2 132
Підписники
-124 години
Немає даних7 днів
+3130 день
Архів дописів
2 133
በእጅህ ከትቢያ ቁንጣሪ ተሠራሁ፤ አንተም አሰማመርከኝ፤ ከአንተም በቀር አንዳች ተስፋ የለኝም! (አቤቱ ታስበኝ ዘንድ እኔ ምንድር ነኝ?!) መዝ. 8ን ሳሰላስል!
2 133
ብቻውን "ሐዋርያት ኾኖ የሚመካከር ሰው"። የታወቀ የነገረ መለኮት ኑ"ፋ'ቄ መምህርነቱ ሲደራለት፣ የፖለቲካ ኑ'ፋቄ'ውም አይቅርብኝ ያለ ይመስላል። ልብ ይመልስ ብለናል።
2 133
ለባህለ ትምህርት አልባ “ተሐድሶዎች”
ወንጌል የማይለወጥና ዘላለማዊ መልእክት ቢኖረውም፣ የራሱ ባህል ግን የለውም፤ ወንጌል ለየትኛውም ሕዝብ፤ ለኹሉም ነገዶች፤ በኹሉም ቋንቋዎችና ባህሎች መሰበክና መነገር ያለበት የእግዚአብሔር መንግሥት ታላቅ ምሥራች ነው። ለዚህ ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ዋና ምሳሌአችን ነው። ጌታችን ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለገሊላና ለይሁዳ መንደሮች ያቀረበበት መንገድ፣ እጅግ ጠቃሚ የኾኑ የባህል ተዛማጅ መመሪያዎችንና ልምምዶችን ያስተምረናል።
ጌታችን ኢየሱስ ከቅድስት ድንግል በመወለዱ፣ ፍጹም አይሁዳዊነቱን ይገልጣል፤ ምንም እንኳ በዘር ግንዶቹ ውስጥ ከአሕዛብ ወገን የኾኑት እነ ሩት፣ ቤርሳቤህና ረዓብ በመጠቀስ መሲሑ የመላለሙ ቤዛና መድኀኒት ቢኾንም፣ “የትውልድ ሐረጉ” ግን የሚመዘዘው ከቤተ እስራኤል፤ ከቀደመው ኪዳን ተቀባይ ሕዝብ ነው። በዚያ ባህል ውስጥ በጠባብ ደረት፤ በአጭር ቁመት ተወስኖ ተመላለሰ፤ እናም ጌታችን ኢየሱስ ሲሠራና መልእክቱን የእግዚአብሔርን መንግሥት አዋጅ ሲያውጅ የምንመለከተው በተወሰነ ባህል ውስጥ ነው። የምናገለግለውን ሕዝብ ባህል ለመረዳትና ለማክበር በመፈለግ ጉዳይ የጌታችን ኢየሱስን ተመሳሳይ ምሳሌ መከተል አለብን።
ከዚህም የተነሣ ኢየሱስ በዕብራይስጥና በአራማይክ ቋንቋዎች ተናግሮአል አስተምሮአል፤ በነዚህ ቋንቋዎች ከብዙ ሰዎች ጋር ተነጋግሮአል። የእርሻውን፣ የመክሊቱን፣ የእርሾውን፣ የዓሳ ማጥመድን፣ የድሪሙን፣ የዘርና የዘሪውን ምሳሌ ሲናገር ሰዎች በሚረዱትና በሚገባቸው ቋንቋ ተናግሮአል። ስለ ሠርግ በሕዝቡ ባህል ምሳሌነት ተናግሮአል፤ እንደ ባህላቸው በሠርግና በልቅሶ ቦታ ተገኝቶአል።
ጌታችን ኢየሱስ፣ ሳምራዊቷን ሴት ሕይወቷን እንድታስተካክል ሲመክራትና ሲወቅሳት ወይም የአይሁድ አለቃ የነበረው ኒቆዲሞስ ከርሱ ጋር ከመነጋገሩ በፊት ከሳንሄድሪን ሸንጎ እንዲወጣ አልጠየቀም። በዚያው ባሉበት የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል በፍቅር መሠከረላቸው። እኛም ኹሉንም ባሉበትና በባህላቸው መናገሩን ልንዘነጋ አይገባም።
ይህ እውነት ግን ዘወትር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ላይቀጥል ይችላል፤ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አንዳንድ አረሞች ሊበቅሉ ይችላሉ፤ ልክ በሐዋርያት ሥራ 15 እንደ ተነገረው አይነት። አስቀድሞ ክርስትና በእስራኤል እና በአይሁድ እምነትና ባህል ውስጥ ተወለደ። አንዳንድ አይሁዳውያን ክርስቲያኖች ሙሉ በሙሉ ክርስቲያን ከመኾናቸው በፊት ከሌላ ባሕሎች የመጡ አዳዲስ አማኞች ወደ አይሁድ ሃይማኖትና ባህል እንዲቀየሩ በግልጥ ጠየቁ። ክርስትና የመላለሙ መኾኑ ተዘነጋና፣ የአንድ ወገንና የአንድ ሕዝብ ባህል ተከታይ ብቻ እንዲኾኑ ተፈለገ። ይህ ግን ፍጹም ስህተት እንደ ነበር በሳልና ተወዳጅ ከነበረው ከሐዋርያት ውሳኔ በሚገባ እንረዳለን።
[አይሁዳዊው]ቅዱስ ጳውሎስ አይሁዳዊ ያልሆኑ አማኞችን ወክሎ፣ መዳን የሚገኘውና የሚጠበቀው በክርስቶስ ጸጋ በማመንና በመታዘዝ እንጂ የአይሁድን ሕግና ባህል በመከተል አይደለም ብሎ ተናገረ፤ የሐዋርያት ጉባኤ በዚህ እውነት ተስማማ። “ለጣዖት ከተሠዋ፥ ከደምም፥ ከታነቀም፥ ከዝሙትም ትርቁ ዘንድ ከዚህ ከሚያስፈልገው በቀር ሌላ ሸክም እንዳንጭንባችሁ እኛና መንፈስ ቅዱስ ፈቅደናልና፤ ከዚህም ሁሉ ራሳችሁን ብትጠብቁ በመልካም ትኖራላችሁ። ጤና ይስጣችሁ።” (ሐ.ሥ. 15፥28-29) በማለት። ከዚህ የተነሳ ማንም ሰው የኢየሱስ ክርስቶስ ተከታይ ለመኾን የአይሁድን ባሕላዊ ቅርጽ መከተል የለበትም የሚለው አቋም እስከ ገላትያና ሌሎችም አብያተ ክርስቲያናት ዘለቀ። በዚያ ታሪካዊ “አጋጣሚ” ወንጌሉ ወደ ኹሉም ባህሎች እንዲተረጐምና፣ እኔ እና እናንተ ባህላችንን “ሳንቀይር” ክርስቲያኖች እንድንኾን የባህላዊ አግባብነት መርህ ተዘረጋልን።
ዛሬ ላይ ግን ይህን መርሕ የማይከተሉ የወንጌል አገልጋይ ነን በዝተዋል፤ “ኦርቶዶክሳዊ ተሐድሶ” ነን የሚሉ ግን አንዳችም “ርቱዕ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርትና ልምምድ” የሌላቸው፤ ነጠላና ቀሚስ መልበስ፤ ካባና ላንቃ መጐናጸፍ፤ ጥምጣም መጠምጠምና ከበሮ ማንገት ብቻ ኦርቶዶክሳዊነት የሚመስላቸው ጥቂት አይደሉም፤ እንዲያው ወንጌል ተረድተው እዚያው ሌሎችን እንዲደርሱ ከመርዳት ማስኮብለል ጽድቅ፤ ከዚያ ማውጣት ታላቅ መንፈሳዊነት የሚመስላቸው “አጀብ ወዳዶች” ቤት ይቊጠራቸው።
እኔ ሐዳሲ ነኝ፤ ልኹንና የሕዝቤን ባህለ ትምህርት አስቀድሜ ለማወቅ ጥራለኹ፤ አለባበሱን፣ አመጋገቡን፣ አለቃቀሱን፣ ሠርግ አደጋገሱን፤ የኑሮ ዘይቤውን እረዳለታለሁ፤ በዚያው በሚኖረው ባህል ውስጥ ንፁሑን፤ ርቱዑን፤ በየትኛውም ባህል ውስጥ አልፎ አሸናፊውና ድል ነሺውን፤ ኀጢአትን የሚጠየፈውንና ከኀጢአት እስራት ነጻ የሚያወጣውን የድል ነሺውን የክርስቶስን ወንጌል እሰብከዋለሁ፤ እነግረዋለሁ። የቱም ቋንቋ፤ የትኛውም የአኗኗር ዘይቤ፤ ማናቸውም ባህል ወንጌል ለመስበክ ደንቃራ፤ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለማስፋት አሰናካይ አይኾንም።
እናም እባካችሁ፤ ሐዳሲ ነን ካልን የኢየሱስንና የደቀ መዛሙርት ሐዋርያትን ፈለግ እንከተል፤ ኦርቶዶክሳውያንን “በመጥላትና በማጥላላት፤ በማጣጣልም” ወንጌል አንድረስ። ባህለ ትምህርት አልባ ሐዳሲ ከመኾን፤ ባህለ ትምህርት የጠነቀቅን “የኹሉ ወገንተኛ፤ ለክርስቶስ ወንጌል በእውነት ቀናተኛ እንኹን”፤ ቅዱስ ጳውሎስ፣ “ክርስቶስ ኢየሱስን ጌታ እንደ ሆነ እንጂ ራሳችንን አንሰብክምና፥ ስለ ኢየሱስም ራሳችንን ለእናንተ ባሪያዎች እናደርጋለን።” እንዲል።
My blog link - https://abenezerteklu.blogspot.com/2026/07/blog-post_17.html
2 133
የኢየሱስ ደም ንጹሕና ኃያል ነው፤ የቱንም ኀጢአት ያጠራል፤ የቱንም የኀጢአትን፣ የሞትንና የዲያብሎስን ጉልበት ወይም ኀይል ይሽራል። ኃያል ሆይ፤ ተባረክ፤ አሜን።
2 133
ፈዋሹ ሐኪም ክርስቶስ ኢየሱስ፤ እነሆ ዛሬም ከነቁስል ምልክቱ አለ፤ እኛን ለዘላለም ስለ መውደዱ ፍቅሩን ያሳይ ዘንድ፤ ጌታ ሆይ፤ ተባረክ፤ ተወደስ፤ ከፍ ከፍ በል! አሜን፡፡
2 133
በአርጀንቲና የመጨረሻው የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ላይ፣ አንድ ደጋፊ መጽሐፍ ቅዱስን ከሕዝቡ በላይ ከፍ አድርጎ አሳይቷል።
በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ባንዲራዎችን ሲያውለበልቡ፣ ይህ ደጋፊ ግን የእግዚአብሔርን ቃል ለማውለብለብ መረጠ።
የእግር ኳስ ውድድሮች ይመጣሉ፤ ያልፋሉ። ሻምፒዮኖች ይቀያየራሉ። የስፖርት ህይወት ያበቃል፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል የማይለወጥ፣ ሕያው እና እውነት ሆኖ ይኖራል።
Source - Ballers in God
2 133
የሚቀድሰውን ቅዳሴ መልእክቱንና ዋናውን ነገር የማያውቅ ከኾነ፣ አገልግሎቱ ነፋስን እንደ መጎሰም አይደለም ወይ?! ታድያ መልእክቱ ነው ዋናውና ተሐድሶም፤ አሕይዎም ያሻል ስንል ለምን ቅር ይላችኋል?!
የቴሌግራም አድራሻ -
2 133
ስለ መጋቢ ሐዲስ ለኦርቶዶክስ "በቀናተኝነት" በተደጋጋሚ የሚናገሩት ዶክተር አረጋ እንዲህ አሉ፦
"...በነገራችን ላይ መጋቤ ሐዲስ ተናጋሪ ወይም ኦራተር የሚባሉ እንጂ ጥንቁቅ ሰባኪ አይደሉም፡፡ በሰበኩ ቁጥር ነጥብ እንደጣሉ ነው፡፡ በስብከት ዘዴ ስንመዝናቸው፣ ነገረ ዘርቅ የሚያበዙ፣ ቧልትና ቀልድ የሚያዘወትሩ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ለፖለቲካውም ለግብርናውም፣ ለአርቲስቱም እንደልባቸው በመተርጎምና የሰውን ህሊና ለመያዝ በሚደረግ ጥረት በርካታ ነጥቦችን በማዝረክረክ የሚታወቁ ናቸው፡፡..."
ከዓመታት በፊት ይህን ስንናገር ግን ማንም አላስተዋለም ነበር።
የቴሌግራም አድራሻ - https://telegram.me/ebenezertek
2 133
የዋልድባ የግድያና የዘረኝነቱ ጦስ!
“... በኹለት ዐመቱ ጌታችን በእናቱ እቅፍ መጥቶ ባረካት[ዋልድባን]። ዋልድባ በአራቱ ወንዞች ትከበብ ብሎ፣ የሰው ብቻ ሳይኾን የእንሰሳ ሴት አይግባባት ብሎ ጌታችን ኢየሱስ የውግዘት ቃል አሳልፎባታል። ሴቶች እንዳይገቡ በግዝት ቃል ተነግሮባታል። ... ስውር ቅዱሳን ክንድ ከስንዝር ከፍ ብለው የቀደሱበት ስፍራ ነው።... ዳልሻ ዋልድባ ቤተ ደናግል የሚባል የሴቶች ገዳም ጨርሶ የለም። ... ገዳሙ ጨርሶ የእርሻ ስፍራ እንዳይኾን እንኳ ተከልክሎአል።... በዋልድባ ጳጳስ እንኳ ቢመጣ 40 ቀን ቋርፍ ሳይጨብጥ በዋልድባ ቀጥታ መቁረብ አይቻልም።…” የሚሉ አያሌ “ተረቶች” በገዳሙ “አባቶች” ሲነገር መደመጡ እንግዳ ነገር አይደለም።
ከዚህም በተጨማሪ፣ “በገዳሙ ስውራን ቅዱሳን አሉ፤ ያልተገባ ተግባር ሲፈጸም ይቀስፋሉ።” ቢሉም በነርሱ ሚዛን፣ እሸቱ መለሰ የተባለ “ኮሜዲያን” በገዳሙ ያልተገባ ተግባር ሲፈጽም ግን አልተቀሰፈም። ያ ብቻ ሳይኾን ሊገደል እንደሚችል፣ ሀብቱን የማጣት ዕጣ እንደሚወጣበትም መነኮሳቱ በድፍረት ተናግረዋል። ከዚህ በዘለለ በዘረኝነት፣ በግድያ፣ የሌሎችን በዐት በማፍረስ የተካኑ መነኮሳት ያለበት ገዳም እንደ ኾነ እዚያው ዋልድባ አከባቢ ያሉ የቤተ ጣዕማ መነኮሳት ምስክርነት ሰጥተዋል።
የግል መደምደሚያዬ!
ገዳሙ “ከስሙ” በተቃራኒ የቆመ ነው። “ጻድቃን ስውራን” የሚል ንግግር በተደጋጋሚ ይነገራል፤ እውነታ ግን “ስውራን” የተባሉ ጨርሶ አለመኖራቸውን ምክንያቶቼን ከዚህ በታች ላስረዳ፣
1. “ኹለት አበምኔት በአንድ ገዳም አለ፤ ይህም የኾነው ፍቅረ ንዋይ ስለሚያጣላን ነው” ይላሉ የገዳሙ መነኮሳት። እውን ስውራን ቢኖሩበት ይህን ማስተካከል እንዴት ተሳናቸው?!
2. አንዳንዶቹ የሴቶች ገዳም አለ ሲሉ፣ ሌሎቹ ግን ዋልድባ ሴት የምትባል የእንሰሳም የሰውም ፍጥረት አይገባባትም ይላሉ። እውን የሴት ፍጥረት ሰውና እንሰሳ ብቻ ነውን? የዛፍ የአትክልት፣ የአዝርእት፣ የአእዋፋት፣ የጥቃቅን ነፍሳት … “ሴቶች” የሉምን? እኒህ ሁሉ በዋልድባ የማይገቡ ኾነው ነው? ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ ያነጋገራቸው “ሴት መነኮሳት” ለምን “ዋልድባውያን” አይደሉም ተባለ?
3. “አንዱ ሌላውን “መናፍቃ.ን” ናቸው እያሉ በሐሰት ይከስሳሉ። ከዚህም በላይ ጁንታ[የዳንኤል ክብረት ስያሜ የተባለለት] ናቸው፤ ኹሉም ትግራይ እንጂ በመካከላቸው አማራ የለም ይሉናል።” ይላሉ የቤተ ጣዕማ መነኮሳት፣ የቤተ ሚናስ መነኮሳትን ሲወቅሱ። ይህን ያህል ዘረኝነት በስውራን መካከል እንዴት ገነነ?!
4. “የቤተ ሚናስ መነኮሳት ገዳማችንን በእሳት አቃጠሉብን፤ የምናመልክበትን ሕንጻ ቤተክርስቲያን አቃጠሉብን፣ መነኮሳቱ የቤተክርስቲያንን ብራናና ንብረታችንን ዘረፉ፣ በቤንዚን አርከፍክፈው ቤተክርስቲያናችንን አቃጠሉት፣ በክላሽና በዱላ አሳደዱን።” ይላሉ የቤተ ጣዕማ መነኮሳት። ይህ እጅግ አሳፋሪ ተግባር አይደለም ወይ?! ዋልድባ መካከል እንዲህ ያሉ መነኮሳት ካሉ፣ “ዓለማዊነት” በከፋ ኹኔታ በገዳም የገነነ አይደለም ወይ?
እነ እንጦንስ ቤተክርስቲያን ከመንግሥት ጋር ስትጣበቅ፣ ከቤተክርስቲያን ወደ ገዳም ሸሹ፤ የቤተ ክርስቲያንንና የመንግሥትን ጋብቻ በዓይናቸው ላለማየትና እነርሱም አብረው እንዳይረክሱ በመጠንቀቅ። በዋልድባ ገዳም ያሉ መነኮሳት ግን የሚሸሹ[ሊርቁአቸው የሚገባ] እንጂ የሚሸሽባቸው አይደሉም። ምክንያቱም የቤተ ጣዕማ መነኮሳት እንደሚናገሩት በዘረኝነት ሌላውን ያጠቃሉ፣ በሐሰት ክስ የሌላውን ስም ያጠለሻሉ ብሎም በፍቅረ ነዋይ ዓይናቸው የታወረ ነው። እንዲህ ያለ ርኩሰት “መልካም ስብዕና ባላቸው ዓለማውያን ወይም አሕዛብ” መካከል እንኳ ጨርሶ የማይሰማ ነው።
ሰው በገዳም ተቀምጦ እንጥፍጣፊ ርኅራኄ፤ ዘለላ ቸርነት ከሌለው፣ በገዳም ከሚኖረው ይልቅ “ወንጌል ገና ያልሰማውና ጌታን ጨርሶ የማያውቀው የተሻለ ተስፋና የመዳን አለኝታ” አለው። ከከፋ “አማኝ”፤ የከፋ ኢአማኒ የተሻለ የንስሐ ዕድል አለውና። ለዚህም ነው በተደጋጋሚ፣ በገዳማት በከንቱ መመካት አይገባም ስንል የነበረው። በገዳም ጽድቅ ብቻ እንዳለ የሚነገረውም “ተቃርኖ እንዳለበት” ዋልድባ ድንቅ ምሳሌ ነው። የክርስቶስን ጽድቅ ሽሮ፣ የራስን ጽድቅ ለማቆም መጣር ፍጻሜው እንዲህ ያለ አስቀያሚ ርኩሰት ነው!
ይህ ብቻ ያይደለ፣ ከሰሞኑ “መነኮሳት ወደ ገዳም ይግቡ” የሚለውም ክርክርና ቅስቀሳ፣ በሚገባ ቢጤን የተሻለ ነው፤ “በገዳም ምን አለ?” ብሎ መጠየቅ ተገቢ ጥያቄ ይመስለኛል። ሰው ለመግደል፤ በዘረኝነት ለማበር፤ ከዓለማዊነት ባልተሻለ ማንነት ለመመላለስ፣ የክርስቶስን ጽድቅ ነቅፎ የራስን ጽድቅ ለማቆም ከኾነ፣ ገዳማዊነት ቢቀርና አግብተው እንበለ በዓት በጽድቅ የሚመላለሱ ባለትዳሮች እጅግ የተሻሉ መኾናቸውን ልንመሰክርላቸው ይገባናል! ክርስቶስ የሌለበት ገዳም ከአውሬነት ይልቅ ይከፋል፤ ክርስቶስ ያለበት ትዳር ደግሞ ከገዳማዊነት ጋር ጨርሶ ሊወዳደር አይገባውም፤ ይበልጣልና!
አቤቱ ወደ እኛ ተመለስ፤ ትውልዱ ወዳንተ ይመለስ ዘንድ፤ አሜን።
My blog link - http://abenezerteklu.blogspot.com/2026/07/blog-post.html
2 133
ታንኳ መረብ ዓሳ የደቀመዛሙርቱን ልብ ብዙ ጊዜ ፈትኖአል፤ መንፈስ ቅዱስ ሲመጣ ግን "ያለን ኢየሱስ ነው" ብለዋል፤ እናም ዓሳ አጓጉቷቸው በተመለሱ አትደነቁ!
2 133
ዋልድባ ምኑ ነው መንፈሳዊነቱ?!
እነእሸቱ መለሰ የሠሩትን የዋልድባን ገዳም ጉዳይ ተመለከትኹ። ልቤ እጅግ በጣም ነው ያዘነው። በገዳሙ ያሉ እህቶች ስለ ገዳሙ የሚናገሩት ኹሉ ከልብ አሳዛኝ ነው። ከንግግሮቻቸው መካከል ለአብነት እኒህን ወስጃለኹ።
" ... ዋልድባ ፈውስ አገኝበታለኹ ተብሎ የሚመጣበት ቦታ አይደለም። ደዌ ተቀብዬ መከራ ተቀብዬ ክብር አገኝበታለኹ የሚባልበት ቦታ ነው። ..."
"... የሚመጡ እናቶች የሞት ቦታ ነው ብለው ሰሌን ይዘው ይመጣሉ። ... በተለይ ሰው በክረምት በብዛት ይሞታል። ... እኛ በዚህ የሰው ሞት አያስለቅሰንም የዋልድባን አፈር ካገኘ ብለን ደስ ይለናል እንጂ ዕድለኛም ነው። ..."
" ...የዋልድባ ቋርፍ መንፈስ ቅዱስ ያሳድራል፤ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ያደርጋል። ከዓለም የተለየ ምግብ ነውና። ... የነፍስም መድኃኒት ነውና ..."
"በዋልድባ 44 ዓይነት በሽታ አለ። ከ44ቱ በአንዱ የሞተ ክብር አለው። ለዚህም ነው እንሙት እንታመም ፤ አንታከምም የሚሉ አሉ። ጸጋ ስለኾነ። ..."
ይህ እንግዲህ በዚያው በገዳሙ የሚኖሩ መነኮሳዪያት እህቶች የተናገሩት ነው። ሰው ጽድቅን አገኛለኹ ብሎ በዚህ ልክ መንከራተቱና የክርስቶስን ጽድቅ ነቅፎ የራሱን ጽድቅ ለማቆም በዚህ ልክ ዋጋ መክፈሉ ከልብ ያሳዝናል። ገዳሙን በጣም መንፈሳዊ ለማድረግ "የመሠረተው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" ይላሉ። ጌታችን ኢየሱስ እንዲህ ያለ መከራና ሰቆቃ በሰዎች ላይ እንዲደርስ አይፈቅድምና፣ ይህ ፍጹም ሐሰትና ፈጽሞ ከእውነት የራቀ ነው።
እንዲያውም ጌታችን ኢየሱስ፣ "እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።
ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤
ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና።" (ማቴ. 11፥28-30) አለ እንጂ የጭንቅና የጣር፤ የደዌና የሞትን መንገድ እንድንከተል አላስተማረንም። ርሱ ለደካሞችና ለሕሙማን የሚራራ መሃሪ ነውና!
እና እንዴት በዚህ ልክ በሽታና ሞት፤ ስቅየትና ጣዕር ክብር ነው ተብሎ ይነገራል?! ይህ በየትኛው የክርስትና አስተምኅሮ የተደገፈ ነው? ክርስትና፣ በገዛ ጥበብና በሰው ሥርዓት የሚደረጉትን ተግባራት የሚጠየፍና በተለይም " ...እነዚህ ነገሮች በገዛ ራስ ላይ ከሚፈጥሩት የአምልኮ ስሜት፣ ከዐጕል ትሕትናና ሰውነትን ከመጨቈን አንጻር በርግጥ ጥበብ ያለባቸው ይመስላሉ፤ ነገር ግን የሥጋን ልቅነት ለመቈጣጠር አንዳች ፋይዳ የላቸውም።" (ቆላ. 2፥24) በማለት ሰዋዊ የጽድቅ መንገዶች ዕርባና ቢስ መኾናቸውን የሚያስተምር የጽድቅ እምነት ነው።
ጽድቅ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በከፈለው ሥራ ለኀጢአተኛው ዓለም ፈጽሞ ተከፍሎአል፤ ተደምድሞአልም። ከሰው የሚጠበቀው በዚህ በተሠራው የጽድቅ ሥራ ማመንና መጽናት ነው፤ በዚህም የዘላለም ሕይወት አለ። መጽሐፍ፣ "ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንዲጸድቅ እንጂ በሕግ ሥራ እንዳይሆን አውቀን፥ ሥጋን የለበሰ ሁሉ በሕግ ሥራ ስለማይጸድቅ፥ እኛ ራሳችን በሕግ ሥራ ሳይሆን በክርስቶስ እምነት እንጸድቅ ዘንድ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል።" (ገላ. 2፥16) ይላል። ሰዎች እንዲጸድቁና እንዲድኑ፤ የነፍስ መድኃኒትም ይኾናቸው ዘንድ እነሆ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ኹሉ ሞቶአል።
በዋልድባና በሌሎችም አያሌ ገዳማት ከዚህ ተቃራኒ የኾነ ትምህርትና ልምምድ አለ። ተሐድሶ ስንል ይኸንኑ መራራ ይነቀልና፣ የክርስቶስ አማናዊ ጽድቅ በሰዎች ኹሉ ልብ ይናኝ ዘንድ ነው።
2 133
8% ብቻ ነው የዘንድሮን ማትሪክ ያለፈው ብሎ አንድ ሰው በቁጭት ፓርላማ ላይ ሲናገር፣ መላው ፓርላማ ይስቃል፤ የጉድ አገር። እኛ'ኮ ኃላፊነት የማይሰማን ኋላቀር ብቻ አይደለንም። ከኋላ ቀሮችም የኋላ ቀር ነን።
2 133
"መቶ በመቶ ተሳስቻለሁ!"
'' ... ስለ ሥላሴ ጾታ መናገሬ መቶ በመቶ ስሕተት ነው፡፡ አርባ ዓመት የደከምኹበትን ትምህርት አበላሽቸዋለሁ። ይኸ ለምእመናንም፣ ለሊቃውንትም የእኔ ዳሕጸ ልሳን መኾኑ ይታወቅልኝ፡፡ ኹሉንም በማሳሳቴም ይቅርታ እጠይቃለሁ። እኔ አድጦኝ የፈጸምኩት ስሕተት እንጂ የቤተ ክርስቲያኗ ትምህርት አይደለም።"
ቀጥለውም፦ " ... ሰው አይሳሳትም፣ ጳጳስ አይሳሳትም አይባልም። የማይሳሳት እግዚአብሔር ብቻ ነው።" ላላቸውም ጠያቂ መልስ ሲሰጡ፦ "... እኔ ሩቅ ብዕሲው እንዴት ነው የማልሳሳተው? ... ለሥላሴ ጾታ በመናገሬ መቶ በመቶ ተሳስቻለሁ።" ብለው ጥፋታቸውን ፍጹም አምነዋል።
ለኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን እንዲህ ያለ ስህተትን በ"ሊቃውንት" ደረጃ ማመን ይበል የሚያሰኝ ነው። ከዚህ ቀደም እምብዛም ያልነበረ፣ ይበል የሚያሰኝ ተግባር ነው። "ቤተክርስቲያን አትሳሳትም" የሚለው የቤተክርስቲያኒቱ ጥብቅ መርኅ፣ ቤተክርስቲያኒቱ እንዲህ ሊሳሳቱ የሚችሉ "ሊቃውንት ያሉባት ስብስብ" መኾንዋን ማስታወስ እንወዳለን።
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እንዲህ በአደባባይ ተሳስቻለኹ ልትላቸው የሚገባ "ግሳንግስ" አለ። ትውልድን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንዲፈልስ ለማድረግ፣ በክርስቶስ ኢየሱስ የመስቀል ሥራ ላይ የተደረገው ነቀፋ በአደባባያዊ ይቅርታና የተበላሸውን በማደስ ማስተካከያ ሊደረግባቸው ይገባል። ይህ ሲኾን ትውልድ ማዳን፤ መንግሥቱን ማስፋቱን ይቻላል።
"ሊቁ ሆይ"፤ የግል ክብርን አሸንፈው ይቅርታ ለጠየቁበት ቅንነትዎ አክብሮት አለን።
2 133
+3
ጌታ ኢየሱስ በወንድሞችና በእህቶች ስለሚሠራው ሥራ፣ እግዚአብሔርን እጅግ አድርጌ አመሰግናለው። አኀው የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከጌታ መንፈስ ቅዱስ ጋር ለኦርቶዶክሳዊ ተሐድሶ ትተጋለች።
የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek
2 133
መነኮሳት ለምን ወደ "ሚሽነሪ" አይላኩም?
"ምንኩስና በገዳም መወሰን ነው" የሚል የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቀኖና አለ፤ ዓላማውም ለጸሎትና ለትህርምት። በግሌ በገዳም መወሰን አሉታዊ ተጽዕኖው ቀላል አይደለም። ዋና ዐሳቤ ርሱ አይደለም።
ዳሩ ግን ምንኩስና በገዳም ከመወሰን ይልቅ፣ በዙሪያችን ባሉ አገራት[ሶማሊያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን ...] ወንጌል ወደ ማድረስ "የጌታ ኢየሱስ ተልእኮ ወይም ሐዋርያዊ ተልእኮ" ለምን አይላኩም?! ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን "ምንኩስናን በኩራት" የምትናገረውን ያህል፣ ወንጌል ለኢትዮጵያ ላልደረሳቸውና ለጎረቤት አገሮች ብሎም ለአፍሪካውያንና ለተቀረው ዓለም የማትልክበት ነገሯ በተደጋጋሚ ይደንቀኛል።
ኢትዮጵያ ክርስትናን በቀደምትነት የተቀበለች ብትኾንም፣ ለሌሎች ወንጌልን ባለማድረስ ግን "ከፍ ያለ ተጠያቂነት" አለባት ብዬ አምናለኹ። ወደ ገዳም ይግቡ ከማለት፣ በቂ ዝግጅት አድርገው ለተልዕኮ ቢላኩ ባይ ነኝ።
ለምግባር ውድቀት መንስኤው የቅዱስ ወንጌል ትምህርትና የልምምድ ችግር እንጂ፣ ወደ ገዳም "የመግባትና ያለ መግባት" ችግር አይደለም። ከኹሉ በላይ በቂ ዝግጅት አድርጎ የሚሻለውን ማድረግ ሲገባ "ወደ ገዳም" ይመለሱ ብቻውን መፍትሔ ሊኾን አይችልም።
ሐዋርያዊ ተልእኮ ቀዳሚም፤ ግዴታዊ ትእዛዝም ነው።
