cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Admas Media - አድማስ ሚዲያ

ይህ Admas Media -አድማስ ሚዲያ - ኦፈሽአል ቴሌግራም ነው። የሚወዱትን Admas Media -አድማስ ሚዲያ ማህበራዊ ገፅ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። This is Admas Media - አድማስ ሚዲያ Official Telegram Channel መልዕክት መቀበያ እና ለማንኛውም አይነት ጥያቄ @Admas_media_bot እንዲሁም ለማስታውቂያ ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ

Більше
Рекламні дописи
4 136
Підписники
-424 години
-847 днів
-40730 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

በመደራጀት ላይ ባለዉ ግዕዝ ባንክ ለስራ ማስኬጃ በሚል 9 ሚሊዮን ብር ወስደዋል የተባሉ አደራጅ አባላት መታገዳቸዉን ኮሚቴዉ አሳወቀ 👉🏼 በአንጻሩ የታገዱ ሶስት አባላት መቐለ የሚገኘዉን የባንኩን ጽ/ቤትን የተቆጣጠሩ ሲሆን ጉዳዩን በሚመለከት በቅርቡ ባንኩ ማብራሪያ ሰጣለሁ ብሏል በመደራጀት ላይ ባለዉ ግዕዝ ባንክ አደራጅ ኮሚቴ አባላት ከሰሞኑ ተፈጠረ ወይንም ይፋ ወጣ በተባለ ዉዝግብ በመደራጀት ላይ ያለዉ ባንኩ ፈተና እንዳጋጠመዉ ተነግሯል። በዋነኛነት በዉስጥ ችግር ክፍፍል አጋጥሞታል የተባለዉ ግዕዝ ባንክ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ጦርነት ወቅት የባንኩ አደራጅ ኮሚቴ ሶስት አባላት ለእያንዳንዳቸው ሶስት ሚሊዮን ብር ለስራ ማስኬጃ በሚል ህገወጥ በሆነ መልኩ ገንዘብ አዉጥተዉ እንደነበር መረጋገጡን የግዕዝ ባንክ አደራጅ ኮሚቴ ም/ል ሰብሳቢ እና የአዲስአበባ የግዕዝ ባንክ ጽ/ቤት አስተባባሪ  አቶ ቶማስ ሀይሉ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። ሶስቱ ግለሰቦች ገንዘቡን ለ 27 ወራት 2015 በእጃቸዉ ላይ አስቀምጠዉ ነበር ያሉት አቶ ቶማስ ፤ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም በቅርቡ በተካሄደ ጉባዔ ግለሰቦቹ ገንዘቡን እንዲመልሱ መደረጉን ነግረዉናል። በምስረታ ላይ ያለዉ ባንኩ በዉስጣዊ ችግሮች መፈተኑን የገለጹት የአደራጅ ኮሚቴዉ ም/ል ሰብሳቢ ፤ ሶስቱ ግለሰቦች እግድ ቢወጣባቸዉም መቐለ የሚገኘዉን የባንኩን ጽ/ቤት በሀይል ተቆጣጥረዋል ብለዋል። ለፖሊስ የተሳሳተ መረጃን በመስጠት ፣ ህጋዊ ያልሆነ ማህተም በመጠቀምና ህጋዊ ሰብሳቢዉን በሀይል አስወጥተዉ ቢሮዉን ተቆጣጥረዉታል ብለዉናል። ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥንም ባደረገዉ ማጣራት ሶስቱ ግለሰቦች ከሰሞኑ በትግራይ ለሚገኙ የመገናኛ ብዙሃን ህጋዊነታቸዉን አስመልክቶ መግለጫ መስጠታቸዉን ነዉ። ሶስቱ የባንክ ሂሳብ ፈራሚ የነበሩት ግለሰቦች ያወጡትን ገንዘብ ከነወለዱ እንዲከፍሉ የተወሰነባቸዉ ሲሆን ዘጠኝ ሚሊዮን ብሩን ቢመልሱም ቀሪ ወለዱን እንዲከፍሉ ጥረት እየተደረገ እንደነበርም ገልጸዋል። ግለሰቦቹ ገንዘቡን መዉሰዳቸዉን በዉጪ ኦዲተር መረጋገጡንም አክለዋል። አቶ ቶማስ ባለድርሻ ሰዎች ገንዘባቸዉ የት መድረሱን መጠየቅ አለባቸዉ ብለዋል። በባንኩ ዉስጥ የተፈጠረዉን ችግር ለብሔራዊ ባንክ ሪፖርት አድርገናል ያሉት አቶ ቶማስ በዚህ ችግር የተነሳ ተጨማሪ የአደራጅ ኮሚቴ አባላትን ማካተቱንም ተናግረዋል። ሶስቱ ግለሰቦች ችግር እየፈጠሩብን ይገኛሉ ሲሉም ይከስሳሉ። የግዕዝ ባንክ አደራጅ ኮሚቴ አባላት በቅርቡ ጉዳዩን በሚመለከት ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ የሚሰጥ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥንም ጉዳዩን በመከታተል በተለይም ለባለአክሲዮኖች መረጃዉን የሚያደርስ ይሆናል።
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በ10 አመታት ውስጥ ሰዎችን ማርስ ላይ ማስፈር እንጀምራለን-ኤለን መስክ በቀጣይ 10 አመታት ውስጥ ሰዎችን ማርስ ላይ ማስፈር እንደሚጀመርና በ30 አመት ውስጥ ማርስ ላይ ዘመናዊ ከተማ እንደሚገነባ የስፔስ ኤክስ መስራች ኤለን መስክ ገልጿል። የማርስ ከተማ ግንባታን እውን ለማድረግ ስፔስ ኤክስ በርካታ የቅኝት ሳተላይቶችን በቅርቡ እንደሚልክ ማስታወቁን የዴይሊ ስታር ዘገባ ያመላክታል። "በጥቂት አመታት ውስጥ ሰዎችን በማርስ ላይ የማስፈር ዕቅዳችንን ዕውን እናደርጋለን" ብሏል የ52 ዓመቱ ቢሊየነር ኤለን መስክ። "ከ10 ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ሰዎችን ማርስ ላይ ማስፈር እንጀምራለን፤ ከበረታን እስከ 20 ዓመት፣ በእርግጠኝነት ግን በ30 ዓመት ውስጥ ዘመናዊ ከተማ በማርስ ላይ እንገነባለን" ብሏል ኤለን መስክ። እ.አ.አ 2002 የተመሰረተው ስፔስኤክስ ወደ አለማቀፉ የህዋ ጣቢያ ለመጀመሪያ ጊዜ መንኮራኩር እና ጠፈርተኞችን የላከ የግል ኩባንያ ነው።
Показати все...
#Hawassa ➡️ " ንፋስ በመጣ ቁጥር ጉዳት እየደረሰ ነው። እሮብ የአንድ ሰው ህይወት አልፏል " - የሀዋሳ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ➡️ " ጉዳት የደረሰበት የካፌ አስተናጋጅ ነው። በወቅቱ ወደህክምና ተወስዶ የህክምና እርዳታ ቢደረግለትም ህይወቱ ግን ሊተርፍ አልቻልም " - የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ በሀዋሳ ከተማ ፤ ፒያሳ በሚገኘው ንብ ባንክ ህንጻ ላይ የወደቀ መስታወት የአንድ ወጣት ህይወት ቀጥፏል። ህንጻው በዝናብና ንፋስ ወቅት እቃ ሲወድቅበት የመጀመሪያው እንዳልሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሀዋሳ የቤተሰብ አባላቱ ጥቆማ ደርሶታል። በቅርቡ የተመረቀዉ የንብ ህንጻ ከዘጠነኛ ፎቅ ላይ የወደቀ መስታወት የህንጻው ወለል ላይ ስራ ላይ የነበረ ሰራተኛ ላይ ማረፉን ተከትሎ ሰራተኛው ህይወቱ አልፏል። በሀዋሳ እሮብ ከ9 ሰአት በኋላ የነበረው ከባድ ዝናብና ውሽንፍር ባስከተለዉ ነፋስ ከህንጻዉ ላይ የወደቀ መስታወት የሰዉ ህይወት ማጥፋቱን ለማረጋገጥ ችለናል። አንድ የሀዋሳ የቤተሰባች አባል ፤ " ንፋስ በመጣ ቁጥር ከህንጻው ላይ በሚወድቅ ቁስ ተደጋጋሚ ጉዳት በግለሰቦች ላይ ሰራተኞች ላይ እየደረሰ ነው። እሮብ አንድ ሰራተኛ መስታወት ወድቆበት እጁ የመቆረጥ ፣ አናቱ ላይ የመጎዳት በኃላም ህይወቱ አልፏል። ህንጸው ግልጽ የሆነ የግንባታ ጉድለት ይታይበታል " ሲል ቃሉን ሰጥቷል። በዚህ ጉዳይ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የሰጡት የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ ወንድማገኝ ቶርባ ፤ ጉዳት የደረሰበት ወጣት የካፌ አስተናጋጅ መሆኑንና በወቅቱ ወደህክምና ተወስዶ የህክምና እርዳታ ቢደረግለትም ህይወቱ ግን ሊተርፍ እንዳልቻለ ገልጸዋል። ይሁንና " ህንጻው ላይ ተደጋጋሚ ችግር ተስተውሏል " ለሚባለዉ ቅሬታ ካሁን በፊት የደረሰ አደጋን የተመለከተ ሪፖርት የለም ሲሉ ገልጸዋል። በወቅቱ በዚህ ህንጻ ውስጥ ከደረሰዉ አደጋ  ውጭ በከተማዉ የተከሰተዉ ነፋስ በርካታ የንብረት ጉዳት ማስከተሉንም አስታውሰዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የህንጻዉን አስተዳዳሪዎች በጉዳዩ ዙሪያ ለማነጋገር ያደረገዉ ሙከራ አልተሳካም። ምላሽ አለም ካሉ መስተናገድ ይችላሉ @tikvahethiopia
Показати все...
በቁጥጥር ስር ውሏል! የአሶሳ ዩኒቨርስቲ ተማሪ በነበረችው ደራርቱ ለሜሳ ግድያ ወንጀል የተጠረጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ። የወረዳ አንድ  ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር በላቸው ፈረደ እንደገለጹት የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸው በአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ ልዩ ቦታው ሰላም ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ዕለቱ ረቡዕ ግንቦት 07/2016 ዓ/ም ከጧቱ በግምት 2:45 ላይ በሟች እና በተጠርጣሪው መካከል በተፈጠረው በሀሳብ ያለመግባባት ምክንያት በአሰቃቂ ሁኔታ ጀርባዋ ላይ  በጩቤ በመውጋት የተማሪዋ ህይወት ሊያልፍ ችሏል ሲሉ ተናግረዋል። ምክትል ኮማንደሩ አክለውም ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ወንጀሉን የፈጸመውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ የሚገኝ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ የምርመራ ውጤቱን በአጭር ጊዜ ለህዝብ እንደሚገለጽም ተናግረዋል። በመጨረሻም የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ከዩኒቨርስቲው ግቢ ውጪ እና ተጠርጣሪው ከአዲስ አበባ ዱከም ከተማ አቋርጦ ወደ አሶሳ ከተማ ለስራ ጉዳይ በመምጣት የወንጀል ድርጊት የፈፀመ ሲሆን ነገር ግን በአንዳንድ ማህበራዊ ሚድያዎች ድርጊቱ የተፈጸመው በግቢ ውስጥ ነው በሚል የሚሰራጨው እና የብሔር ግጭት አስመስለው የሚወራው ፍጹም ከእውነት የራቀ እና ሁለቱም የአንድ ብሔር ተወላጅ እንዲሁም በጓደኝነት አብረው እየኖሩ የነበሩ መሆኑን ኃላፊው ገልጸዋል።
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ያደረጉትን ንግግር ተቃወመች የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ለኢትዮጵያ መንግሥት ላይ "ውንጀላ አቅርበዋል"፤ "መንግሥት አገሪቱን እንዴት መምራት እንዳለበትም ያልተጠየቁትን ምክር ለግሰዋል" በማለት ወቅሷል። የአምባሳደሩ ንግግር "ትርጉም የማይሰጡ" እና "በበቂ ኹኔታ ያልተጤኑ" ሃሳቦችን ያካተተ ነው ያለው ሚንስቴሩ፣ አምባሳደሩ "በምርጫ የተመረጠውን መንግሥት በኃይል ለመጣል የሚሠሩ ቡድኖችንም በስም ጠቅሰዋል" በማለት ተችቷል። ኢምባሲው፣ በአምባሳደሩ መግለጫ ላይ የተንጸባረቁትን "የፍሬ ነገር ስህተቶች" ለማስተካከል ከኢምባሲው ጋር እንደሚሠራ ገልጧል። አምባሳደር ማሲንጋ ትናንት የመን የማኅበረሰብ ትምህርት ቤት ውስጥ ባደረጉት ንግግር፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደው ጦርነት በሲቪሎች ላይ እያደረሰ ያለውን ጉዳይ በመጥቀስ "አገር ዓቀፍ የተኩስ አቁም" እንዲደረግ ጠይቀው ነበር።
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
በሻሸመኔ ከተማ ንፋስ በቀላቀለ ከባድ ዝናብ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በከተማዋ ሙሉ በሙሉ ተቋረጠ  በሻሸመኔ ከተማ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ መስመር ላይ ጉዳት በመድረሱ የኃይል አቅርቦት መቋረጡ ተገልጿል። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን እሮብ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ከባድ ዝናብ በኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የኃይል መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የሻሸመኔ ከተማ ዲስትሪክት ሃላፊ የሆኑት አቶ ጣሂር አህመድ በተለይ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በዚሁ ምክንያት ግንቦት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ጀምሮ በሻሸመኔ ከተማ እና በዙሪያው በሚገኙ ከተሞችና አካባቢዎች የሃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል።   የተቋረጠውን የሃይል አቅርቦት ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን  በሻሸመኔ ከተማ እና በከተማዋ ዙሪያ የሚገኙ ደንበኞቻች  አገልግሎቱ እኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቅ እናበአካባቢው የወደቁ ምሰሶዎች ጉዳት እንዳያደርስ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አቶ ጣሂር አህመድ   መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
Показати все...
#የአሜሪካ_አቋም! " ግጭት የኢትዮጵያውያንን #ስቃይ_ከማባባስ ያለፈ መፍትሔ የለውም " - አሜሪካ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ አሜሪካ ስለ ኢትዮጵያ ያላትን ፖሊሲ በተመለከተ ምን አሉ ? - በትጥቅ ግጭት ውስጥ የገቡ አካላት፣ ግጭት አቁመው በንግግር ሰላምን ሊያሰፍኑና የሰብአዊ መብቶችን ማክበር አለባቸው። - የታጠቁ ቡድኖች ፖለቲካዊ ዓላማዎቻቸውን በአመፅ ለማሳካት እየገፉ ናቸው ፤ መንግስትም ይህን ለመከላከል የሚወስዳቸው ርምጃዎች፣ በፖለቲካ ምኅዳሩ ላይ የማይካድ ተጽእኖ አለው። ውይይትን ወደ ጎን ያለው ይህ አካሔድ የመብት ጥሰቶች እንዲቀጥሉ አድርጓል። - ሰላማዊ ዜጎች፣ በተለያዩ ኀይሎች ከሕግ ውጭ ግድያ፣ የዘፈቀደ እስራት፣ አስገዳጅ ስወራ፣ ከግጭት ጋራ የተያያዘ ጾታዊ ጥቃት እና ሌሎችም ጥቃቶች እየተፈጸሙባቸው መሆኑን የሚገልጹ ዘገባዎችን ማየቱ እጅግ ያሳዝናል። - የተፈጸሙ ጥፋቶች እውነተኛና ግልጽ የሽግግር ፍትሕ ሒደት በተከተለ የተጠያቂነት አሰራር በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል። - ሽፍታዎች፣ የታጠቁ ቡድኖች፣ አንዳንዴም የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች፤ በህይወት የመኖር፣ የሰብዓዊ ክብርን፣ መከበርን በመሰሉ መብቶች ላይ ያለምንም ተጠያቂነት ጥሰቶች ይፈጽማሉ። - በጦርነት እና ግጭት ወቅት እንኳ የሰብዓዊ መብቶች ሊረሱ አይገባም። - ሁሉም ሀገር ራሱን የመከላከል ህጋዊ መብት አለው፤ ሆኖም ሀገራት ራሳቸውን የሚከላከሉበት መንገድ ያለምንም ጥርጥር የወደፊት ግጭቶችን አካሄድ የሚወስን ነው። - ሀገር የመከላከያ መንገዶቹ በዛሬው እና በወደፊቱ የማህብረሰብ ትስስር ላይ ይበልጡኑ ተጽዕኖ የሚያሳድር ነው። - የታጠቁ ወገኖች የፖለቲካ ግባቸውን ከውይይት ይልቅ በግጭት ለማሳካት ሲሞክሩ፤ ለሚፈጸሙ በደሎች ሁኔታዎች የተመቻቹ ይሆናሉ። - በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱት እራሳቸውን ' ፋኖ ' ብለው የሚጠሩ ታጣቂ ቡድኖች ንግግር / ድርድር አንቀበልም ማለታቸው እራሳቸውን ነው የሚጎዳቸው። በአማራ ያሉ በርካታ ሰዎች " የቆሙለት ዓላማ ፍትሃዊ ነው " የሚል እምነት/አላቸው ይህንኑ መከራከሪያቸውን ከግጭት ይልቅ በውይይት ማቅረብ አለባቸው። - በአማራ ክልል ውጊያዎች የሚቀጥሉ ከሆነ በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች እንዳለው በውጤቱ የሚሰቃዩት ሰላማዊ ሰዎች ናቸው።   - ህወሓት በኀይል ወሰን ለማስመለስ ከሚደረግ እንቅስቃሴ መቆጠብ አለበት። - የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ኃይሎች በድርድር ተስፋ ሳይቆርጡ መተማመን ለመገንባት የሰላም ውይይትን ሊቀጥሉ ይገባል። - ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በውስጣዊ ግጭቶች እየታመሰች ትገኛለች። - የኢትዮጵያ መንግስት የአገሪቱን ችግሮች በኀይል ለመፍታት ከሚያደርገው ጥረት መቆጠብ አለበት። በእስር ላይ የሚገኙ ቁልፍ የፖለቲካ ሰዎችን መፍታቱ ጠቃሚ ነው፤ ያን ተፈጻሚ ማድረግ ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉትን የፖለቲካ ውይይት ሊያግዝ ይችላል። - ጊዜያዊ አገር አቀፍ የተኩስ አቁም ስምምነት ሊፈጸም ይገባል። - ሁሉም የታጠቁ ተዋናዮች፣ በመላ አገሪቱ አዲስ የሕዝብ መፈናቀልን ጨምሮ ለሰዎች ስቃይ ምክንያት ከመሆን መገታት አለባቸው። - የታጣቁ ኃይሎች ት/ቤቶችን፣ ጤና ተቋማትንና የውኃ መሠረተ ልማቶችን ዒላማ ማድረግ ማቆም አለባቸው። የተሟላና ያልተገደበ ሰብአዊ አቅርቦት ሊኖር ይገባል። ይህም ጊዜያዊ አገር አቀፍ የተኩስ አቁም ማድረግን ይጨምራል። - ግጭት የኢትዮጵያውያንን ሥቃይ ከማባባስ ያለፈ መፍትሔ የለውም። ውይይት ትኩረት ሊደረግበት ይገባል። - ምንም እንኳን ፍጹም ሊሆን ባይችልም፣ ሁሉም ወገኖች የአገራዊ ምክክሩን ዕድል ሊጠቀሙበት ይገባል። #USEmbassyAddisAbaba
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram