ar
Feedback
Chefie Bulbula Pre-Primary, Primary and Middle School

Chefie Bulbula Pre-Primary, Primary and Middle School

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 088
المشتركون
-224 ساعات
+37 أيام
-330 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from N/a
📚 የተፈታኞች መብትና ግዴታ ✅ 📚 ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት  አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና   ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት። 📚 ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል። 📚 ተፈታኙ/ኟ የሰራበትን የመልስ ወረቀት ለፈታኙ በመስጠት  የጥያቄ ወረቀቱን ይዞ መውጣት ይችላል 📚 ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ከመጀመሩ በፊት በፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የግል መለያ መረጃዎችን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተከተል ጽፎ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ)። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ የራሱን ችሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ 📚 የሚሠራባቸው የጥያቄና የመልስ መስጫ ወረቀቶች ለሌሎች ተፈታኞች ዕይታ የተጋለጡ እንዳይሆኑ ሸፍኖ መስራት ይኖርበታል 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና የመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት  የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ። 📚 እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ። 📚 ይህንን ባለማድረጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ተፈታኙ  ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ የሚያውኩ ሁኔታዎች ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ችግሩን በመግለጽ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይችላል ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባከነ ጊዜ ተጨማሪ ሰዓት አይፈቀድም 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ከመፈታኛው ቦታ በመገኘት መቀመጫቸውን መያዝ አለባቸው። 📚 ፈተናው ከተጀመረ ከ15 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሽ መግባት አይፈቀድለትም። 📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም። 📚 ይሁን እንጂ ፈተናው ከተጀመረ ከ45 ደቂቃ በኋላ ከፈተና አዳራሹ ለመውጣት   እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ የመልስ ወረቀቱን ለፈታኙ አስረክቦ በጸጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። 📚 ፈተናው ሊጠናቀቅ ከ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀረው የሚጨርስ ተፈታኝ የሁሉም ተፈታኞች የመልስ ወረቀቶች እስኪሰበሰቡና ለፈተናው የተፈቀደው የጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድረስ በቦታው ተቀምጦ እንዲቆይ ይደረጋል። 📚 ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ የተቀደደ ወይም የተበላሸ የፈተና ጥያቄ ጥራዝ ከገጠመው ወይም የተሰጠው የመልስ ወረቀት የተበላሸ ከሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሽበት እጁን አንስቶ በመጠየቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይችላል። ለተፈታኞች የተፈቀዱ ✅ እርሳስ ✅ የተማሪዎች የደንብ ልብስ (UNIFORM) ✅ ADMISSION CARD ✅ ላጲስ፣ መቅረጫና ማስመሪያ ለተፈታኞች የተከለከሉ ❌ ስልክ ይዞ መግባት አይቻልም ❌ ካልኩሌተር ❌ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ❌ ሰዓት ❌ በሀኪም ከታዘዘ ውጪ የሆኑ መነጽሮች ❌ የሚነበቡ ጽሁፎች በሙሉ

ማሳሰቢያ ለት/ቤታችን ትምህርት ክፍል ተጠሪዎች እና መ/ራን በሙሉ 1. የማጠቃለያ ፈተና ዛሬ (04/10/2018 ዓ.ም) ተባዝቶ ተቆጥሮ ዝግጁ መሆኑን ማረጋገጥ፣ 2. ያለቁትን የውጤት ትንተና ከስር ከስር ገቢ ማድረግና እስከ ቀን 12/10/2018 ዓ.ም ድረስ በቴሌግራም @negussieteriesa መላክ፣ 3. የመፅሐፍ ግምገማ እስከ ዛሬ (04/10/2018 ዓ.ም) ከቀኑ 11:00 በሶፍትና በሃርድ ኮፒ ፈርሞ ገቢ ማድረግ፣ እና 4. ውጤት ታርሞ ተማሪው እንደወቀ ሲስተም ላይ ማስገባት እንዲሁም ሌሎች የማጠቃለያ ስራዎችን መስራት እንዳይዘንጋ። የተማሪ ውጤት ከሲስተም ላይ ፕሪንት ተደርጎ እያንዳንዱ ተማሪ ፈርሞበት ነው ክሊራንስ የሚፈረመው። በመሆኑ የአንድም ተማሪ ውጤት ሲስተም ላይ ባይገባ ክሊራንስ የማይፈረምና ኢፊሸንሲም የማይሞላ መሆኑ ታሳቢ ይደረግ።

የ2018_ዓ_ም_ከተማ_አቀፍ_የ8ኛ_ክፍል_ፈተና_የሚፈትኑ_መምህራን_ምደባ.pdf1.15 KB

የ2018_ዓ_ም_8ኛ_ክፍል_ከተማ_አቀፍ_ፈተና_በፈተና_ቆጣሪነት_የተመደቡ_መምህራን.pdf3.86 KB

የ2018_ዓ_ም_የ8ኛ_ክፍል_ከተማ_አቀፍ_ፈተና_አስፈፃሚ_ሱፐርቫይዘሮች_ምደባ.pdf0.68 KB

+4
ለ6ኛ_ክፍል_ፈተና_በቆጣሪነት_የተመደቡ_መምህራን_ምደባ_2018.pdf0.33 KB

የ6ኛ ክፍል የከተማ አቀፍ ፈተና ምደባ

✅ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። ✅ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን። 📌 ለሁሉም ተፈታኞች መልካም የጥናትና የፈተና ጊዜ! 👏👏👏👏

✔️ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም ዙሪያ ሊያውቋቸው የሚገቡ ጉዳዮች ✅የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀ
+3
✔️ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም ዙሪያ  ሊያውቋቸው የሚገቡ  ጉዳዮች ✅የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ✅ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ብቻ ማጥቆር አለበት፡፡ ✅ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ✅ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን የአራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ✅በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ መልስ (የአራት ማዕዘን ቅንፍ/Square Bracket) ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ✅ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ✅ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ✅ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ✅መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ✅ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ ✅ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ።

✔️ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም ዙሪያ ሊያውቋቸው የሚገቡ ጉዳዮች ✅የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀ
+3
✔️ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተና መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም ዙሪያ  ሊያውቋቸው የሚገቡ  ጉዳዮች ✅የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ✅ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ብቻ ማጥቆር አለበት፡፡ ✅ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ✅ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን የአራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ✅በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ መልስ (የአራት ማዕዘን ቅንፍ/Square Bracket) ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ✅ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ✅ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ✅ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው አራት ማዕዘን ቅንፍ (Square Bracket) መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ✅መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ✅ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ ✅ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ።

✅ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። ✅ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን። 📌 ለሁሉም ተፈታኞች መልካም የጥናትና የፈተና ጊዜ! 👏👏👏👏

ቀን/Guyyaa 28/09/2018 ዓ.ም / A.L.I ለት/ቤታችን የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች በሙሉ በቀን 28/09/2018 ዓ.ም አስቸኳይ ውይይት ስላለን ከቀኑ 6:30 ላይ በት/ቤቱ ምክትል ርዕሰ መምህራን ቢሮ እንድትገኙ ስንል እናሳውቃለን። ​Itti gaafatamtoota Muummee Mana Barumsaa keenyaa hundaaf: ​Guyyaa 28/09/2018 A.L.I marii ariifachiisaa waan qabnuuf, sa'aatii 6:30 irratti Biiroo Itti Aantota Hogganaa Mana Barumsaatti akka argamtan isin beeksifna. ት/ቤቱ Mana Barumsichaa

book evaluation form.docx0.23 KB

የመፅሐፍ መገምገሚያ ቅጵ Guca Madaallii Kitaabaa

photo content

እንደምን አደራችሁ ሰኞ አገራዊ ምርጫ የሚካሄድበት ቀን በመሆኑ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ዝግ እንደሚሆኑ ይታወቃል። ሆኖም ግን በመስሪያ ቦታቸው አካባቢ የምርጫ ካርድ ያወጡ ሰራተኞች ድምጽ መስጠት እንዲችሉ የፕብሊክ ትራንስፖርት አውቶቡሶች ጠዋት በመደበኛው ሰዓት አግልግሎት የሚሰጡ ሲሆን ከሰዓት ደግሞ ከቀኑ 6፡30 ወደቤታቸው ለመመለስ ስምሪት ተሰጥቷቸዋል። ስለሆነም በመስሪያ ቤታቸው አካባቢ ካርድ ያወጡ ሰራተኞች እስከ ስድስት ሰዓት ድምጽ ሰጥተው እንዲመለሱ ኦሬንቴሽን እንዲሰጣቸው/መልዕክት እንዲተላለፍላቸው እናሳውቃለን። መልካም ቀን

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ሰኞ ግንቦት 24 ሥራ ዝግ ነው። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ/ም በፌዴራል እና ክልል መንግሥታዊ ተቋማት እንዲሁም የግል ተቋማት ሥራ ዝግ ሆኖ ይውላል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 2
+1
ሰኞ ግንቦት 24 ሥራ ዝግ ነው። ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ/ም በፌዴራል እና ክልል መንግሥታዊ ተቋማት እንዲሁም የግል ተቋማት ሥራ ዝግ ሆኖ ይውላል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚካሄደውን የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል። ቦርዱ፦ - ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል። - ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ዝግ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል። - የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ እንዲያከነውኑ ፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት እንደማያስገድድ አሳውቋል። - የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ አረበታቷል። #NEBE ቲክቫህ ኢትዮጵያ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

ጤና ይስጥልን! ከአ/አ ከተማ አስተዳደር ት/ቢሮ በወረደውና በክፍለ ከተማ በኩል በደረሰን አቅጣጫ መሰረት የ2018 የትምህርት ዘመን የ2ኛው ወሰነ-ትምህርት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና ውጤ
ጤና ይስጥልን! ከአ/አ ከተማ አስተዳደር ት/ቢሮ በወረደውና በክፍለ ከተማ በኩል በደረሰን አቅጣጫ መሰረት የ2018 የትምህርት ዘመን የ2ኛው ወሰነ-ትምህርት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና ውጤት ለተማሪዎች ከ 20% የሚያዝ እና የውጤት ትንተናው የሚሰራው ግን ከሙሉ (100%) መሆኑን እናሳስባለበን። Akka kallattii Biiroo Barnootaa Bulchiinsa Magaalaa Finfinneen gadi bu’ee fi kutaa magaalaatiin nu dhaqqabeetti, firiin qormaata moodelaa kutaa 6ffaa fi 8ffaa semisteera 2ffaa bara barnootaa 2018 barattootaaf 20% irraa kan qabamuu fi qaaccessi qabxii kan hojjatamu garuu guutuu (100%) irraa ta'uu isaa isin hubachiifna. መልካም ጊዜ/Yeroo gaarii! ት/ቤቱ/M/B

+3
G 6 A.O AS 2ND LANGU. ANS.KEY.xlsx0.10 KB