Nikodimos Christian center
الذهاب إلى القناة على Telegram
Nikodimos Show is a unique program which is hosted by the famous Ethiopian Gospel Singer Tigist Ejigu, https://www.facebook.com/tigist.ejigu.5 This show is working on creating awareness on sensitive Christian issues inside the Church of Ethiopia.
إظهار المزيد6 565
المشتركون
-124 ساعات
-47 أيام
-730 أيام
أرشيف المشاركات
የይሁዳ ንጉሥ የኢዮስያስ ልጅ የነበረው ኢዮአቄም በነገሠ በአራተኛው ዓመት እንዲህ የሚል ቃል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ ኤርምያስ መጣ፤(አ.መ.ት)
ባሮክ ፀሀፊ ነበር
ኤርምያስ 36
4. ኤርምያስም የኔርያን ልጅ ባሮክን ጠራው፤ ባሮክም እግዚአብሔር የተናገረውን ቃል ሁሉ ከኤርምያስ አፍ ተቀብሎ በብራናው ላይ ጻፈ።(አ.መ.ት)
“2. “ባሮክ ሆይ፤ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይልሃል፤
3. አንተ፣ ‘እግዚአብሔር በሕመሜ ላይ ሐዘን ጨምሮብኛልና ወዮልኝ፤ ከልቅሶዬ ብዛት የተነሣ ደክሜያለሁ፤ ዕረፍትም የለኝም’ ብለሃል።”(አ.መ.ት)
ከኤርምያስ መልዕክትን ተቀብሎ ሲፅፍ ይሄ ሰው ፍርሀት ተሰማው ምክንያቱም የሚፅፈው በጣም ከባባድ የሆኑ የፍርድ ቃላቶችን ነው
እግዚአብሔር ግን ስለእያንዳንዱ ሰው ግድ ይለዋል
ባሮክን ህይወትህን አተርፋለው ሲለው እናያለን
“4. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “እንዲህ በለው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በምድር ሁሉ የገነባሁትን አፈርሳለሁ፤ የተከልሁትን እነቅላለሁ።
5. ታዲያ፣ ለራስህ ታላቅ ነገር ትሻለህን? በሰው ልጆች ሁሉ ላይ ጥፋት አመጣለሁና አትፈልገው፤ ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን በሄድህበት ሁሉ ሕይወትህ እንዲተርፍልህ አደርጋለሁ።’ ”(አ.መ.ት)
ለአንድ ሰው እግዚአብሔር ግድ ይለዋል ለእስራኤል ፍርድን እየተናገረ ባለበት በዚያው ሰአት ደግሞ ስለባሮክ ግድ ብሎት ህይወትህን አተርፋለው ይላል
ትንቢተ ኤርሚያስ ምዕራፍ 43-45
ከምዕራፍ 42 የቀጠለ ታሪክ ነው
ኤርምያስ 42
2. ነቢዩ ኤርምያስን እንዲህ አሉት፤ “ቀድሞ ብዙዎች ነበርን አሁን እንደምታየን ግን የቀረነው ጥቂት ነን፤ ስለዚህ እባክህ ልመናችንን ስማ፤ ለዚህ ለተረፈው ሕዝብ ሁሉ ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ።
3. አምላክህ እግዚአብሔር ወዴት መሄድ እንዳለብንና ምን ማድረግ እንደሚገባን እንዲነግረን ጸልይልን።”(አ.መ.ት)
ኤርምያስ ብዙ ጊዜ የእግዚአብሔርን ድምጽ ይነግራቸዋል አይታዘዙም አሁንም ደግሞ ጸልይልን አሉት
እግዚአብሔርም ከ 10 ቀን በኋላ መለሰላቸው አትውጡ ባላችሁበት ቆዩ አላቸው
የመጣው መልዕክት እነሱ ካሰቡት ጋር አንድ ስላልሆነ አልተቀበሉትም
እኛ ባቀድነው መሰረት ሳይሆን እግዚአብሔርን የምናስኬደው እርሱ ባዘጋጀልን እቅድ ውስጥ ነው እራሳችንን የምናስገዛው
መታዘዝን ስለማይፈልጉ ኤርምያስን ይከሱታል:: የእግዚአብሔርን መልዕክት አይደለም የነገርከን: ተገዝተህ ነው ይሉታል
ኤርምያስ የተናገረው እያንዳንዱ ነገር በፊታቸው ተፈፅሟል ግን አሁንም አያምኑም
ትዕቢተኛ ያስባላቸው ለእግዚአብሔር ቃል አለመታዘዛቸው ፡ የእግዚአብሔርን ሙሉ ማንነት አለመረዳታቸውና እራሳችን በቂ ነን ብለው ማሰባቸው ነው
እግዚአብሔር ነፃ አውጪ ብቻ እንደሆነ ነው የሚያስቡት ሀጢአትን የሚቀጣ አምላክ መሆኑን አልተረዱም
ነቢይ ማለት ከእግዚአብሔር የመጣውን ትክክለኛ ቃል የነገረን እንጂ የምንፈልገውን የሚነገረን ሰው ማለት አይደለም
ከቁጥር 4-7 ህዝቡ ወደ ግብፅ እንዲወርዱ የግድ ሲባሉ እናያለን
“4. ስለዚህ የቃሬያ ልጅ ዮሐናንና፣ የጦር መኰንኖቹ ሁሉ እንዲሁም ሕዝቡ በሙሉ እግዚአብሔር በይሁዳ ምድር እንዲቀመጡ ያዘዛቸውን ቃል አልሰሙም።(አ.መ.ት)
እንደ ህዝብ ነው በእግዚአብሔር ላይ ያመፁት
ከቁጥር 8-10 የእግዚአብሔር ቃል በግብፅ መጣ
“8. በጣፍናስም የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ፤(አ.መ.ት)
ከእግዚአብሔር ቃል ማምለጥ አንችልም
“9. “ትልልቅ ድንጋዮች ውሰድና በጣፍናስ ባለው የፈርዖን ቤተ መንግሥት በር ላይ የይሁዳ ሰዎች እያዩ በሸክላ ጡብ ወለል ውስጥ ቅበራቸው፤(አ.መ.ት)
እነዚህ የሸክላ ጡቦች የሚያሳዩት መሰረት መጣልን ነው
ቁጥር 10 ላይ እግዚአብሔር ባቢሎን መጥቶ እንደሚገዛቸው ይናገራል
ናቡከደነፆርም የእግዚአብሔርን ሀሳብ የሚፈፅም አገልጋይ ነው::
ስለዚህ እግዚአብሔር ወደ ግብፅ መምጣችሁ አያተርፋችሁም እያላቸው ነው
ለእግዚአብሔር ህዝብ መሸሻው ከሆነ ሀገር ወደ ሆነ ሀገር መሄዱ አይደለም መሸሸጊያው እራሱ እግዚአብሔር ሲሆን ብቻ ነው በሰላም መኖር የሚችለው
ትንቢተ ኤርሚያስ ምዕራፍ 44
ጣዖትን ማምለክ ያስከተለው ጥፋት
ከቁጥር 1-6 እግዚአብሔር ከአባቶቻቸው እንዲማሩ ይናገራል
“4. እኔም፣ ‘ይህን የምጠላውን አስጸያፊ ነገር አታድርጉ’ በማለት አገልጋዮቼን ነቢያትን ደጋግሜ ላክሁባቸው።”(አ.መ.ት)
ጣኦትን ማምለክ በእግዚአብሔር አይን አፀያፊ ነው
እግዚአብሔር ደጋግሞ ጣኦት እንዳያመልኩ ነግሯቸው ነበር
የደረሰባቸው ነገር በምን ምክንያት እንደሆነ ይነግራቸዋል
ከ 7-10 በግብፅ አሁን ላሉት ቅሬታዎች እግዚአብሔር ይናገራል
“7. “አሁንም የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ዘር እንዳይቀርላችሁ ወንዶችና ሴቶች፣ ልጆችና ሕፃናት በይሁዳ እንዳይገኙ ለምን እንዲህ ዐይነት ታላቅ ጥፋት በራሳችሁ ላይ ታመጣላችሁ?”(አ.መ.ት)
ሀጢአት ሰሪውን ያጎሳቁላል
ሐጢአትን የሚያደርግ ሰው እግዚአብሔርን ይበድላል እራሱንም ደግሞ ይጎዳል
“8. ልትኖሩባት በመጣች ሁባት በግብፅ ምድር ለሌሎች አማልክት በማጠን፣ እጆቻችሁ ባበጇቸው ነገሮች ለምን ታስቈጡኛላችሁ? በምድር ባሉት ሕዝቦች ሁሉ ዘንድ የርግማንና የመዘባበቻ ምልክት ለመሆን ራሳችሁን ታጠፋላችሁን?”(አ.መ.ት)
የርግማንና የመዘባበቻ ምልክት ለመሆን ራሳችሁን ታጠፋላችሁን?
ሐጢአት የርግማንና የመዘባበቻ ምልክት ያደርጋል
ከቁጥር 11-14 እግዚአብሔር ሊፈርድባቸው እንደቆረጠ ይናገራል
“13. ኢየሩሳሌምን እንደቀጣሁ፣ በግብፅ የሚኖሩትን በሰይፍ፣ በራብና በቸነፈር እቀጣለሁ፤”(አ.መ.ት)
ከ 15-19 የህዝቡ ማመፅና በሀጢአት መፅናት ያሳየናል
ከዚህ ሁሉ ነገር በኋላ ምንም አልተማሩም ጭራሽ አንሰማህም የፈለግነውን ነገር እንዳደርጋለን ይሉታል
ከእግዚአብሔር ቃል ይልቅ ለራሳቸው ስሜት መታዘዝን መረጡ
በእኛ ህይወት ውስጥ ስሜታችን የመጨረሻው ባለስልጣን ሊሆን አይገባም::
የመጨረሻው ባለስልጣን የእግዚአብሔር ቃል ነው
“19. ሴቶቹም፣ “ለሰማይዋ ንግሥት በምናጥንበትና የመጠጥ ቍርባን በምናፈስበት ጊዜ፣ በምስሏ ዕንጐቻ ስንጋግርና የመጠጥ ቍርባን ስናፈስላት ባሎቻችን አያውቁም ነበርን?” አሉ።”(አ.መ.ት)
ባሎቻችን አያውቁም ነበርን ይላሉ የፀሀይ ንግስት የምትባለዋን በብዛት የሚያመልኳት ሴቶች ነበሩ ይሄንን ያደርገነው በባሎቻችን ፈቃድ ነው ይላሉ
የባሎቻቸውን ፈቃድ ማግኘታቸው በትክክለኛው መንገድ እየሄዱ እንደሆነ እንዲሰማቸው አድርጓቸዋል
ከቁጥር 20-22 የኤርምያስን መልስ እናያለን
“22. እግዚአብሔር ክፉ አድራጎታችሁንና አስጸያፊ ተግባራችሁን ሊታገሥ ባለመቻሉ፣ ዛሬ እንደሆነው ምድራችሁ የርግማን ምልክት፣ ሰው የማይኖርበት ባዶ ምድረ በዳ ሆኖአል።”(አ.መ.ት)
ከ 23-30 የመጨረሻውን ፍርድ ያሳየናል
“25. የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ እናንተና ሚስቶቻችሁ፣ ‘ለሰማይዋ ንግሥት ለማጠንና የመጠጥ ቍርባን ለማፍሰስ የተሳልነውን ስእለታችንን በእርግጥ እንፈጽማለን’ ብላችሁ የገባችሁትን ቃል በተግባር አሳይታችኋል።’“እንግዲያውስ ወደ ኋላ አትበሉ፤ ቃል የገባችሁትን፤ ስእለታችሁንም ፈጽሙ።”(አ.መ.ት)
እናንተም የምታደርጉትን አድርጉ እግዚአብሔርም የሚያደርገውን ያደርጋል እያላቸው ነው
“28. ከሰይፍ አምልጠው፣ ከግብፅ ወደ ይሁዳ ምድር የሚመለሱት በጣም ጥቂት ሰዎች ይሆናሉ። በግብፅ ምድር ለመኖር የመጡት የይሁዳ ቅሬታ ሁሉ፣ ከእኔ ወይም ከእነርሱ የማንኛችን ቃል እንደሚጸና ያውቃሉ።”(አ.መ.ት)
እግዚአብሔር በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ብንሆን ያያል ይፈርዳል ከእርሱ ጋር መስማማት ይሻላል
ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ 45
ለባሮክ የተነገረ መልእክት
ባሮክ ማለት የኤርምያስ ረዳት በቅርብ አብሮት የሚያገለግል ሰው ነው
በኤርምያስ አፍ የተነገረን ትንቢት የሚፅፍ ሰው ነበረ
ባሮክ ከሚታዩትና ከሚታወቁት አገልጋዮች ጀርባ የሚያገለግሉ አብሮ ያሉ አገልጋዮች እንዳሉ ማሳያ ነው
ባሮክ የስሙ ትርጉም የተባረከ ማለት ነው
የኤርምያስ መፅሀፍ ላይ 25 ጊዜ ስሙ ተጠቅሷል
መጽሐፍ ቅዱስ ቅደመ ተከተሉን ጠብቆ የተቀመጠ መጽሐፍ ሳይሆን ለንባብ እንዲመች ተደርጎ የተደረደረ መጽሐፍ ነው ምዕራፍ 44 ለንባብ እንዲመች ተደርጎ እዚህ ቦታ ላይ ተፃፈ እንጂ ታሪኩ የሚቀጥለው ከምዕራፍ 36 ነው
1. በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ልጅ በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት በአራተኛው ዓመት፣ ኤርምያስ በቃል የነገረውን ባሮክ በብራና ላይ ከጻፈ በኋላ፣ ነቢዩ ኤርምያስ ለኔርያ ልጅ ለባሮክ የተናገረው ይህ ነው፤(አ.መ.ት)
ኢዮአቄም ንጉስ የነበረው ኢየሩሳሌም ከመፍረሷ ከ 21 አመት በፊት ነበረ ለዚህ ነው ይሄ ምዕራፍ ከምዕራፍ 36 ቀጥሎ ያለ ታሪክ ነው የተባለው
ኤርምያስ 36
1.
323ኛ ቀን
በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና::
ዛሬ የምናነበው ክፍል ወደ ሮሜ ሰዎች ምዕራፍ 10 - 12
የዩቱብ የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች ታገኛላችሁ👇
YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow
YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316
TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu
TIKTOK#2:- tiktok.com/nikodimoschrstiancenter
TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
ኤርሚያስ ከማህፀን የተመረጠና በሆድ ሳይሰራ ነቢይ ተደርጎ የተቀባ የእግዚአብሔር ሰው ሆኖ ሳለ የእግዚአብሔርን ድምፅ ለመስማት 10 ቀናትን መጠበቁ ለትምህርታችን ተፅፏል
9-12 እግዚአብሔር እዚህችው ምድር ላይ ተቀመጡ ብሎ መለሰላቸው
የሰው ጥበብ ማምለጥ ነው የእግዚአብሔር ጥበብ ማሳረፍ ነው
ከ 13-18 ማስጠንቀቂያ
“16 የምትፈሩት ሰይፍ በዚያ በግብጽ ምድር ያገኛችኋል፥ ስለ እርሱም የምትደነግጡበት ራብ በዚያ በግብጽ ይደርስባቸኋል፥ በዚያም ትሞታላችሁ።”
ችግራቸው መንፈሳዊ ስለሆነ ስፍራ በመቀየር ሊያመልጡ አይችሉም ቢሄዱም ችግሩ ተከትሏቸው ይሄዳል
መንፈሳዊ ችግር የሚፈታው እግዚአብሔርን በመታዘዝ ነው
ትንቢተ ኢሳይያስ 31
1 ስለ እርዳታ ወደ ግብጽ ለሚወርዱ በፈረሶችም ለሚደገፉ፥ ስለ ብዛታቸውም በሰረገሎች፥ እጅግ ብርቱዎችም ስለ ሆኑ በፈረሰኞች ለሚታመኑ፥ ወደ እስራኤልም ቅዱስ ለማይመለከቱ እግዚአብሔርንም ለማይፈልጉ ወዮላቸው!
ፍርሀት ሲከበን ድሮ ወደ ምናውቀው ዘዴያችን እንዳንመለስ መጠንቀቅ አለብን
“18. የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ‘ቍጣዬና መዓቴ በኢየሩሳሌም በሚኖሩት ሁሉ ላይ እንደ ፈሰሰ፣ እንዲሁ ወደ ግብፅ በገባችሁ ጊዜ መዓቴ በእናንተ ላይ ይፈሳል፤ እናንተም የመነቀፊያና የድንጋጤ፣ የመረገሚያና የመዘባበቻ ምልክት ትሆናላችሁ፤ ይህንም ስፍራ ዳግመኛ አታዩም።’”(አ.መ.ት)
ጉዳዩ የመሄድም የመቀመጥም ሳይሆን እግዚአብሔርን የመታዘዝና ያለመታዘዝ ነው
ሂዱ ስላቸው የተቀመጡት ላይ ያመጣሁትን መአት አትሂዱ ስላችሁ በምትሄዱትም ላይ አፈሰዋለሁ!
19-22 የኤርሚያስ ወቀሳ
“20. ‘ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ጸልይልን፤ እርሱ ያለህን ሁሉ ንገረን፤ እኛም እንታዘዛለን’ ብላችሁ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር በላካችሁኝ ጊዜ ሕይወታችሁን የሚያጠፋ ስሕተት ፈጸማችሁ።”(አ.መ.ት)
እግዚአብሔር የሚፈልገው ፍቃዱን ጠይቀው የማያደርጓትን ሳይሆን ሰምተው የሚታዘዙትን ነው
የማርቆስ ወንጌል 10
17 እርሱም በመንገድ ሲወጣ አንድ ሰው ወደ እርሱ ሮጦ ተንበረከከለትና። ቸር መምህር ሆይ፥ የዘላለም ሕይወትን እወርስ ዘንድ ምን ላድርግ? ብሎ ጠየቀው።
18 ኢየሱስም። ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።
19 ትእዛዛትን ታውቃለህ፤ አታመንዝር፥ አትግደል፥ አትስረቅ፥ በሐሰት አትመስክር፥ አታታልል፥ አባትህንና እናትህን አክብር አለው።
20 እርሱም መልሶ። መምህር ሆይ፥ ይህን ሁሉ ከሕፃንነቴ ጀምሬ ጠብቄአለሁ አለው።
21 ኢየሱስም ወደ እርሱ ተመልክቶ ወደደውና። አንድ ነገር ጐደለህ፤ ሂድ፥ ያለህን ሁሉ ሽጠህ ለድሆች ስጥ፥ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ፥ መስቀሉንም ተሸክመህ ና፥ ተከተለኝ አለው።
22 ነገር ግን ስለዚህ ነገር ፊቱ ጠቈረ፥ ብዙ ንብረት ነበረውና እያዘነም ሄደ።
ምን እንማር ?
1. የእግዚአብሔርን ፈቃድ መፈለግ(መጠየቅ) ያለብን ለመታዘዝ መሆን አለበት
2. የእግዚአብሔርን ፈቃድ ስንፈልግ በትዕግስት ይሁን እንጂ በችኮላ አይሁን
3. የትኛውም ውሳኔያችን የፍርሀት ተፅዕኖ እንዳይኖርበት እንጠንቀቅ
4. ስንፈራ ወደ ድሮ ዘዴዎቻችን እንዳንመለስ ፈጥነን ወደ እግዚአብሔር እንሽሽ
ትንቢተ ኤርሚያስ ምዕራፍ 40-42
ከኢየሩሳሌም መያዝ በኋላ የኤርሚያስ ነፃነትና የጎዶልያስ መገደል
ከ 1-6 የኤርሚያስ ነፃ መውጣት
ኤርሚያስ በምርኮኞች መካከል በሰንሰለት ታስሮ ተገኘ
ኤርሚያስ የእግዚአብሔርን ቃል በታማኝነት ከመናገር ውጪ ምንም የበደለው በደል የለም ግን በዚህ ሁኔታ ተገኘ
በወደቀው አለም ስንኖር ሁሉን ነገር በስሌት ማስቀመጥ (ይህ ስለሆነ ነው ይህ የሆነው) ማለት አንችልም እግዘኢብሔር ግን በጊዜው ለታማኞቹ ይፈርዳልና ኤርሚያስን አስፈታው
“3. አሁንም እግዚአብሔር አመጣው፤ እንደ ተናገረውም አደረገ። ይህ ሁሉ የሆነው እናንተ በእግዚአብሔር ላይ ኀጢአት ስለ ሠራችሁና እርሱን ስላልታዘዛችሁ ነው።”(አ.መ.ት)
አንዳንዴ በቤቱ ካሉት ሰዎች ይልቅ በውጭ ያሉቱ መንፈሳዊውን ችግር ያስተውላሉ
7-12 ጎዶልያስ በኢየሩሳሌም በቀሩት ትሩፋን ላይ ተሾመ የሾመውም የባቢሎን ንጉስ ነበረ
በምድሪቱ እንቀመጥ ፡ ለባቢሎን መንግስት እንገዛ ፡ ምርት እያመረትን ህይወትን እናስቀጥል አላቸው ፡ አበረታታቸውም
“12. ሁላቸውም ከተበታተኑበት አገር ሁሉ ወደ ይሁዳ ምድር ተመለሱ፤ በምጽጳ ወደ ሚኖረውም ወደ ጎዶልያስ መጡ፤ ወይንና የበጋ ፍሬም በብዛት አከማቹ።” (አ.መ.ት)
እግዚአብሔር ከፍርድ በኋላም ቅሬታዎቹን እንደሚጠብቅ ያሳያል
ከ 13-16 ዮሀናን አመፅን ማጋለጡ
የአሞናውያን ንጉስ በአሊስ እስማኤልን ልኮ እያሴረ ነው ብሎ ዮሐናን ቢነግረውም ጎዶልያስ አላመነውም አልተጠነቀቀም
እግዚአብሔር አንድን ሴራ እንድንሰማ ሲያደርግ እንድንጠነቀቅ እና እንድንፀልይ ሊሆን እንደሚችል ማሰብ ተገቢ ነው
የሰማነውን ሁሉ እናምናለን ማለት ሳይሆን እግዚአብሔር ለምን እንድንሰማ ፈቀደ ? ብለን ተገቢውን ምላሽ መስጠት አለብን
“15 የቃሬያም ልጅ ዮሐናን። እባክህ፥ ልሂድ፤ ማንም ሳያውቅ የናታንያን ልጅ እስማኤልን ልግደለው፤ ወደ አንተ የተሰበሰቡ አይሁድ ሁሉ እንዲበተኑ የይሁዳም ቅሬታ እንዲጠፋ ነፍስህን ስለ ምን ይገድላል? ብሎ በምጽጳ በቆይታ ለጎዶልያስ ተናገረ።”
ጠላት መሪዎችን ሲያጠቃ ከግለሰቡ የዘለለ አላማ ቀርፆ ነው የሚያጠቃው
“የመጡት እንዲበተኑ…….የቀሩት እንዲጠፉ”
በመሪዎች ላይ የሚሰነዘር የጠላት ጥቃት አላማውም ስልቱም ከፍ ያለ ስለሆነ ለመሪዎች ልንራራና አጥብቀን ልንፀልይ ይገባል
ምን እንማር ?
1. እግዚአብሔር ቅሬታዎቹን (ትሩፋኑን) ይጠብቃል
2. ታማኝ አገልጋዮች መከራ ሊቀበሉ ይችላሉ ፡ እግዚአብሔር ለእነርሱ የሚፈርድበት ቀን መምጣቱ ግን አይቀርም
3. ይህንን ወሬ ለምን ሰማሁ? ይህንን ህልም ለምን አየሁ? በዚህ ጊዜ እዚህ ቦታ ለምን ተገኘሁ? ብለን እግዚአብሔርን እንጠይቅ
4. ለመሪዎች የሚራራና የሚማልድ ልብ ይኑረን
ትንቢተ ኤርሚያስ ምዕራፍ 41
የጎዶልያስ መገደልና ወደ ግብፅ የተደረገ ሽሽት
ከ 1-3 እስማኤል ጎዶልያስን ገደለው
እስማኤል ጎዶልያስን ከመግደሉ በፊት በማዕድ አብሮት ተቀምጦ ነበር
ይህ ሁኔታ ይሁዳ ጌታን ከማዕድ ህብረት በኋላ እንደሚክደውና አሳልፎ እንደሚሰጠው በሩቅ ያመላክተናል
ጠላት መከዳታችን በጣም እንዲያሳምመን ስለሚፈልግ የእኔ ባልነውና ወደ ማዕዳችን ባቀረብነው ሰው ይጠቀማል ፡
ጎዶልያስ የተሰጠውን ማስጠንቀቂያ ችላ ብሎ ተታሎ ተገደለ ኢየሱስ ግን ይሁዳ ልብ ውስጥ ያለውን እያወቀ “ልታደርገው ያለህን ፈጥነህ አድርግ” በማለት ነፍሱን በፈቃዱ አኖረ
4-10 የእህል ቁርባንና እጣን ይዘው የመጡት 80 ሰዎች
“6. የናታንያ ልጅ እስማኤል ሊገናኛቸው እያለቀሰ ከምጽጳ ወጣ፣ ሲያገኛቸውም፣ “ወደ አኪቃም ልጅ ወደ ጎዶልያስ ኑቃ አላቸው።”(አ.መ.ት)
የጠላትን አቀራራቡን እንጂ የልቡን ሀሳብ ለይተው ማወቅ የተሳናቸው መስዋዕት አቅራቢዎች በእስማኤል እጅ ተገደሉ
በይሁዳ ላይ የተላለፈው የእግዚአብሔር ፍርድ በወቅቱ ያሉትን ሰዎች ወደ ንስሀ እንዲመጡና ዳግመኛ እንዳያምፁ አላደረጋቸውም
ወደ ሮሜ ሰዎች 2
4 ወይስ የእግዚአብሔር ቸርነት ወደ ንስሐ እንዲመራህ ሳታውቅ የቸርነቱንና የመቻሉን የትዕግሥቱንም ባለጠግነት ትንቃለህን?
ሰዎች በንስሀ እንዲመለሱ ማወጅ ያለብን ፍርድን ሳይሆን የእግዚአብሔርን ቸርነት ነው
11-15 ዮሐናን ቅሬታዎችን መታደጉ
ዮሐናን የሰጠው መረጃ ውድቅ በመደረጉ አኩርፎ ዳር አልቆመም ወይንም እርሱን አልሰማ ብለው በገቡበት ችግር ላይ አልተሳለቀም ፡ አሁንም የመፍትሄ አካል ለመሆን ይተጋል
ከ 16-18 ወደ ግብፅ የተደረገ ሽሽት
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ወደ ግብፅ የመመለስ ተምሳሌትነት
- በሰው ጥንካሬና ብርታት ላይ መተማመን
- ወደ ቀደመው ባርነት መመለስ
- በእግዚአብሔር ፈንታ አለምን ማመን ማለት ነው
ኢሳይያስ 31
1. ወደ እስራኤል ቅዱስ ለማይመለከቱ፣ ከእግዚአብሔርም ርዳታን ለማይሹ፣ነገር ግን፤ ለርዳታ ብለው ወደ ግብፅ ለሚወርዱ፣በፈረሶች ለሚታመኑ፣በሠረገሎቻቸው ብዛት፣በፈረሶቻቸውም ታላቅ ብርታት ለሚመኩ ወዮላቸው! (አ.መ.ት)
ፍርሀት ከእግዚአብሔር ይልቅ በሚታዩ ነገሮች እንድንታመን የመገፋፋት ባህሪ አለው
ምን እንማር ?
1. ጠላት ከመከዳታችን በላይ ከከዱን ሰዎች ጋር ያለንን ቅርበት እያሳየ ሊጎዳን እንደሚፈልግ እንወቅ
2. ሰዎችን ወደ ንስሀ የሚጠራው ፍርድ ሳይሆን የእግዚአብሔር ምህረትና ቸርነት ነው
3. እግዚአብሔር አኩራፊዎችንና እኔ ያልኩት ካልሆነ ባዮችን በቀጣይነት አይጠቀምም
4. ፍርሀት ከእግዚአብሔር ይልቅ በሚታዩ ነገሮች እንድንታመን የማድረግ ጠባይ ስላለው ስንፈራ እንጠንቀቅ
ትንቢተ ኤርሚያስ ምዕራፍ 42
ለመታዘዝ ዝግጁ ባልሆነ ልብ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማወቅ መፈለግ የሚያስከፍለው ዋጋ
ከ 1-6 ኤርሚያስ እንዲፀልይላቸውና የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንዲጠይቅላቸው ጠየቁት
“6. አምላካችንን እግዚአብሔርን በመታዘዝ መልካም ይሆንልን ዘንድ ነገሩ ቢስ ማማንም ባይስማማንም፣ አንተን ወደ እርሱ የምንልክህን አምላካችንን እግዚአብሔርን እንታዘዛለን።” (አ.መ.ት)
በአንደበታቸው “የእግዚአብሔርን ፈቃድ ጠይቀህ አሳውቀንና የተናገረንን ሁሉ እንታዘዛለን” ቢሉም በልባቸው ግን መስማት የሚፈልጉት የገዛ መሻታቸውን ነው
አንዳንድ ጊዜ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማወቅ በሚል እየፀለይን እውነተኛው መሻታችን ግን የኛን ሀሳብ እንዲያፀድቅልን ነው የሚሆነው
የሉቃስ ወንጌል 6
46 ስለ ምን። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ ትሉኛላችሁ፥ የምለውንም አታደርጉም?
የያዕቆብ መልእክት 1
22 ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።
የእግዚአብሔርን ፈቃድ አውቀን ከማናደርጋት ባናውቃት ይሻለናል
የሉቃስ ወንጌል 12
47 የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ያ ባሪያ እጅግ ይገረፋል፤
48 ያላወቀ ግን መገረፍ የሚገባውንም ያደረገ ጥቂት ይገረፋል። ብዙም ከተሰጠው ሰው ሁሉ ከእርሱ ብዙ ይፈለግበታል፥ ብዙ አደራም ከተሰጠው ከእርሱ አብዝተው ይሹበታል።
የያዕቆብ መልእክት 4
17 እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው።
እውቀት የሚሰጠው ከሃላፊነት ጋር ነው
“7. ከዐሥር ቀን በኋላ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ መጣ።” (አ.መ.ት)
322ኛ ቀን
በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና::
ዛሬ የምናነበው ክፍል ወደ ሮሜ ሰዎች ምዕራፍ 7 - 9
የዩቱብ የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች ታገኛላችሁ👇
YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow
YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316
TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu
TIKTOK#2:- tiktok.com/nikodimoschrstiancenter
TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
321ኛ ቀን
በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና::
ዛሬ የምናነበው ክፍል ወደ ሮሜ ሰዎች ምዕራፍ 4 - 6
የዩቱብ የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች ታገኛላችሁ👇
YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow
YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316
TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu
TIKTOK#2:- tiktok.com/nikodimoschrstiancenter
TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
320ኛ ቀን
በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና::
ዛሬ የምናነበው ክፍል ወደ ሮሜ ሰዎች ምዕራፍ 1 - 3
የዩቱብ የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች ታገኛላችሁ👇
YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow
YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316
TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu
TIKTOK#2:- tiktok.com/nikodimoschrstiancenter
TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
ይሄ ሰው እንደዚህ ወላዋይ የሆነው ለእግዚአብሔር ድምጽ የሚታዘዝ ልብ ስላልነበረው ነው
“12. ኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ ኤርምያስን፣ “ይህን ያረጀ ጨርቅና ያረጀ ልብስ ገመዱ እንዳይከረክርህ በብብትህ ሥር አድርገው አለው፤ ኤርምያስም እንዲሁ አደረገ፤”(አ.መ.ት)
እግዚአብሔር ስለዚህ ስራው አቤሜሌክን ኢየሩሳሌም በሰይፍ ስትጠፋ አንተ ምንም አትሆንም ብሎ ይሸልመዋል
“14. ንጉሡ ሴዴቅያስ ወደ ነቢዩ ወደ ኤርምያስ ልኮ ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሦስተኛው በር አስመጣውና፤ “አንድ ነገር እጠይቅሃለሁ፤ ምንም አትሸሽገኝ” አለው።
15. ኤርምያስም ሴዴቅያስን፣ “መልስ ብሰጥህ አትገድለኝምን? ምክር ብሰጥህ አትሰማኝም” አለው።”(አ.መ.ት)
ንጉሱ ምሎ ኤርምያስን ይጠይቃል
ኤርምያስ ንጉሱ ጠንካራ አለመሆኑን ያውቃል የመጣ ሰው ሁሉ ሀሳቡን እንደሚያስቀይረው ያውቃል የእግዚአብሔር ሀሳብ ከመናገር ግን አለተቆጠበም
ከ 19-24ኤርምያስና ንጉሱ ያደረጉትን ንግግር ያሳየናል
እጅ ብትሰጥ ትተርፋለህ ካልሆነ ግን ከተማዋም ትቃጠላለች አንተም አትርፍም ሚስትህም ልጆችህም ይማረካሉ ብሎ ይነግረዋል
ለእግዚአብሔር ድምፅ መታዘዝ ካላስፈላጊ ጥፋት ያድነናል
ከቁጥር 25-28 ንጉሱ ሚስጥር እንዲጠብቅ ኤርምያስን ያዘዋል
ኤርምያስ ከእስር ቤት እየተጠራ ንጉሱን የእግዚአብሔርን ድምፅ እንዲታዘዝ ይለምነዋል
“20. ኤርምያስም እንዲህ አለው፤ “ዐሳልፈው አይሰጡህም፣ ብቻ የምነግርህን የእግዚአብሔር ቃል ታዘዝ፤ መልካም ይሆንልሃል፤ ሕይወትህም ትተርፋለች።”(አ.መ.ት)
ትንቢተ ኤርሚያስ ምዕራፍ 39
የኢየሩሳሌም መውደቅ
እግዚአብሔር ከዚህ በፊት ሲናገር የነበራቸውን ነገሮች የሚፈፅምበት ምዕራፍ ነው
“1. ኢየሩሳሌም የተያዘችው እንዲህ ነበር፤ በይሁዳ ንጉሥ በሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት በዘጠነኛው ዓመት በዐሥረኛው ወር፣ የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ሰራዊቱን ሁሉ አሰልፎ በመምጣት ኢየሩሳሌምን ከበባት።
2. በሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥት በዐሥራ አንደኛው ዓመት በአራተኛው ወር፣ በወሩም በዘጠነኛው ቀን የከተማዪቱ ቅጥር ተሰበረ።”(አ.መ.ት)
በድሮ ጊዜ ትልልቅ ግንቦችን ይሰሩና ከተማይቱ በሮች እንዲኖሯት ይደረጋል
ቅጥር ተከበበ ማለት ሰው መውጣትም መግባትም አይችልም ማለት ነው
ምግብ አይኖርም ፡ ንግድ አይኖርም እንቅስቃሴ ሁሉ ይቆማል ማለት ነው
ይሄ ሁኔታ ታድያ በሰቆቃው ኤርምያስ ላይ ኢየሩሳሌም ምን ያህል አስከፊ ነገር እንዳሳለፈች ተተርኳል
የተፈፀሙ የእግዚአብሔር ትንቢቶች
1 የግብፅ ሰራዊት እስራኤልን ሊረዱ እንደወጡና ነገር ግን እንዳላዳኗቸው እናያለን
2 ሐሰተኛ ነቢያቶች የተናገሩት ስህተት ሆኖ ሲገኝ እናያለን
3 ቅጥራቸው ፈርሶ ወታደሮቹ ገቡ
4 ሴዴቅያስም ተፈረደበት
ከእግዚአብሔር ፍርድ የሚያመልጥ ሰው እንደሌለ ይሔ ቁጥር ያስተምረናል
የሴዴቅያስ አለመታዘዝ ለብዙዎቹ የጥፋት ምክንያት ሲሆን እናያለን
ሕዝቅኤል 12
13. መረቤን በእርሱ ላይ እዘረጋለሁ፤ በወጥመዴም ይያዛል፤ ወደ ከለዳውያን ምድር ወደ ባቢሎን አመጣዋለሁ፤ ነገር ግን እርሷን ሳያያት በዚያ ይሞታል።(አ.መ.ት)
ረጅም ጊዜ ወስደው የገነቡት ከተማቸውና ቤተመቅደሱ ፈረሰ ባለመታዘዛቸው ምክንያት
“11. የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በክብር ዘበኞቹ አዛዥ በናቡዘረዳን በኩል ስለ ኤርምያስ እንዲህ የሚል ትእዛዝ ሰጠ፤
12. “ውሰደውና እንክብካቤ አድርግለት፤ የሚፈልገውን ነገር ፈጽምለት እንጂ አትጒዳው።”(አ.መ.ት)
እግዚአብሔር በዚህ ሁኔታ ውስጥ ለኤርምያስ እንክብካቤን ሲያድርግ እናያለን
ኤርምያስ እውነትን በመናገሩ ለዚህ ሁሉ ጊዜ ታስሮ ነበር አሁን ግን እግዚአብሔር ሰው ሲያስነሳለት ያሳየናል
“14. ልከው ኤርምያስን ከዘበኞች አደባባይ አስወጡት፤ የሳፋን ልጅ የአኪቃም ልጅ ጎዶልያስ ወደ ቤቱ እንዲወስደው በዐደራ ሰጡት፤ ኤርምያስም በራሱ ሕዝብ መካከል ተቀመጠ።”(አ.መ.ት)
እንዴት እንደሆነ በማይታወቅ ሁኔታ እግዚአብሔር ለኤርምያስ ሞገስ ሰጠው ናቡከደነፆር እንዲንከባከበው አደረገው
“16. “ሂድና ለኢትዮጵያዊው አቤሜሌክ እንዲህ በለው፤ ‘የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ እድገት ሳይሆን ጥፋት በማምጣት በዚህች ከተማ ላይ ቃሌን እፈጽማለሁ፤ በዚያ ጊዜ በዐይንህ እያየህ ይህ ይፈጸማል።
17. አንተን ግን በዚያ ቀን አድንሃለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር፤ ለምትፈራቸው ሰዎች ዐልፈህ አትሰጥም።
18. እታደግሃለሁ፤ በእኔ ታምነሃልና በሕይወት ታመልጣለህ እንጂ በሰይፍ አትወድቅም፤ ይላል እግዚአብሔር።’ ”(አ.መ.ት)
እግዚአብሔር የሰው ውለታ ባለእዳ አይደለም አቤሜሌክ ለኤርምያስ ባደረገው መልካም ነገር ሲክሰው እናያለን
ትንቢተ ኤርሚያስ ምዕራፍ 37-39
የኤርምያስ መታሰር
የሴዴቅያስን መንገስ በመናገር ክፍሉ ይጀምራል
እግዚአብሔር ነገስታቱን ለራሱ አላማ እንደሚጠቀማቸው ተመልክተናል
ሴዴቅያስ የመጨረሻው የኢየሩሳሌም ንጉስ ነው
የሴዴቅያስ ወደ ንግስና መምጣት ምዕራፍ 36 ላይ ለኢዮአቄም ለተነገረው ትንቢት ማስፈፀሚያ ነው
እግዚአብሔር የተናገረውን ሲፈፅም እናያለን
“2. ነገር ግን እርሱም ሆነ መኳንንቱ የምድሪቱም ሕዝብ በነቢዩ በኤርምያስ አማካይነት የተነገረውን የእግዚአብሔርን ቃል አልሰሙም።(አ.መ.ት)
ሴዴቅያስ ነገሰ ብሎ ሳይጨርስ እግዚአብሔርን አለመስማቱን አያይዞ ክፍሉ ያሳየናል
የእግዚአብሔር ድምፅ መቷል የሚሰማ ግን አልነበረም
ንጉሱም የእግዚአብሔርን ድምፅ አልሰማም ፡ መኳንንቶቹም አልሰሙም ፡ ህዝቡም ጭምር ለመስማት ፍቃደኛ አይደሉም
የእግዚአብሔር ድምጽ የይሁዳ ህዝብ ፈጽመው በባቢሎን እንደሚማረኩና ለዚህ ለእግዚአብሔር ውሳኔ ደግሞ እራሳቸውን እንዲያስገዙ የሚያሳስብ መልዕክት ነበር
“3. ንጉሡ ሴዴቅያስም፣ “ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ስለ እኛ ጸልይ” በማለት የሰሌምያን ልጅ ዮካልንና ካህኑን የመዕሤያን ልጅ ሶፎንያስን ወደ ነቢዩ ወደ ኤርምያስ ላከ።(አ.መ.ት)
ንጉስ ሴዴቅያስ የእግዚአብሔርን ምሪት ይፈልጋል ፀልይልን ብሎ ወደ ኤርምያስ ይልካል ነገር ግን መታዘዝ ደግሞ አይፈልግም
የሚፈልጉት ፀሎት ለውጊያ ሄደው የነበሩት የባቢሎን ወታደሮች በዚያው እንዲቀሩ የሚል ነው
እግዚአብሔር የኛ ጉዳይ አስፈፃሚ አይደለም
በፀሎት የሚቀየር አጀንዳ አይደለም የያዙት መታዘዝ ስለማይፈልጉ ያደረጉት ፀሎት ነው
የኤርምያስና የንጉሱ እንዲሁም የህዝቡ ልዩነት
እግዚአብሔር ለሁሉም ድምፁን ይልካለቸዋል ነገር ግን ኤርምያስ ቶሎ ቶሎ ስለሚቀበልና ስለሚታዘዝ እግዚአብሔርም ደጋግሞ ሲናገረው እናያለን
እግዚአብሔር በግልጽ ደግሞ ለህዝቡ ያመጣላቸው መልዕክት በባቢሎን ምርኮ ስር ትወድቃላችሁ ለሱም ከተገዛችሁ ትባረካላችሁ ከ 70 አመት በኋላ ትመለሳላችሁ የሚል ነው ነገር ባለመታዘዛቸው ምክንያት ደጋግሞ ሲያጠፉ እናያቸዋለን
ከኤርምያስ ህይወት የምንማረው ነገር
ኤርምያስ ያለ እግዚአብሔር ድምፅ አይንቀሳቀስ
የሰማውን ድምጽ ደግሞ ይታዘዛል
“8. ባቢሎናውያንም ተመልሰው ይህችን ከተማ ይወጓታል፤ ይዘውም ያቃጥሏታል።’
9. “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ባቢሎናውያን በእርግጥ ትተውን ይሄዳሉ’ ብላችሁ አታስቡ፤ አይሄዱምና ራሳችሁን አታታሉ።(አ.መ.ት)
አይሁዳውያን ራሳቸውን ከእግዚአብሔር ፍርድ እንዳመለጡ ቆጥረው ይሳሳቱ ስለ ነበረ እግዚአብሔር ራሳችሁን አታታሉ ይላቸዋል
ከእግዚአብሔር ድምጽ ውጪ መስማት ራስን ማታለል ነው
ከ 10-14 ኤርምያስ ድርሻውን ለመካፈል ወደ ትውልድ ሀገሩ ሊሄድ ሲነሳ እናየዋለን
ኤርምያስ 32
6. ኤርምያስም የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ አለ፦
7. “የአጎትህ የሰሎም ልጅ አናምኤል ወደ አንተ መጥቶ፣ ‘የመቤዠት መብት የአንተ ስለ ሆነ፣ በዓናቶት ያለውን መሬቴን ግዛኝ’ ይልሃል።”(አ.መ.ት)
“13. ነገር ግን ወደ ብንያም በር ሲደርስ፣ የዘበኞች አለቃ የነበረው የሐናንያ ልጅ የሴሌምያ ልጅ የሪያ የተባለው፣ “ከድተህ ወደ ባቢሎናውያን ልትሄድ ነው!” በማለት ያዘው።(አ.መ.ት)
ኤርምያስን ያዙት
“15. መኳንንቱም እጅግ ተቈጥተው ኤርምያስን ደበደቡት፤ የግዞት ቤትም አድርገውት በነበረው፤ በጸሓፊው በዮናታን ቤት አሰሩት።”(አ.መ.ት)
ትክክለኛው የእግዚአብሔርን ድምጽ ያመጣው ንጹሁ ኤርምያስ ታስሮ ተደበደበ
ኤርምያስ ያለምንም ፍርሀት ከእግዚአብሔር የሰማውን ድምጽ በቀጥታ የተናገረ ሰው ነበር
ሐሰተኞቹ በሰላም ተቀምጠው እውነተኛው ነቢይ ታሰረ
አንዳንዱ ነገር እኛ እንዲህ ነው ብለን ልንረዳው አንችልም ምክንያቱም ጉዳዩ ሲታይ ሚዛናዊ አይመስልም ነገር ግን እግዚአብሔር ለሁሉም ነገር ዋጋ ይሰጣል
ባይገባንም ባንረዳውም ከእግዚአብሔር ጋር መቆም ግን ያዋጣናል
“17. ከዚያም በኋላ ንጉሡ ሴዴቅያስ ላከበትና ወደ ቤተ መንግሥት አስመጣው፤ ለብቻውም ወስዶ፣ “ከእግዚአብሔር የመጣ ቃል አለህ?” በማለት ጠየቀው።ኤርምያስም፣ “አዎን አለ፤ ለባቢሎን ንጉሥ ዐልፈህ ትሰጣለህ” አለው።(አ.መ.ት)
ኤርምያስ ከረጅም ጊዜ እስር በኋላ ጥያቄ ይጠየቃል
“ከእግዚአብሔር የመጣ ቃል አለህ?”
ኤርምያስ ቢታሰርም አሁንም ከእግዚአብሔር የሚመጣ ድምጽ አለው
እግዚአብሔርም የሚሰማበት አቅም አለው ፡ ከእግዚአብሔር የሰማውንም ነገር በድፍረት የመናገር አቅም ነበረው
ኤርምያስ ስለመታሰሩና ስለደረሰበት ነገር እግዚአብሔርን ሲወቅስ አናይም ንጉስንና ጠባቂዎቹን ይጠይቃል እንጂ
ኤርምያስ ከእግዚአብሔር የመጣውን ድምጽ ለመናገር ምንም አይፈራም ቀጥታ ሲናገር እናየዋለን ነገር ግን ስለራሱ ደግሞ ንጉሱን ወደ እስር ቤቱ እንዳይመልሰው ሲለምን እናያለን
መከራ ስለበዛ የእግዚአብሔር መልዕክት አይቀየርም የሚለውን ከኤርምያስ ህይወት እንማራለን
ትንቢተ ኤርሚያስ ምዕራፍ 38
ኤርምያስ በውሃ ጒድጓድ ውስጥ ተጣለ
“1. ኤርምያስ ለሕዝቡ የተናገረውን ቃል የማታን ልጅ ሰፋጥያስ፣ የጳስኮር ልጅ ጎዶልያስ፣ የሰሌምያ ልጅ ዮካል እንዲሁም የመልክያ ልጅ ጳስኮር ሰሙ፤ ቃሉም እንዲህ የሚል ነበር፦”(አ.መ.ት)
ኤርምያስ በዚህም ሁኔታ ውስጥ ሆኖ የእግዚአብሔር መልዕክት ይሰማል ይናገራል
“2. “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘በዚህች ከተማ የሚቀር ሁሉ በሰይፍ፣ በራብ ወይም በቸነፈር ይሞታል፤ ይህን ስፍራ ለቆ ወደ ባቢሎናውያን የሚሄድ ሁሉ ይተርፋል፤ ያመልጣል፤ በሕይወትም ይኖራል።’”(አ.መ.ት)
አሁንም የመጣው የእግዚአብሔር ድምጽ ተስፋ እንዳለው ሲናገራቸው እንመለከታለን
“4. መኳንንቱም ንጉሡን እንዲህ አሉት፤ “ይህ ሰው በሚናገረው ነገር በዚህች ከተማ የቀሩትን ወታደሮችና ሕዝቡንም ሁሉ ተስፋ የሚያስቈርጥ ስለ ሆነ መሞት አለበት፤ ይህ ሰው የሕዝቡን መጥፋት እንጂ መልካም ነገር አይሻም።”(አ.መ.ት)
መኳንንቶቹ ፍፁም ውሸት በሆነ ክስ ኤርምያስን ይከሱታል
የሐሰት ክስ የተለመደ ነው ሙሴን ትዕቢተኛ ነው ብለው ሲከሱት አይተናል ፡ ኢዮብ እግዚአብሔር የመሰከረለትን ፃዲቅ ከባድ ሀጢአት ሰርተሀል ሲሉትም ተመልክተናል ፡ ጌታ ኢየሱስንም ጭምር አጋንንት አድሮበታል ብለው ከሰውታል
“5. ንጉሡ ሴዴቅያስም፤ “እርሱ በእጃችሁ ነው፤ ንጉሡ እናንተን ተቃውሞ ምንም ማድረግ አይችልም” አለ።”(አ.መ.ት)
ንጉስ ነው ግን መወሰን አይችልም ነበር
“6. ስለዚህ ኤርምያስን ወስደው፣ በዘበኞች አደባባይ በነበረው በንጉሡ ልጅ በመልክያ የውሃ ማጠራቀሚያ ጒድጓድ ውስጥ ጣሉት፤ በገመድም ኤርምያስን ወደ ጒድጓዱ አወረዱት። ጒድጓዱም ጭቃ እንጂ ውሃ አልነበረበትም፤ ኤርምያስም ወደ ጭቃው ዘልቆ ገባ።”(አ.መ.ት)
የነዚህ ሰዎች አላማ ኤርምያስን በእጃቸው ደም ሳያፈሱ በረሀብና በብርድ እዛው እንዲሞት ማድረግ ነው
በዚህ ጊዜ ታማኝ የሆነው እግዚአብሔር ሲገለጥ እናያለን
“9. “ጌታዬ ንጉሥ ሆይ፤ እነዚህ ሰዎች በነቢዩ በኤርምያስ ላይ ባደረጉት ነገር ሁሉ ክፋትን አድርገዋል፤ ከከተማዪቱም እንጀራ በጠፋ ጊዜ በራብ እንዲሞት ጒድጓድ ውስጥ ጥለውታል።”(አ.መ.ት)
ንጉሱ ሴዴቅያስ በቀላሉ የሰዎች ተፅእኖ ውስጥ የሚወድቅ ሰው ስለነበረ ይሄንን ሰው ሲሰማው እናያለን
እውነቱን እንገራቸው‼️ | የሐዋርያት ስራ ጥናት ምዕራፍ 10 | ቃልህ | #tigist_Ejigu #Hermela_Tesema #Rekik_Menda
