Chefie Bulbula Pre-Primary, Primary and Middle School
Відкрити в Telegram
Показати більше
1 140
Підписники
+124 години
+107 днів
+5030 день
Архів дописів
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ዘንድሮ ለተመዘገበው ውጤት ከተማ አስተዳደሩ ለትምህርት ስራዉ ልዩ ትኩረት በመስጠት መንቀሳቀሱ ፣ የትምህርት ቤት ምገባ መርሀ ግብር ተጠናክሮ መቀጠሉ ፣ የሂሳብና እንግሊዘኛ ትምህርት ስትራቴጂ ተነድፎ በትኩረት መስራት መቻሉ ፣ የመማሪያና የማስተማሪያ ግብዓቶች መቅረባቸው እንዲሁም ከትምህርት ባለድርሻ አካላት ጋር በተለይም ከወላጆች ጋር በቅንጅት መሰራቱ ተጠቃሽ መሆናቸውን ኃላፊው አብራርተዋል::
በከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ስርአቱ የብዝሀ ቋንቋ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ አማርኛ እና አፋን ኦሮሞ እንደሁለተኛ ቋንቋ የተማሩ ተማሪዎች በትምህርት አይነቶቹ ፈተና መውሰዳቸውን ዶክተር ዘላለም አስታውሰው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናን ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች መካከል 543 ያህሉ ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸውን አስታውቀዋል።
ተፈታኝ ተማሪዎች ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ተጠቁሟል።
https://aa6.ministry.et/#/result
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+2
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2018 የትምህርት ዘመን 97.48% የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ ተዘዋወሩ፡፡
(ሰኔ 29/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 97.48 % የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ አስታወቁ።
ኃላፊው የ2018 የትምህርት ዓመት የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑን በማስመልከት ለተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በጋዜጣዊ መግለጫቸው በከተማ አስተዳደሩ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 84,257 ተማሪዎች መካከል 82,137 የሚሆኑ ተማሪዎች 50 በመቶ እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የትምህርት እርከን መሸጋገራቸውን አስታውቀዋል።
ኃላፊው አያይዘውም ዘንድሮ 97.48% የሚሆኑ ተማሪዎች 50 እና በላይ በማምጣት ወደ ዘጠነኛ ክፍል ያልፉበት ውጤት በ2017 ዓ.ም ከነበረው 95% አንጻር እድገት ማሳየቱን ገልጸው ውጤቱ እንዲመዘገብ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ መምህራን ፣ የትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ለወላጆችና ለሌሎች ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
https://aa6.ministry.et/#/result
የ6ኛ ክፍል በዚህ👆 ሊንክ መመልከት ትችላላችሁ።
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+5
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን ተወሰነ።
(ሰኔ 28/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ቢሮው በ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር የተለያዩ ተግባራት ማከናወኑን ጠቅሰው ውጤቱ እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ዶክተር ዘላለም አያይዘውም በ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል እንዲቻል የማጠናከሪያ ትምህርት ከመሰጠቱ ባሻገር ተማሪዎች በሒሳብና እንግሊዘኛ ትምህርት ውጤታማ እንዲሆኑ ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ መደረጉ ለተመዘገው ውጤት ያበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ፈተናውን በአጭር ጊዜ በማረም ውጤቱ ይፋ እንዲሆን ቀን ከሌት ሲሰሩ ለቆዩ የፈተና ክፍል ባለሙያዎችና ሂደቱን ሲደግፉ ለነበሩ አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ በ2018 ዓ.ም 84,257 ተማሪዎች በ199 የፈተና ጣቢያዎች ፈተና መውሰዳቸውን ገልጸው የዘንድሮ ውጤት ከዚህ በፊት ከነበረው አንጻር እድገት ማሳየቱን አስታውቀዋል፡፡
በመርሀግብሩ ማጠቃለያ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% ፣ የአካል ጉዳተኞች 45% እንዲሁም የኦቲስቲክ ዳውን ሲንድረምና ኢንተሌክቹዋል ዲሴቢሊቲ ላለባቸው ተማሪዎች 40% እንዲሆን የቀረበውን የማለፊያ ነጥብ በሙሉ ድምጽ አጽድቀዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
በዛሬው ዕለት (28/10/2018 ዓ.ም) በት/ቤታችን የዓመቱ ትምህርት መጠናቀቅን አስመልክቶ ለተማሪዎች የውጤት መግለጫ ካርድ የመስጠትና በተማሪዎች ውጤት እንዲሁም ስነ-ምግባር ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።
በመድረኩም:
1. የተቋሙ የአጠቃላይ የ2018 ዓ.ም የስራ አፈፃፀም እና የ2019 ዓ.ም የስራ እቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
2. በሁለቱም ስርዓተ-ትምህርት የውጤት ትንተና ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
3. በወተመህ በኩል የ2019 ዓ.ም የስራ እቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
4. የተማሪ ወላጆች ት/ቤቱ የተማሪ ውጤት እና ስነ-ምግባርን ለማሻሻል በሚደራቸው ስራዎች ከጎኑ እንደሆኑ ቁርጠኝነታቸውን በሃሳብ አሳውቋል።
5. ለደረጃ ተማሪዎች የሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
6. የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተቀምጦ መድረጉ በሰላም ተጠናቋል።
Guyyaa har'aa (28/10/2018 A.L.H) mana barnootaa keenyatti xumuramuu bara barnootaa ilaalchisee barattootaaf kaardii gabaasa firii barnootaa kennuun, akkasumas qabxii fi naamusni barattootaa maal akka fakkaatu irratti mariin gaggeeffameera.
Waltajjicharrattis:
1. Raawwiin hojii waliigalaa mana barumsaa kan bara 2018 fi karoorri hojii kan bara 2019 dhiyaatee irratti mari'atameera.
2. Sirna barnootaa lamaaniinuu xiinxalli/qaaccessi qabxii barattootaa dhiyaatee irratti mariin taasifameera.
3. GMB'tiin raawwiin hojii bara 2018 fi karoorri hojii bara 2019 dhiyaatee irratti mari'atameera.
4. Maatiin barattootaa carraaqqii manni barumsaa bu'aa fi naamusa barattootaa fooyyessuuf taasisurratti cinaa akka dhaabbatan waadaa galaniiru.
5. Barattoota sadarkaa 1ffaa-3ffaa ba'aniif badhaasni waraqaa ragaa kennameeraf.
6. Kallattiin hojii fuulduraa kaa'amuun waltajjichi nagaadhan xumurameera.
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ጠዋት ይፋ ይሆናል፡፡
(ሰኔ 28/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ጠዋት ይፋ ይደረጋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 የትምህርት ዘመንን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ አርሞ ይፋ ማድረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 8 -10 /2018 ዓ.ም ድረስ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 199 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሶስት ቀናት መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
በዛሬው ዕለት (28/10/2018 ዓ.ም) በት/ቤታችን የዓመቱ ትምህርት መጠናቀቅን አስመልክቶ ለተማሪዎች የውጤት መግለጫ ካርድ የመስጠትና በተማሪዎች ውጤት እንዲሁም ስነ-ምግባር ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።
በመድረኩም:
1. የተቋሙ የአጠቃላይ የ2018 ዓ.ም የስራ አፈፃፀም እና የ2019 ዓ.ም የስራ እቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
2. በሁለቱም ስርዓተ-ትምህርት የውጤት ትንተና ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
3. በወተመህ በኩል የ2019 ዓ.ም የስራ እቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
4. የተማሪ ወላጆች ት/ቤቱ የተማሪ ውጤት እና ስነ-ምግባርን ለማሻሻል በሚደራቸው ስራዎች ከጎኑ እንደሆኑ ቁርጠኝነታቸውን በሃሳብ አሳውቋል።
5. ለደረጃ ተማሪዎች የሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
6. የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተቀምጦ መድረጉ በሰላም ተጠናቋል።
Guyyaa har'aa (28/10/2018 A.L.H) mana barnootaa keenyatti xumuramuu bara barnootaa ilaalchisee barattootaaf kaardii gabaasa firii barnootaa kennuun, akkasumas qabxii fi naamusni barattootaa maal akka fakkaatu irratti mariin gaggeeffameera.
Waltajjicharrattis:
1. Raawwiin hojii waliigalaa mana barumsaa kan bara 2018 fi karoorri hojii kan bara 2019 dhiyaatee irratti mari'atameera.
2. Sirna barnootaa lamaaniinuu xiinxalli/qaaccessi qabxii barattootaa dhiyaatee irratti mariin taasifameera.
3. GMB'tiin raawwiin hojii bara 2018 fi karoorri hojii bara 2019 dhiyaatee irratti mari'atameera.
4. Maatiin barattootaa carraaqqii manni barumsaa bu'aa fi naamusa barattootaa fooyyessuuf taasisurratti cinaa akka dhaabbatan waadaa galaniiru.
5. Barattoota sadarkaa 1ffaa-3ffaa ba'aniif badhaasni waraqaa ragaa kennameeraf.
6. Kallattiin hojii fuulduraa kaa'amuun waltajjichi nagaadhan xumurameera.
በዛሬው ዕለት (28/10/2018 ዓ.ም) በት/ቤታችን የዓመቱ ትምህርት መጠናቀቅን አስመልክቶ ለተማሪዎች የውጤት መግለጫ ካርድ የመስጠትና በተማሪዎች ውጤት እንዲሁም ስነ-ምግባር ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።
በመድረኩም:
1. የተቋሙ የአጠቃላይ የ2018 ዓ.ም የስራ አፈፃፀም እና የ2019 ዓ.ም የስራ እቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
2. በሁለቱም ስርዓተ-ትምህርት የውጤት ትንተና ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
3. በወተመህ በኩል የ2019 ዓ.ም የስራ እቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
4. የተማሪ ወላጆች ት/ቤቱ የተማሪ ውጤት እና ስነ-ምግባርን ለማሻሻል በሚደራቸው ስራዎች ከጎኑ እንደሆኑ ቁርጠኝነታቸውን በሃሳብ አሳውቋል።
5. ለደረጃ ተማሪዎች የሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
6. የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተቀምጦ መድረጉ በሰላም ተጠናቋል።
Guyyaa har'aa (28/10/2018 A.L.H) mana barnootaa keenyatti xumuramuu bara barnootaa ilaalchisee barattootaaf kaardii gabaasa firii barnootaa kennuun, akkasumas qabxii fi naamusni barattootaa maal akka fakkaatu irratti mariin gaggeeffameera.
Waltajjicharrattis:
1. Raawwiin hojii waliigalaa mana barumsaa kan bara 2018 fi karoorri hojii kan bara 2019 dhiyaatee irratti mari'atameera.
2. Sirna barnootaa lamaaniinuu xiinxalli/qaaccessi qabxii barattootaa dhiyaatee irratti mariin taasifameera.
3. GMB'tiin raawwiin hojii bara 2018 fi karoorri hojii bara 2019 dhiyaatee irratti mari'atameera.
4. Maatiin barattootaa carraaqqii manni barumsaa bu'aa fi naamusa barattootaa fooyyessuuf taasisurratti cinaa akka dhaabbatan waadaa galaniiru.
5. Barattoota sadarkaa 1ffaa-3ffaa ba'aniif badhaasni waraqaa ragaa kennameeraf.
6. Kallattiin hojii fuulduraa kaa'amuun waltajjichi nagaadhan xumurameera.
