካቾች ለፈተና ሲቀርቡ የ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት፣ የሀገር አቀፍ ፈተና አድሚሽን ካርድ (ወይም መታወቂያ) እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
• የመግቢያ ፈተናውን የሚያልፉ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሚደረገው የዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ አይካተቱም፡፡
• በውጤታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ ከላይ በተጠቀሱት ድረ-ገፆች ይገለፃል፡፡
• በመስፈርቱ መሰረት ያልተመረጡ አመልካቾች ከዚህ በፊት እንደሚደረገው በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች የሚመደቡ ይሆናል፡፡
• በፈተናው ዕለት ማንኛውንም የሞባይል ስልኮችንና ስማርት ሰዓቶችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት የተከለከለ ነው፡፡
• በፈተና ወቅት ያልተገባ ተግባር መፈፀም በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን ድረ-ገፆች መጎብኘት ይቻላል፡፡
www.astu.edu.et; www.aastu.edu.et
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፡፡
1 767
+1
#AASTU/ASTU
AASTU/ASTU መግባት ለምትፈልጉ ተማሪዎች በሙሉ
የምዝገባ ጊዜ፦
➫ ከመስከረም 13 እስከ መስከረም 18 ቀን 2018 ዓ.ም
ምዝገባው የሚጠናቀቀው፡-
➫ መስከረም 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ይሆናል፡፡
መመዝገቢያ Link
➫ https://stuexam.astu.edu.et/
በዚህ Link በመጠቀም እና አቀራራቢያችሁ ያለውን መፈተኛ University በመምረጥ መመዝገብ ትችላላቹ።
@Joseph_maths_tutorial
1 767
#Registration
👉 በ2017 ዓ.ም ኢንተራንስ አልፋችሁ ASTUን መቀላቀል ፈልጋችሁ የመግቢያ ፈተናውን የምትጠባበቁ በርካታ ተማሪዎች “ምዝገባ ተጀምሯል እንዴ? ፣ መቼ ነው የምንመዘገበው? ፣ መቼ ነው ግቢ የምንገባው?” እያላችሁ እየጠየቃችሁን ነው።
👉 የመመዝገቢያ ሊንክ እስከአሁን አልተለቀቀም ፤ ስለዚህ ምዝገባም አልተጀመረም። ሊንኩ ሲለቀቅ ምዝገባውም አብሮ ይጀምራል። ምዝገባው ከፊታችን ባሉት ጥቂት ቀናት ይጀምራል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ግቢ የምትገቡት ደግሞ ዩኒቨርስቲው ባሳወቀው ቀን ነው። የመግቢያ ፈተናውን ተፈትናችሁ ውጤት ከወጣ በኋላ ፈተናውን አልፋችሁ ASTU ለተመደባችሁ ተማሪዎች ወደግቢ የምትገቡበትን ቀን ዩኒቨርስቲው ይፋ ያደርጋል። እኛም እናሳውቃችኋለን!
እስከዚያው ድረስ ለፈተናው እየተዘጋጃችሁ በትዕግሥት ጠብቁ!
1 767
ASTU የምትገቡ ተማሪዎች ግቢ ከገባችሁ በኋላ የሁሉንም Course Material የምታገኙበት ቻናል👇👇👇
https://t.me/josephmathtutor
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
