fa
Feedback
የዲያቆን አቤንኤዘር ተክሉ ገጽ

የዲያቆን አቤንኤዘር ተክሉ ገጽ

رفتن به کانال در Telegram
2 104
مشترکین
-124 ساعت
+17 روز
-3830 روز
آرشیو پست ها
ለታመሙና እጅግ ኀጢአተኞች ለኾኑ ክርስቶስ የበዛ ሀብትና ጸጋ አለው።

ፌስቲቫል? በባህል እንኳ ጎረቤትህ ሰው ሲሞት፣ ቲቪና ሬዲዮ ትዘጋለህ። ጎረቤትነት እንኳ እንዲህ ይርከስ?! መንፈሳዊነቱ ይቅር ስብዕናና ሞራሉ እንዴት ነጠፈብን? የአርሲ ምድር ደ'ም ገና አልደረቀም'
ፌስቲቫል? በባህል እንኳ ጎረቤትህ ሰው ሲሞት፣ ቲቪና ሬዲዮ ትዘጋለህ። ጎረቤትነት እንኳ እንዲህ ይርከስ?! መንፈሳዊነቱ ይቅር ስብዕናና ሞራሉ እንዴት ነጠፈብን? የአርሲ ምድር ደ'ም ገና አልደረቀም'ኮ!

ጳውሎስ የሰማው የሞት ድምጽ! (2ቆሮ. 1፥9-11) ቅዱስ ጳውሎስ ኹለተኛውን ቆሮንቶስ እየጻፈ ያለው፣ በአንደኛ መልእክቱ ላይ በታላቅ ተግሳጽ የገሰጻቸውንና ንስሐም በመግባት የንስሐ ፍሬ ያሳዩትን ቅዱሳን ወገኖቹን ለማጽናናትና ለማበረታታት ነው። አንደኛውን መልእክት ሲዘጋ፣ የወንጌል ሥራ በር እንደ ተከፈተለትና ነገር ግን የዚያኑ ያህል ደግሞ እጅግ ተቃዋሚዎች እንደ ተነሱም ተናግሮአል (1ቆሮ. 16፥8-9)፤ ምናልባት ተቃዋሚዎቹ ከባድ ስደት አልያም ከፍ ያለ እንግልት አድርሰው ሊኾን ይችላል። ይኹንና የደረሰባቸው መከራ ለሞት ጭምር ሊያጋልጣቸው እንደሚችልና የሚሞቱም እንደ መሰላቸው ይናገራል። የኹኔታውን ክብደት ሐዋርያው ሲናገር፣ “እኛ ራሳችን የሞትን ፍርድ በውስጣችን ሰምተን ነበር።” ብሎአል።ሁኔታው በጣም አስጨናቂ ስለነበር ጳውሎስና ጓደኞቹ በሕይወት የመቆየት ችሎታቸው ላይ ሙሉ በሙሉ “ተስፋ ቈርጠዋል”። ይህ ማለት ሙታንን በሚያስነሣው አምላክ እንዲታመኑ ተገደዱ። አቅመ ደካሞች ነበሩ እናም ሁሉንም ተስፋቸውን በእግዚአብሔር ላይ እንዲያደርጉ እንኳን ተገደዱ። መከራ በማንኛውም አማኝ ላይ ተመሳሳይ የኾነ ስሜትን ይፈጥራል። በሐሰት የምንጠብቀውን ማንኛውንም ነገር አስወግዶ ሙሉ ተስፋችንን በምንታመንበት ኃያል አምላክ ላይ እንድናሳርፍ ያደርጋል። አኹንም፣ ጳውሎስ መከራውን ከኢየሱስ መከራ ጋር አገናኘው። ኢየሱስ የሞት ፍርድ የተቀበለው ከሮማውያን ሲኾን፣ ጥላቻንና፣ ንቀትንና ስድብን ገድሞ የተገበው ከገዛ ወገኖቹ አይሁድና የሃይማኖት መሪዎች ነው። ጌታችን ግን በዚህ ኹሉ መከራ ውስጥ፣ “በስጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥” ደግሞም፣ “ከተቀበለው መከራ መታዘዝን ተማረ፤” (ዕብ. 5፥7፡ 8)፤ አሜን። የዳነ አማኝ ዘወትር ባለማቋረጥ ወዳዳነው ጌታ መቅረብ አለበት፤ አምነን የመዳናችን ትልቁ ግብ ወደ ጌታ ፍጹም መጠጋትና በርሱ ጥላ ሥር መከለል ነውና። ቅዱስ ጳውሎስ፣ “… ሙታንን በሚያነሣ በእግዚአብሔር እንጂ በራሳችን እንዳንታመን፥ እርሱም ይህን ከሚያህል ሞት አዳነን፥ ያድነንማል፤” (2ቆሮ. 1፥9-11) አለ። አሜን ዛሬም ከዘላለም ሞት የዳንን እኛ፣ በዙሪያችን ካለው ከብርቱ ሞት ድምጽ ያድነናል፤ ይታደገንማል። My telegram link - https://t.me/ebenezertek My blog link - https://abenezerteklu.blogspot.com/2026/06/2-19-11.html

ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ስለ አርሲው ጭ'ፍጨፋ ስልክ አያነሱም ወይም መረጃ የለንም ይሉሃል፤ በቁም ስትናቅና ስትተው፤ ምንም አታመጣም ሲሉህ፣ ለወገኔ ግን እላለኹ፣ እግዚአብሔር አለ!

“ቅዱስና እውነተኛ፥ ልዑል እግዚአብሔር ሆይ፥ በምድር ባሉት ሰዎች ላይ የማትፈርደውና ስለ ደማችንም የማትበቀለው እስከ መቼ ነው!” (ራእ. 6፥10 ዐት)

የወገን ቅጥቃጤ ዛሬ ካልተሰማን፣ ነገ የእያንዳንዳችንን ቤት ላለማቁሰላቸው ዋስትና የለንም! በርግጥ "ባገርህ እንደ መጤ ስትቆጠር ብርቱ" ጥዝጣዜ ይፈጥራል!
የወገን ቅጥቃጤ ዛሬ ካልተሰማን፣ ነገ የእያንዳንዳችንን ቤት ላለማቁሰላቸው ዋስትና የለንም! በርግጥ "ባገርህ እንደ መጤ ስትቆጠር ብርቱ" ጥዝጣዜ ይፈጥራል!

የአርሲ ሰ'ቆቃን ችላ ማስባያ ወይስ ከልክ ያለፈ ፍቅረ ነዋይ?! እናንተ ለገዛ ልጆቻችሁ ይህን ያህል ደንታ ከሌላችሁ ሌላው ምን ይባላል?! የምትሰበስቡት ድንጋይ በድንጋይ ላይ ለመካብ አይደለምን?!
የአርሲ ሰ'ቆቃን ችላ ማስባያ ወይስ ከልክ ያለፈ ፍቅረ ነዋይ?! እናንተ ለገዛ ልጆቻችሁ ይህን ያህል ደንታ ከሌላችሁ ሌላው ምን ይባላል?! የምትሰበስቡት ድንጋይ በድንጋይ ላይ ለመካብ አይደለምን?! የሚሞ'ተውና የሚጨ'ፈጨፈው ግን የሥላሴ አምሳል ነው። ለመንጋው አትራሩምን?! ይህን ስታደርጉስ  አይሰቀጥጣችሁምን?! እግዚአብሔር ልብ ይስጣችኹ፤ ከጥበብ አትንጠፉ። "... በሕዝቤ ላይ በደረሰው ጥፋት ምክንያት እንባ ከዐይኖቼ እንደ ወንዝ ውሃ ይጐርፋል።  “እንባዬ ያለማቋረጥ ይፈስሳል።  ይህም የሚሆነው እግዚአብሔር ከሰማይ ወደ ታች ተመልክቶ እስኪያይ ድረስ ነው።" (ሰቈ. 3፥48-50 ዐት)

“የምንኖረውና የምንንቀሳቀሰው፣ ያለነውም በእርሱ[በእግዚአብሔር] ነውና።’” (ሐዋ. 17፥28)

"...ይህ መከራ እያበቃ ሳይኾን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደህንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድቤተክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን። ..." አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ

የአርሲውን የኦርቶዶክሳውያን ግድያ የወረዳው አስተዳዳሪ "መረጃው የለኝም" ይላል፤ የጉድ ሙዳይ፣ ለነገሩ ከርሱ በላይ ያሉትም "መረጃው የላቸውምና ወጥተው አይናገሩለትም!" ይህን ያህል የምትጠሉትን ሕዝብ "አንመራህም ማለት ይቀላል እኮ"! ሟች ሄዶአል፤ በኛ በቆምነው ግን ይዘብታሉ፤ ተስፋችንን ለማጨለም ይተጋሉ፤ እግዚአብሔር ይገስጻችኹ!

የአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ጉዳይ ያምማል! በአርሲ ዞን በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመውን ተደጋጋሚ ግድያዎች ፍጹም ከሚቃወሙት መካከል ነኝ፤ ምናልባት ስልጡን መሪዎች ቢኖሩን፣ ይህን ተደጋጋሚ ግድያ ማስ
የአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ጉዳይ ያምማል! በአርሲ ዞን በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመውን ተደጋጋሚ ግድያዎች ፍጹም ከሚቃወሙት መካከል ነኝ፤ ምናልባት ስልጡን መሪዎች ቢኖሩን፣ ይህን ተደጋጋሚ ግድያ ማስቀረት ባለመቻላቸው ሥልጣን በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸውን እንሰማ ነበር፤ ግን አልታደልንም፡፡ መሪዎች ባሉባት ምድር በተደጋጋሚ ግድያዎች አሉ፣ በተመሳሳይ ኹኔታ፣ በተመሳሳይ መንገድ፣ በተመሳሳይ ስፍራ፣ በተመሳሳይ “የእምነት አቋም” ባላቸው ሕዝቦች ላይ …! ደም ግን ባለቤት አለው፤ ተራና ርካሽ አይደለም፤ ይዘገያል እንጂ እግዚአብሔር የግፉአንን ደም የተበቀለ ለታ “ምድር ሰንጥቃ ብትውጠው እንኳ” እፎይታ የለውም! መዘዙ በቀላሉ ይተወናል ብዬም አላምንም! የመንግሥት ተቀዳሚና ዋና ተግባር የገዛ ዜጎቹን ደህንነትና ሰብዓዊ ክብር መጠበቅና ማስጠበቅ ነው ብሎ ደጋግሞ ማስታወስ የሚገባ ይመስለኛል!

የመካነ ኢየሱስና የቃለ ሕይወት አብያተ ክርስቲያናት እያደረጉ ያሉት “ነገረ ሐዋርያትና ነቢያት" ላይ፣ በግሌ "እሰየው" ባይ ነኝ። በተለይ "ራስ አንጋሽና ቀቢ ነቢያትና ሐዋርያት" በገነኑበት፣ የቤተ
+1
የመካነ ኢየሱስና የቃለ ሕይወት አብያተ ክርስቲያናት እያደረጉ ያሉት “ነገረ ሐዋርያትና ነቢያት" ላይ፣ በግሌ "እሰየው" ባይ ነኝ። በተለይ "ራስ አንጋሽና ቀቢ ነቢያትና ሐዋርያት" በገነኑበት፣ የቤተ ክርስቲያንን ሥልጣንና ለቤተ ክርስቲያን መሰጠትን አሽቀንጥረው የጣሉ “የጐበዝ አለቆች” ሲፋንኑ፣ “ከየበረቱ” በጎችን በሚያ.ባብልና በሚያማልል ንግግር አጥ.ምደው እያስኮበለሉ ሸልተው ለልብሳቸው፤ አር.ደው ለምግባቸው ያለ አንዳች ሃፍረት ሲጠቀሙ… ጨክኖ በልዩነት እንዲህ ያለ አቋም መያዝ እጅግ የተገባ ነው። በርግጥ ረፍዷል፤ ብዙ በጎችና አማንያን "ከተበሉ በኋላ" ጨርሶ ከመቅረት ግን ይሻላል። በመግለጫው "የነሰራቸው አባ.ይ ነቢያትና ሐዋርያት" የሚይይዙትና የሚጨብጡት አሳጥቶአቸዋል። በተለይ "pause apostle ዘላለም ጌታቸው" ያስለፈልፈዋል አይገልጠውም፤ ነገሩ ጨክኖ ከቀጠለ፣ የእንጀራ ገመዱ[ገመዳቸው] ሊበ.ጠስ ነውና። 'ቢበጣጠስ' ደግሞ ደስ ከሚላቸው አንዱ ነኝ። እግዚአብሔር 'ለክፉዎች ሰላም እንደ ሌላቸው' በግልጥ ተናግሮም የለ?! እነአጋቦስ፣ ይሁዳና ሲላስ (ሐ.ሥ. 15፥32)፣ የኢየሩሳሌምና የአንጾኪያ ነቢያት (ሐ.ሥ. 10፥43፤ 13፥1) በጽድቅ ያገለገሉበት ታላቅ ስጦታ "ወፈ.ፌዎችና ዋ.ሾዎች" በስሙ መጠራታቸው ያሰቅቃል። እናም ኹለቱ አብያተ ክርስቲያናት ምንም እንኳ "የአስተሳሰብ እንከን" ቢኖርባቸውም፣ በሐሰ'ተኞች ላይ የወሰዱት እርምጃቸው ይበል ያሰኛል። ከቃሉ በላይ ነቢይ፤ የነቢያት ፍጻሜና መደምደሚያ ከኾነው ከመሲሑ ኢየሱስ የሚበልጥ ሌላ "ሊቀ ነቢያት" (ዘዳ. 18፥15፤ ማቴ. 13፥57፤ ዕብ. 1፥1-2) የለንም፤ አናውቅምም! የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek

በክርስቶስ ኢየሱስ የደም መፍሰስ ቤተክርስቲያን ተመሠረተች፤ በመንፈስ ቅዱስ ለቅዱሳን ሐዋርያት በመውረድ ደግሞ ተመርቃ ተከፈተች፤ አሜን።

የዳንነው፣ "ምን ዐይነት ጻድቃን ተገኙ?" ለመባል ሳይኾን፣ "ምን ዐይነት አጽዳቂ ተገኘ?" ይባል ዘንድ ነው፤ መጽሐፍ፣ "የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ" እንዲል።

እኛ በሰማያዊ ስፍራ እንጂ በአብ ቀኝ አልተቀመጥንም፤ በአብ ተቀመጠ የተባለለት ውድና አንድያ ልጁ ክርስቶስ ኢየሱ ብቻ ነው!

በየቀኑ መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብ፣ በየሳምንቱ በጉባኤና በማኅደራት ኅብረት ማድረግ፣ ደግሞም በዓላማና በአምልኮ መጾምን ዘወትር አትርሳ!

ዕጸ መስቀሉን በእጁ ብቻ ይዞ ከሚዞር ቄስ ይልቅ፣ በልቡ መከራ መስቀሉን ተሸክሞ የሚከተል ምዕመን እጅጉን ይሻላል!

ዶክተር ተስፋዬ ሮበሌን አለማክበር አይቻልም፤ እናከብርሃለን። ይቅርታ ራስን የመግዛትና የጎበዛዝት ልብ ውጤት ነውና፤ ተባረክ። እግረ መንገድ "ቤተክርስቲያንህ" ቃለ ሕይወትም እየወሰደች ባለው "ከካው
ዶክተር ተስፋዬ ሮበሌን አለማክበር አይቻልም፤ እናከብርሃለን። ይቅርታ ራስን የመግዛትና የጎበዛዝት ልብ ውጤት ነውና፤ ተባረክ። እግረ መንገድ "ቤተክርስቲያንህ" ቃለ ሕይወትም እየወሰደች ባለው "ከካውንስሉ ራስን የማግለል እርምጃም" ሳላደንቅ አላልፍም። በአንተና "በቤተክርስቲያንህ" ላይ የጻፍኹትን ጽሑፌንም አንስቻለኹ። ተትረፍርፋችኹ ተባረኩ። የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek

Yasuus koo - iddoo waan hundaa naaf buuta!

አቤል አቡና ታስሮ "ለስም ማጥፋት ወንጀል" 14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ፖሊስ እንደ ጠየቀበትና ፍርድ ቤት ግን 3 ቀን ብቻ መፍቀዱን ሰማኹ። ከዚህ ነገር ኹለት ነገር ታዝቤአለኹ፦ 1. ፖሊስ ጊዜ ቀጠሮ የ
አቤል አቡና ታስሮ "ለስም ማጥፋት ወንጀል" 14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ፖሊስ እንደ ጠየቀበትና ፍርድ ቤት ግን 3 ቀን ብቻ መፍቀዱን ሰማኹ። ከዚህ ነገር ኹለት ነገር ታዝቤአለኹ፦ 1. ፖሊስ ጊዜ ቀጠሮ የሚጠየቅባቸው ወንጀሎች የትኞቹ እንደ ኾነ ይጠፋዋል ብዬ አላምንም። እንደ ውንብድና፣ ግድያ፣ ሽብርተኝነትና ... ሌሎች ማስረጃ ለመሰብሰብና ለማደራጀት ጊዜ ለሚፈልጉ ወንጀሎች መኾኑን የሥነ ሥርዓት ሕጉ በግልጥ አስቀምጦአል። ይህን ያህል በግል አቤቱታ ለሚቀርብ ወንጀል፣ አንድን "ሐሰተኛ ነቢይ" ለማስደሰት ረጅም መንገድ መሄድ ለምን አስፈለገው? 2. ፍርድ ቤት ጊዜ ቀጠሮን በተመለከተ መስጠቱ በሕግ የተፈቀደለት አግባብ ቢኾንም፣ ፖሊስ ስላቀረበ ብቻ ይሰጣል የሚል የሕግ መርኅ ግን የለም። በተለይ ደግሞ ዋስትና የማያስከለክሉና ተጠርጣሪው ቢወጣ ማስረጃ ሊያጠፋ፣ ሊያባብል የማይችልበት ኹኔታ ካለ ወዲያውኑ በፖሊስ የቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አድርጎ ዋስትና የመፍቀድ የማይገፈፍ ነጻ ሥልጣን አለው። በአቤል አቡና ላይ ግን ይህን አልተጠቀመም። ፍትሕ በዚህ መንገድ ትዛባለች ብቻ ሳይኾን ትታፈናለች። ዐቃቤ ሕግ ከፖሊስ ጋር እንደ መሥራቱ ይህን ዐይነት ከፍ ያለ ስህተት ማስተካከል ሲገባውም አላደረገም። መጽሐፍ፣ ​"ጽድቅንና ፍትሕን ማድረግ መሥዋዕት ከማቅረብ ይልቅ በእግዚአብሔር ዘንድ የተመረጠ ነው።" (ምሳ. 21፥3) እንዲል በፍትህ ዙፋን ያሉ ይህን ቃል ያስተውሉ ዘንድ እንጸልያለን። ለወንድማችን ብርቱ ትጋትን ይስጥ፤ አሜን። የቴሌግራም አድራሻ -