uk
Feedback
Nikodimos Christian center

Nikodimos Christian center

Відкрити в Telegram

Nikodimos Show is a unique program which is hosted by the famous Ethiopian Gospel Singer Tigist Ejigu, https://www.facebook.com/tigist.ejigu.5 This show is working on creating awareness on sensitive Christian issues inside the Church of Ethiopia.

Показати більше
6 580
Підписники
-424 години
+27 днів
+1530 день
Архів дописів
ይህ ተስፋ በአዲስ ኪዳን ሙሉ ፍፃሜውን አግኝቷል በክርስቶስ የመዳን በር ያለ ልዩነት ለሁሉም ተከፍቷል ሐዋርያት ስራ ምዕራፍ 8 ላይ የምናገኘው ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የዚህ ምስክር ነው በክርስቶስ ያመኑ ሁሉ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች የሚበልጥ መታሰቢያቸው ስማቸው በሰማይ መዝገብ መፃፉ ነው የሚጠጉት ፡ የሚወዱት ፡ የሚያገለግሉት ፡ ሰንበትን የሚያከብሩ ኪዳኑን የሚጠብቁ ሁሉ ወደ ተቀደሰው ተራራው ደርሰዋል! “ቤቴ ለህዝቦች ሁሉ ፀሎት ቤት ተብሎ ስለሚጠራ ነው” የእግዚአብሔር አላማ አለም ሁሉ እንዲድን ነው በእውነተኛ ልብ ወደ እርሱ የሚመጡትን ያለ ልዩነት ይቀበላል “8. የተበተኑትን እስራኤል የሚሰበስብ፣ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ከተሰበሰቡት በተጨማሪ፣ሌሎችን እንደ ገና እሰበስባለሁ።”(አ.መ.ት) ዛሬም እግዚአብሔር እየሰበሰበ ነው የዮሐንስ ወንጌል 10 16 ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ። የእግዚአብሔር ቤተሰብ (መንጋው) እኛ ከምናስበው በላይ ትልቅ ነው ከቁጥር 9-12 ክፉ ፡ እራስ ወዳድና የማያስተውሉ እረኞችን ይወቅሳል ህዝቡን በመጠበቅና በመምራት ፋንታ የራሳቸውን ጥቅምና ጊዜያዊ ደስታ ያሳድዳሉ የዮሐንስ ወንጌል 10 11 መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል። መንፈሳዊ መሪነት ትልቅ አደራና ሀላፊነት ነው ምን እንማር ? 1. እምነታችንን እንኑረው ፡ ፀጋ የተሰጠን ይህን ሊያስችለን ነው 2. እግዚአብሔር ያለ ልዩነት ተቀብሎናልና ያለመወደድና ተቀባይነት የማጣትን ስሜት እናስወግድ 3. በክርስቶስ አርፈናል ፡ አሁን የቀረው እግዚአብሔር ሁሉን በክርስቶስ ሊጠቀልል : ሲሰበስብ አብሮ ሰራተኛ መሆን ነው 4. መንጋው ሰፊ ነውና ልባችንን እናስፋ ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ 57 ተግሳጽና መፅናናት “1ጻድቃን ሲሞቱ ማንም ትኲረት አይሰጠውም፤ ደጋግ ሰዎች በሞት ሲወሰዱ ከክፉ ነገር እንዲድኑ የተወሰዱ መሆናቸውን ማንም ሰው ሊያስተውለው አይችልም። 2ቀጥተኛ ሕይወትን የሚኖሩ ሰዎች ሰላም ይኖራቸዋል፤ በሚሞቱበትም ጊዜ ዕረፍትን ያገኛሉ።”(አ.ት) ሞትን ሁልጊዜ እንደ ክፉ ነገር መቁጠር ተገቢ አይደለም ይልቁንም ምክንያቱን ማስተዋል ነው ያለብን እግዚአብሔር በቅንነት የሚሄዱትን ለአኗኗራቸው ብቻ ሳይሆን ለአሟሟታቸውም ይጠነቀቅላቸዋል ሰላማቸው ሳይደፈርስ ወደ እረፍታቸው ይገባሉ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 1 23 በእነዚህም በሁለቱ እጨነቃለሁ፤ ልሄድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር እናፍቃለሁ፥ ከሁሉ ይልቅ እጅግ የሚሻል ነውና፤ እግዚአብሔር ሞትን የሚያይበት መንገድ እኛ ከምናይበት መንገድ እጅግ የራቀ ነው ብዙዎቻችን ስለሞት አለኝ የምንለው እምነት የምንወዳቸውን በማጣት ወይንም እኛ ራሳችን ከሞት ጋር ስንፋጠጥ ተፈትኖ ወድቋል 3-9 የጣኦት አምልኮን ማጋለጥ ጣኦት አምልኮ መንፈሳዊ ግልሙትና ነው እውነተኛውን አምላክ በመተው የውሸት አማልክትን ከመከተል ባሻገር ለእግዚአብሔር ብቻ ሊኖራቸው የሚገባውን ፍቅር ፡ በእርሱ ብቻ ሊኖራቸው የተገባውን መተማመን ለሌሎች ባዕዳን መሰጠትም ነው ከ 10-13 የጣኦታት ከንቱነት “ደከምሽ ፡ ግን ተስፋ የለውም አላልሽም” ከሀጢአት ውስጥ ደስታን መፈለግ ያደክማል ፡ ግን ሰዎች ቶሎ ተስፋ ቆርጠው አይመለሱም “11“እኔን ባለማስታወስና ስለ እኔ ባለማሰብ ውሸት የተናገራችሁት ማንን ፈርታችሁ ነው? እኔን ያልፈራችሁኝ ለብዙ ጊዜ ዝም ስለልኩና እንዳላየ ስለሆንኩ ነውን?”(አ.ት) የእግዚአብሔር ዝምታ እንዳንፈራው(እንደናከብረው) ሊያደርገን አይገባም “የሰበሰብሻቸው ጣኦታትሽ እስኪ ያድኑሽ !” ለክፉ ቀን ብለን የሰበሰብናቸው ነገሮች እምነታችንን እና ፍቅራችንን ከእግዚአብሔር ላይ አንስተው ከወሰዱት አያድኑንም ፡ “ነፋስ ጠራርጎ ይወስዳቸዋል” 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 2 17 ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል። 13-14 የንስሀ ጥሪ “እኔን መጠጊያው ያደረገ ሰው ግን ምደሪቱን ይወርሳል” “14. እንዲህ ይባላል፤“አብጁ፤ አብጁ፤ መንገድ አዘጋጁ፤ከሕዝቤ መንገድ ዕንቅፋት አስወግዱ።”(አ.መ.ት) መጥምቁ ዮሐንስ ይህንን ጥሪ አስተጋብቷል የማቴዎስ ወንጌል 3 3 በነቢዩ በኢሳይያስ። የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ የተባለለት ይህ ነውና። ዛሬም እግዚአብሔር ወደ እርሱ እንዳንመለስ ያደረገንን እንቅፋት እንድናስወግድ ጥሪ ያደርጋል ያልተገባ ጓደኝነት ፡ አላስፈላጊ ልምምዶች ፡ የገንዘብና የአለም ፍቅር ……. ምንም ይሁን ምን እንቅፋት ከሆኑብን መወገድ አለበት “15ከፍተኛውና ከሁሉ የላቀው፥ ለዘለዓለም የሚኖር ቅዱሱ እንዲህ ይላል፦ “እኔ በተቀደሰና በከፍተኛ ቦታ፥ እንዲሁም ልባቸው ከተሰበረና መንፈሳቸው ትሑት ከሆኑት ጋር እኖራለሁ፤ ይኸውም ትሑት መንፈሳቸውንና የተሰበረ ልባቸውን ለማደስ ነው።”(አ.ት) እግዚአብሔር እኖርባቸዋለሁ ያላቸው የሀብቱ ስፍራዎች ልዩነት በጣም አስደናቂ ነው 1. በተቀደሰና በከፍተኛ ስፍራ 2. ልባቸው ከተሰበረና መንፈሳቸው ትሁት ከሆኑት ጋር የማቴዎስ ወንጌል 5 3 በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። እግዚአብሔርን የሚስበው ትህትና እንጂ የሰው ብርታት ፡ ብልፅግና ወይንም ሌላ አይደለም “16እኔ ዘወትር ሰውን አልወቅስም..." እግዚአብሔር የሚቆጣው በአላማና በገደብ ነው ፡ አላማው እንዲመለሱ ስለሆነ እስኪደመሰሱ በቁጣው አይፀናም “መንገዶቹን አይቻለሁ ቢሆንም እፈውሰዋለሁ” የሚፈውሰው ስለማያውቅ ሳይሆን ፀጋው ከሰው ልጆች ሀጢአት ስለሚበልጥ ነው ወደ ሮሜ ሰዎች 5 20 -21 በደልም እንዲበዛ ሕግ ጭምር ገባ፤ ዳሩ ግን ኃጢአት በበዛበት፥ ኃጢአት በሞት እንደ ነገሠ፥ እንዲሁ ደግሞ ጸጋ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሣ በጽድቅ ምክንያት ለዘላለም ሕይወት ይነግሥ ዘንድ፥ ጸጋ ከመጠን ይልቅ በለጠ። “19በሩቅና በቅርብ ላሉትም ሁሉ ሰላም ይሁን! እኔ ሕዝቤን እፈውሳለሁ፤”(አ.ት) ይህ ሰላም የተገኘው በክርስቶስ ኢየሱስ ነው ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2 17 መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን፥ ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምስራች ብሎ ሰበከ፤ 20-21 ክፉዎች ግን ሰላም የላቸውም ! ምክንያቱም ሰላም በሀጢአት ውስጥ አይገኝም ምን እንማር ? 1. ጥንታዊም ሆነ ዘመናዊ ጣኦት አምልኮ መንፈሳዊ ግልሙትና ነው 2. እግዚአብሔርን ስለ ዝምታው እናክብረው እንጂ አንናቀው 3. እግዚአብሔርን የሚስበው የኛ ምድራዊ ስኬት ሳይሆን ትህትና ነው 4. ወደ እግዚአብሔር እንመለስ ፡ እርሱ ሊፈውሰን ተዘጋጅቶ ይጠብቀናል

ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ 55-57 ጥሪ ለተጠሙ ሁሉ ! ቁጥር 1 ላይ ታላቁን ግብዣ እናገኘዋለን “1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ “እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ ወደ ውሃው ኑ! የምትገዙበት ገንዘብ የሌላችሁ ኑና ገዝታችሁ ብሉ! ኑና ያለ ገንዘብና ያለ ዋጋ ወተትና የወይን ጠጅን ግዙ።”(አ.ት) ጥሪው ለተጠሙ ሁሉ ነው ፡ ነገር ግን መጠማታችንን ማወቅና ምላሽ መስጠት ከሰው የሚጠበቅ ነው ገንዘብ የሌላችሁ (መግዛት የማትችሉ) ኑ በነፃ ግዙ ፡ ይህ ሀሳብ በቀጥታ የእግዚአብሔርን ፀጋ አመልካች ነው ድነት ነፃ ስጦታ ነው ፡ ነፃ የሆነው ግን ርካሽ ስለሆነ ሳይሆን ውድ ስለሆነና ችለን ስለማንገዛው እግዚአብሔር ከፍሎልን ነው የዮሐንስ ወንጌል 7 37 ከበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢየሱስ ቆሞ። ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ። “2. ገንዘባችሁን እንጀራ ባልሆነ ነገር ላይ ለምን ታጠፋላችሁ?በማያጠግብስ ነገር ላይ ለምን ጒልበታችሁን ትጨርሳላችሁ?ስሙ፤ እኔን ስሙኝ፤ መልካም የሆነውንም ብሉ፤ነፍሳችሁም በጥሩ ምግብ ትደሰታለች።”(አ.መ.ት) የማያረካ ውሀ የማያጠግብ እንጀራ ፍለጋ ገንዘባችሁን አታባክኑ የምትባክኑለት ነገር ባዶና ጊዜያዊ ነው ! “እኔን ስሙኝ” መልካም የሆነውን ለመብላትና ለመደሰት እግዚአብሔርን መስማት ያስፈልጋል የዮሐንስ ወንጌል 6 35 ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ አይጠማም። እውነተኛና ዘላለማዊ እርካታን የሚሰጥ መብል ክርስቶስ ነው “3“ጆሮአችሁን አዘንብላችሁ ወደ እኔ ቅረቡ፤ በሕይወት ትኖሩ ዘንድ ቃሌን አድምጡ፤ ዳዊትን እንደ ወደድኩት እናንተን በታማኝነት ለመውደድ ዘለዓለማዊ ቃል ኪዳን እገባለሁ።”(አ.ት) ….አዘንብላችሁ ፡ ጠጋ ብላችሁ ብትሰሙኝ በህይወት ትኖራላችሁ የዘላለም ፍቅሬን ኪዳን ትቀበላላችሁ እዚህ ጋ “መስማት” ለመታዘዝ በተዘጋጀ ልብ ትኩረት ሰጥቶ ማዳመጥ ነው 4-5 ለአህዛብ ሁሉ ምስክር ትሆናላችሁ እግዚአብሔር አንድን ህዝብ የወደደው ሌላውን ለመጣል ሳይሆን በተጠሩት ምስክርነት ሁሉን ለመጠቅለል ነው የማቴዎስ ወንጌል 28 19 -20 እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ። ጌታም የሰራበት መንገድ ተመሳሳይ ነው “6. እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፤ቀርቦም ሳለ ጥሩት። 7. ክፉ ሰው መንገዱን፣በደለኛም ሐሳቡን ይተው።ወደ እግዚአብሔር ይመለስ፤ እርሱም ምሕረት ያደርግለታል፤ወደ አምላካችን ይመለስ፤ ይቅርታው ብዙ ነውና።”(አ.መ.ት) “በሚገኝበት ጊዜ” ማለት እግዚአብሔር የሚደብቅበት ጊዜ አለ ማለት ሳይሆን ለየት ያለ መለኮታዊ ጉብኝት በሚሆንበት ጊዜ ፈልጉት ማለት ነው 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6 2 በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው። መለኮታዊ ጥሪ ሲደርሰን መዘግየት ዋጋ ያስከፍላል “ጥሩት” ወደ ሮሜ ሰዎች 10 13 የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና። ከመዳን ጥሪ በተጨማሪም ልዩ መለኮታዊ ጉብኝት በህይወታችን የሚሆንባቸው ጊዜያት አሉና ልናባክናቸው አይገባም “ክፉ ሰው መንገዱን : በደለኛም ሀሳቡን ይተው” ንስሀ አካሄድንና አስተሳሰብን መለወጥ ነው “ወደ እግዚአብሔር ይመለስ” ሀጢአት መስራት ማቆም ብቻ ሳይሆን ወደ እግዚአብሔር መመለስንም ይጨምራል የሉቃስ ወንጌል 15 20 ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ። እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት፥ ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው። ለሚመለሱ እግዚአብሔር ይቅር ለማለት ተዘጋጅቶ ይጠብቃቸዋል የዮሐንስ ወንጌል 6 37 አብ የሚሰጠኝ ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል፥ ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም፤ ከቁጥር 8-9 ከፍ ያለው የእግዚአብሔር መንገድ ! ከፍ ያለ ፡ ከማስተዋል በላይ የሆነ የእግዚአብሔር መንገድ ኢየሱስ ነው ፡ የሰው መንገድ ወደ እግዚአብሔር አያደርስም አድካሚና ውስብስብ ነው ሰዎች የኢየሱስን መንገድነት መቀበል የሚያቅታቸው እነርሱ ከሚያስቡት መንገድ እጅግ የራቀ ስለሆነ ነው “10. ዝናምና በረዶ ከሰማይ ወርዶ፣ምድርን በማራስ፣እንድታበቅልና እንድታፈራለዘሪው ዘር፣ለበላተኛም እንጀራ እንድትሰጥ ሳያደርግ፣ወደ ላይ እንደማይመለስ ሁሉ፣ 11. ከአፌ የሚወጣውም ቃሌ፣በከንቱ ወደ እኔ አይመለስም፤ነገር ግን የምሻውን ያከናውናል፤የተላከበትንም ዐላማ ይፈጽማል።”(አ.መ.ት) የእግዚአብሔር ቃል፡- ከሰማይ ነው የሚመጣው ፡ ህይወት እርካታና ፍሬያማነትን ይሰጣል ፡ የእግዚአብሔርን አላማ ይፈጽማል እንጂ በከንቱ አይመለስም ትንቢታዊነቱ አካላዊ ቃል የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን ያመላክታል የዮሐንስ ወንጌል 1 14 ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን። ኢየሱስ በከንቱ አልተመለሰም 12-13 “ከባቢሎን በደስታ ወጥታችሁ በደስታ ወደ ሀገራችሁ ትመለሳላችሁ” እግዚአብሔር ህዝቡን ከባቢሎን ለማውጣት ብዙ ሰራዊት ሳይሆን ቃል ነው የላከላቸው ቃሉ ያወጣችኋል ብቻ ሳይሆን በሰላም ወደ ሀገራችሁ ያደርሳችኋል አላቸው ! የዮሐንስ ወንጌል 8 32 እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው። የዮሐንስ ወንጌል 8 36 እንግዲህ ልጁ አርነት ቢያወጣችሁ በእውነት አርነት ትወጣላችሁ። ምን እንማር ? 1. ከመለኮታዊ ጉብኝት (ጥሪ) ጋር እንዳንተላለፍ እንጠንቀቅ 2. ህይወት የማይሰጡ ነገሮችን ከማሳደድ ተመልሰን እግዚአብሔርን እንስማ ፡ በፍቅሩ እንረፍ በህይወትም እንኑር 3. የራሳችንን(የትም የማያደርሰውን) መንገድ ትተን የእግዚአብሔርን መንገድ (ኢየሱስን) እንመነው 4. የእግዚአብሔር ቃል አርነት ያወጣል ሀገራችንም ያደርሰናል ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ 56 ለህዝቦች ሁሉ የተሰጠ መዳን “1. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ፍትሕን ጠብቁ፤መልካሙን አድርጉ፤ማዳኔ በቅርብ ነው፤ጽድቄም ፈጥኖ ይገለጣልና። 2. ሰንበትን ሳያረክስ የሚያከብር፣ክፉን ከማድረግ እጁን የሚሰበስብ፣ የሚገታ፣እነዚህን የሚፈጽም ሰው የተባረከ ነው።”(አ.መ.ት) የእግዚአብሔር ማዳንና ጽድቁ ወደ እኛ መምጣቱ ፍትህን ከመጠበቅ መልካሙን ከማድረግ ነፃ አያደርገንም የያዕቆብ መልእክት 2 17 እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው። ዛሬ ሰንበት ብለን የምናከብረው ቀንን ሳይሆን የአዲስ ኪዳን ሰንበት የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን ነው ወደ ዕብራውያን 4 9እንግዲህ ለእግዚአብሔር ሕዝብ የሰንበትን ዕረፍት የመሰለ ዕረፍት ገና ይቀረዋል፤ 10እግዚአብሔር ከሥራው እንዳረፈ እንዲሁም እግዚአብሔር ወደሚሰጠው ዕረፍት የሚገባ ከሥራው ያርፋል። (አ.ት) ዛሬ ሰንበትን ማክበር ማለት በክርስቶስ የተሰራው ስራ በቂ ነው ብሎ ማረፍ ነው ከ 3-7ልዩነት የለም ! መጻተኛና ጃንደረባ በዚያ ዘመን መሳተፍ (መካፈል) የማይችሉባቸው ብዙ ጉዳዮች ነበሩ አድሎና መገለል ይደርስባቸው ነበር “መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ”

302ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 13 - 16
302ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ  ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ  13 - 16 የዩቱብ  የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች  ታገኛላችሁ👇 YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316 TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu TIKTOK#2:-  tiktok.com/nikodimoschrstiancenter TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow

301ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 9 - 12 የ
301ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ  ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ  9 - 12 የዩቱብ  የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች  ታገኛላችሁ👇 YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316 TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu TIKTOK#2:-  tiktok.com/nikodimoschrstiancenter TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow

300ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 5 - 8 የዩ
300ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ  ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ  5 - 8 የዩቱብ  የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች  ታገኛላችሁ👇 YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316 TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu TIKTOK#2:-  tiktok.com/nikodimoschrstiancenter TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow

ሻሎም ቅዱሳን የሐምሌ ወር ንባብ መርሃግብር የሚከተለው ነው ሰኞ ሰኔ 29 ሉቃስ 1-4 ማክሰኞ ሰኔ 30 ሉቃስ 5-8 እሮብ ሀምሌ 1 ሉቃስ 9-12 ሐሙስ ሀምሌ 2 ሉቃስ 13-16 አርብ ሀምሌ 3 ሉቃስ 17-20 ቅዳሜ ሀምሌ 4 ሉቃስ 21-24 እሁድ ሀምሌ 5 ዩሐንስ 1-3 ሰኞ ሀምሌ 6 ዩሐንስ 4-6 ማክሰኞ ሀምሌ 7 ዩሐንስ 7-9 እሮብ ሀምሌ 8 ዩሐንስ 10-12 ሀሙስ ሀምሌ 9 ዩሐንስ 13-16 አርብ ሀምሌ 10 ዩሐንስ 17-21 ቅዳሜ ሀምሌ 11 ሐዋርያት 1-3 እሁድ ሀምሌ 12 ሐዋርያት 4-6 ሰኞ ሀምሌ 13 ሐዋርያት 7-9 ማክሰኞ ሀምሌ 14 ሐዋርያት 10-12 እሮብ ሀምሌ 15 ሐዋርያት 13-15 ሀሙስ ሀምሌ 16 ሐዋርያት 16-18 አርብ ሀምሌ 17 ሐዋርያት 19-21 ቅዳሜ ሀምሌ 18 ሐዋርያት 22-24 እሁድ ሀምሌ 19 ሐዋርያት 25-28 ሰኞ ሀምሌ 20 ሮሜ 1-3 ማክሰኞ ሀምሌ 21 ሮሜ 4-6 እሮብ ሀምሌ 22 ሮሜ 7-9 ሀሙስ ሀምሌ 23 ሮሜ 10-12 አርብ ሀምሌ 24 ሮሜ 13-16 ቅዳሜ ሀምሌ 25 1ኛ ቆሮንቶስ 1-3 እሁድ ሀምሌ 26 1ኛ ቆሮንቶስ 4-6 ሰኞ ሀምሌ 27 1ኛ ቆሮንቶስ 7-9 ማክሰኞ ሀምሌ 28 1ኛ ቆሮንቶስ 10-12 እሮብ ሀምሌ 29 1ኛ ቆሮንቶስ 13-16 ፀጋ ይብዛላችሁ🙏

299ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 1 - 4 የዩ
299ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ  ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ  1 - 4 የዩቱብ  የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች  ታገኛላችሁ👇 YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316 TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu TIKTOK#2:-  tiktok.com/nikodimoschrstiancenter TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow

"ኢየሱስ ሰማዕቱን ሊቀበል ቆመ!!" |የሐዋርያት ስራ ጥናት ምዕራፍ 7 | ቃልህ | #tigist_Ejigu #Hermela_Tesema #Rekik_Menda

298ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ 14 - 16
298ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ  ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ  14 - 16 የዩቱብ  የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች  ታገኛላችሁ👇 YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316 TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu TIKTOK#2:-  tiktok.com/nikodimoschrstiancenter TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow