Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)
Відкрити в Telegram
Показати більше
1 631
Підписники
+124 години
+97 днів
+1330 днів
Архів дописів
የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ2019 አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል::
+6
ኮርፖሬሽኑ በህክምና ላይ ለሚገኙ ህሙማን የበዓል ስጦታ አበረከተ
ኮርፖሬሽኑ ከራስ ቲያትር እና ከአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በተለያዩ ሆስፒታሎች ማለትም በአበበች ጎበና፣ በራስ ደስታ፣ ዘውዲቱ፣ ዳግማዊ ምኒሊክ እና ጋንዲ በመገኘት በህክምና ላይ ለሚገኙ150 ህሙማን የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመትን በማስመልከት የፍራፍሬ ምርቶችን ጳጉሜን 04/ 2018 ዓ.ም አበርክቷል፡፡
ኮርፖሬሽኑ ሶስተኛውን ዘንቢል ሱፐር ማርኬት ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ ከፈተ
የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በዋና መ/ቤት ግቢ ውስጥ ጳጉሜን 04 ቀን 2018 ዓ.ም ዘንቢል ሱፐር ማርኬት ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ በመክፈት ተደራሽነቱን በማስፋት ላይ ይገኛል፡፡
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በኃይሉ ንጉሴ ኮርፖሬሽኑ ያሉትን ሱፐር ማርኬቶች ቁጥር በመጨመር ተደራሽነቱን እያስፋፋ መሆኑን ጠቅሰው ከዚህ ቀደም በፒያሳና ሰሚት ሱፐር ማርኬቶች መከፈታቸውን አስታውሰዋል፡፡ በቀጣይም ሃይፐር ማርኬት ለመክፈት መታቀዱን በመጠቆም ህብረተሰቡ በአቅራቢያቸው የሚገኙ ሱፐርና ሚኒ ማርኬቶችን በመጠቀም ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲሸምቱ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በኮርፖሬሽኑ የኢንዱስትሪ ምርቶች ንግድ ዘርፍ ም/ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ዮሚ አበጀ በበኩላቸው ዘርፉ በአለ በጅምላ በኩል በጅምላ የሚያቀርባቸው ምርቶች አሁን በተከፈቱት ሱፐርና ሚኒ ማርኬቶች ውስጥ በችርቻሮ እየቀረቡ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይም በተለያዩ ከተሞች ላይ የማስፋፋት ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል፡፡
ሱፐር ማርኬቱ የኢንዱስትሪ ውጤቶች የሆኑትን የምግብ ዘይት፣ የስንዴ ዱቄት፣ ፓስታ፣ ማካሮኒ፣ የንጽህና መጠበቂያዎች እና የመሳሰሉትን በዓይነት፣ በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ የያዘ ሲሆን ቦታው ለተገልጋዮች ምቹና የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው፡፡
ኮርፖሬሽኑ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ሠራተኞች የአዲስ ዓመት ስጦታ አበረከተ
የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አነስተኛ ገቢ ላላቸው በአዲስ አበባና በክልል ቅርንጫፍ ግብይት ማዕከላት ለሚገኙ የቢሮ ውበትና የጽህፈት ሥራ ረዳት ሠራተኞች መጪውን አዲስ ዓመት በማስመልከት የ5ኪሎ የስንዴ ዱቄት እና የ5 ሊትር የምግብ ዘይት እንዲሁም የገንዘብ ስጦታ አበርክቷል፡፡
በዋና መሥሪያ ቤት በተካሄደው ሥነ-ሥርዓት የተዘጋጀውን ስጦታ የኮርፖሬሽኑ ሥራ አመራር አባላት ለሠራተኞች ያበረከቱ ሲሆን በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በኃይሉ ንጉሤ ባስተላለፉት መልዕክት ዝቅተኛ ገቢ እያገኙ ተቋማቸውን ለመቀየር እየተጉ የሚገኙ ሠራተኞች ተቋሙን ለማሳደግ ያላቸውን ጥረትና አስተዋጽዖ አድንቀው ኮርፖሬሽኑ ይህንኑ ቁርጠኝነታቸውን ከግምት በማስገባት በየበዓላቱ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ ተሳታፊ የነበሩት የኮርፖሬሽኑ ሰራተኞችም በተበረከተላቸው የአዲስ አመት ስጦታ መደሰታቸውን ከምስጋና ጋር ገልፀዋል::
የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አነስተኛ ገቢ ላላቸው የኮርፖሬሽኑ ሠራተኞች የአዲስ ዓመት ስጦታ አበረከተ
የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አነስተኛ ገቢ ላላቸው በአዲስ አበባና በክልል ቅርንጫፍ ግብይት ጣቢያዎች ለሚገኙ 81 የኮርፖሬሽኑ የቢሮ ውበትና የጽህፈት ሥራ ረዳት ሠራተኞች መጪውን አዲስ ዓመት በማስመልከት የ5ኪሎ የስንዴ ዱቄት እና የ5 ሊትር የምግብ ዘይት እንዲሁም በክልል ቅርንጫፍ ግብይት ጣቢያዎች ለሚገኙት የገንዘብ ስጦታ ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ/ም አበርክቷል፡፡
በዋና መሥሪያ ቤት በተካሂደው ሥነ ሥርዓት የተዘጋጀውን ስጦታ የኮርፖሬሽኑ ሥራ አመራር አባላት ለሠራተኞች አበርክተዋል፡፡ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በኃይሉ ንጉሤ ባስተላለፉት መልዕክት ዝቅተኛ ገቢ እያገኙ ተቋማቸውን ለመቀየር እየተጉ የሚገኙ ሠራተኞች ተቋሙን ለማሳደግ ያላቸውን ጥረትና አስተዋጽዖ አድንቀው፤ ኮርፖሬሽኑ ይህንኑ ቁርጠኝነታቸውን ከግምት በማስገባት በየበዓላቱ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸው አያይዘውም ኮርፖሬሽኑ የቢሮ ውበትና የጽህፈት ሥራ ረዳት ሠራተኞችን ለማገዝ በቅርቡ የደመወዝ ማሻሻያ ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ አሁን ካለበት ደረጃ በላይ ማደግ የሚችል ተቋም ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ ሁሉም ሠራተኛ አቅሙ የፈቀደለትን ጥረት በማድረግ ተቋሙን ወደተሻለ ዕድገት የማምጣት ኃላፊነት አለበት ብለዋል፡፡ “ተቋሙ ውጤታማ እየሆነ ሲመጣ የሚጠቀመው ህዝብና ራሱ ሠራተኛውም ጭምር” ነው ያሉት ሥራ አስፈጻሚው፤ ይህም በመሆኑ በዚያ ልክ መትጋት፣ ለተቋም ተቆርቋሪ መሆንና ውጤታማ መሆን ከሁሉም ይጠበቃል ብለዋል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ ተሳታፊ የሆኑት ሰራተኞችም በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡
በመጨረሻም ቀጣዩ ዓመት ለሠራተኛው የሠላም፣ የፍቅር፣ የተስፋና የ
+4
የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አነስተኛ ገቢ ላላቸው የኮርፖሬሽኑ ሠራተኞች የአዲስ ዓመት ስጦታ አበረከተ
የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አነስተኛ ገቢ ላላቸው በአዲስ አበባና በክልል ቅርንጫፍ ግብይት ጣቢያዎች ለሚገኙ 81 የኮርፖሬሽኑ የቢሮ ውበትና የጽህፈት ሥራ ረዳት ሠራተኞች መጪውን አዲስ ዓመት በማስመልከት የ5ኪሎ የስንዴ ዱቄት እና የ5 ሊትር የምግብ ዘይት እንዲሁም በክልል ቅርንጫፍ ግብይት ጣቢያዎች ለሚገኙት የገንዘብ ስጦታ ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ/ም አበርክቷል፡፡
በዋና መሥሪያ ቤት በተካሂደው ሥነ ሥርዓት የተዘጋጀውን ስጦታ የኮርፖሬሽኑ ሥራ አመራር አባላት ለሠራተኞች አበርክተዋል፡፡ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በኃይሉ ንጉሤ ባስተላለፉት መልዕክት ዝቅተኛ ገቢ እያገኙ ተቋማቸውን ለመቀየር እየተጉ የሚገኙ ሠራተኞች ተቋሙን ለማሳደግ ያላቸውን ጥረትና አስተዋጽዖ አድንቀው፤ ኮርፖሬሽኑ ይህንኑ ቁርጠኝነታቸውን ከግምት በማስገባት በየበዓላቱ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸው አያይዘውም ኮርፖሬሽኑ የቢሮ ውበትና የጽህፈት ሥራ ረዳት ሠራተኞችን ለማገዝ በቅርቡ የደመወዝ ማሻሻያ ማድረጉን ጠቁመዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ አሁን ካለበት ደረጃ በላይ ማደግ የሚችል ተቋም ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ ሁሉም ሠራተኛ አቅሙ የፈቀደለትን ጥረት በማድረግ ተቋሙን ወደተሻለ ዕድገት የማምጣት ኃላፊነት አለበት ብለዋል፡፡ “ተቋሙ ውጤታማ እየሆነ ሲመጣ የሚጠቀመው ህዝብና ራሱ ሠራተኛውም ጭምር” ነው ያሉት ሥራ አስፈጻሚው፤ ይህም በመሆኑ በዚያ ልክ መትጋት፣ ለተቋም ተቆርቋሪ መሆንና ውጤታማ መሆን ከሁሉም ይጠበቃል ብለዋል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ ተሳታፊ የሆኑት ሰራተኞችም በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡
በመጨረሻም ቀጣዩ ዓመት ለሠራተኛው የሠላም፣ የፍቅር፣ የተስፋና የ
+7
Ethiopian Investment Holdings
7͏m͏
Day 7 of the EFY 2018 Annual Performance Dialogue reviewed the performance of the Ethiopian Trading Businesses Corporation - ETBC (ETBC), which achieved 71.37% of its trading target, handling 1,098 million quintals supply of key commodities including cereal grains, pulses, oilseeds, coffee, spices and seasonings, FMCG products, and fresh produce. While ETBC continued to play a critical role in ensuring market supply, a provisional decline in gross profit underscored the need to drive growth, strengthen value addition, enhance operational efficiency, optimize asset and working capital utilization, and reinforce governance and financial discipline. Ethiopian Investment Holdings also emphasized the importance of sharpening ETBC's competitive positioning and its catalyst role in an increasingly liberalized trading landscape.
#EthiopianInvestmentHoldings #PerformanceDialogue #annualreview #DiversifyDriveDeliver #Ethiopia
+4
ኮርፖሬሽኑ በአዳማ ከተማ በተዘጋጀው የአዲስ ዓመት ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ እየተሣተፈ ይገኛል
የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን መጪውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በአዳማ ከተማ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ምርትና አገልግሎቶቹን እያስተዋወቀና ምርቶቹን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ ይገኛል፡፡
“አዳማ የንግድና ኢንቨስትመንት ከተማ 2018” በሚል መሪ ቃል ከነሀሴ 19 እስከ ጳጉሜ 4 ቀን 2018 ዓ/ም በሚካሄደውና የገበያ ንረትን የማረጋጋት፣ በአምራቾችና በንግድ ተቋማት መካከል ትስስርን የመፍጠር እንዲሁም የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን የማነቃቃት ተልዕኮ ባለው በዚህ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ኮርፖሬሽኑ የአትክልት፣ ፍራፍሬና የኢንዱስትሪ ውጤት የሆኑ ልዩ ልዩ ምርቶችን በስፋት ይዞ ቀርቧል፡፡
በተጨማሪም ለውጭ ገበያ የሚያቀርባቸውን የቡና፣ የቅባት እህሎችና የጥራጥሬ ምርቶች እንዲሁም የሚሰጣቸውን ተዛማጅ አገልግሎቶች በማስተዋወቅ ጠንካራ የገበያ ትስስርን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
