ar
Feedback
Nikodimos Christian center

Nikodimos Christian center

الذهاب إلى القناة على Telegram

Nikodimos Show is a unique program which is hosted by the famous Ethiopian Gospel Singer Tigist Ejigu, https://www.facebook.com/tigist.ejigu.5 This show is working on creating awareness on sensitive Christian issues inside the Church of Ethiopia.

إظهار المزيد
6 504
المشتركون
-124 ساعات
-247 أيام
-4830 أيام
أرشيف المشاركات
"9 ጥበበኛ የሆነ እነዚህን ነገሮች ያስተውላል፤ አስተዋይም እነዚህን ነገሮች ይረዳል። የእግዚአብሔር መንገድ ቅን ነውና፤ ጻድቃን ይሄዱበታል፤ ዐመፀኞች ግን ይሰናከሉበታል።"(አ.መ.ት) የእግዚአብሔር መንገድ ቅን ነው : ግን ማስተዋል ይጠይቃል ምክንያቱም ያው መንገድ ፃድቃን ይሄዱበታል ኃጢአተኞች ይሰናከሉበታል 1 የጴጥሮስ መልእክት 2: [7] እንግዲህ ለእናንተ ለምታምኑት ይህ ድንጋይ ክቡር ነው፤ ለማያምኑት ግን “ግንበኞች ንቀው የጣሉት ድንጋይ የማእዘን ራስ ሆነ።” [8] ደግሞም፥ “እነሆ! ሰዎችን የሚያሰናክል ድንጋይ፤ እነሆ! ሰዎችን አደናቅፎ የሚጥል አለት” ይላል። እነርሱ ቃሉን ባለማመናቸው ይሰናከላሉ፤ አስቀድመውም ለዚህ የተመደቡ ናቸው።(አ.ት) ምን እንማር ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ ምን ጊዜም አይረፍድም እውነትን ሰምተን እውነተኞች ሆነን እንመለስ እግዚአብሔር ኃጢአትን ይቅር ማለት ብቻ ሳይሆን ኃጢአተኝነትንም ይፈውሳል ንስሐ (መመለስ) በረከት አለው በኃጢአታችን ከማዘንና ከመፀፀት አልፈን ከዚያ ድርጊት ጋር ያለንን ግንኙነት ለማቋረጥ ድልድዩን መስበር ያስፈልጋል ማጠቃለያ የእግዚአብሔር ፍቅር ከሰዎች ውድቀት የላቀና እጅግ የታመነ ነው (ጎሜርና ሆሴእ) በኃጢአት እየኖርን ከሚያስከፍለው ዋጋ ማምለጥ አንችልም ምንም ያህል ርቀን ብንሄድ ወደ እግዚአብሔር መመለሻው በር ክፍት ነው : እግዚአብሔርም ያለማቋረጥ ይጣራል እግዚአብሔር ሃይማኖታዊ ስርዓትን ሳይሆን እውነተኛ ንስሐን ይፈልጋል እግዚአብሔር ቅዱስም አፍቃሪም ነው ወደ እርሱ ለሚመለሱ እግዚአብሔር በረከትና ፈውስን አዘጋጅቶአል ሆሴእ ጥላ ነው ኢየሱስ አካል ነው : ሆሴእ መልእክተኛ ነው ኢየሱስ ግን መልእክት ነው

"የያዕቆብን አታላይነቱን ሳይሆን ለውጡን ተከተሉ" "6 ስለዚህ ወደ አምላክህ ተመለስ፤ ፍቅርንና ፍትሕን ጠብቅ፤ ዘወትርም በአምላክህ ታመን።"(አ.መ.ት) የያዕቆብ መልእክት 4:10 በጌታ ፊት ራሳችሁን አዋርዱ፣ እርሱም ከፍ ከፍ ያደርጋችኋል። (አ.መ.ት) ከ 7-8 ሀብት ኃጢያትን ሊሸፍን አይችልም በሙስና እና በግፍ የሰበሰቡትን ሀብት የእግዚአብሔር ይሁንታ ማረጋገጫ እንደሆነ አድርገው ይቆጥሩ ነበር "[8] ከከነዓን ወገን ነው፥ በእጁ የተንኰል ሚዛን አለ፥ ሽንገላንም ይወድዳል።" እግዚአብሔር ምድራዊ ብልፅግናን ለህዝቡ ይሰጣል : ምድራዊ ብልፅግና ሁሉ ግን የእግዚአብሔር አብሮነት ማረጋገጫ አይደለም 9-14 እግዚአብሔር ሁልጊዜም ታማኝ ነበር ከግብፅ አወጣኃችሁ : በነቢዩ እጅ መራኃችሁ : በታሪካችሁ ሁሉ ጠበቅኃችሁ :: እናንተ ግን ደጋግማችሁ አመፃችሁብኝ 2 ወደ ጢሞቴዎስ 2 [13] ባናምነው፥ እርሱ የታመነ ሆኖ ይኖራል፤ ራሱን ሊክድ አይችልምና። የእግዚአብሔር ታማኝነት በሰው አለመታመን አይቀየርም ታማኝነት ፍፁም የሆነ በሁኔታም የማይለወጥ ባህሪው ነው ምን እንማር ከእግዚአብሔር ውጪ መታመኛ መፈለግ ንፋስን እንደመከተል ነው አታላዩ ያዕቆብ እውነተኛ ማንነቱን ለእግዚአብሔር ነግሮ እንደተለወጠ እንዲለውጠን በእግዚአብሔር ፊት እውነተኞች እንሁን ቁሳቁስ የእግዚአብሔር አብሮነት ማረጋገጫዎች አይደሉም እኛ ባንታመን እንኳን ለዘላለም ታማኝ በሆነው አምላክ እንደገፍ ትንቢተ ሆሴእ ምዕራፍ 13 የእግዚአብሔር ቁጣ በእስራኤል ላይ እግዚአብሔር የእስራኤልን ውድቀት ዋና ዋና ምክንያቶች ይናገራል ትእቢት : በራስ መታመን : ጣኦት አምልኮ : እግዚአብሔርን መርሳት ይህንን ሁሉ በደላቸውን ከዘረዘረ በኃላ ግን የመቤዠትን ተስፋ ይሰጣቸዋል 1-3 ከክብር ወደ ውድቀት ኤፍሬም (እስራኤል) በአንድ ወቅት የተከበረ ነበረ ባአልን ስላመለከ እንደጠዋት ጭጋግና ጠል እንደገለባና እንደጭስ ይጠፋል ኃጢአት ውርደት እንጂ ክብር የለበትም ከእግዚአብሔር ውጪ የሚገኝም "ክብር" ዘላቂነት የለውም 4-6 እግዚአብሔርን ራሱ! እግዚአብሔር "ከግብፅ ምድር ያወጣኅችሁ አምላካችሁ እኔ ነኝ " ብሎ ያስታውሳቸዋል "[5] በምድረ በዳ፥ እጅግ በደረቀ ምድር አውቄህ ነበር።" ብዙዎች እግዚአብሔርን የሚረሱት ሲርባቸው ሳይሆን ሲጠግቡ ነው ከመከራ ይልቅ ስኬት እግዚአብሔርን የማስረሳት ዝንባሌ አለው ኦሪት ዘዳግም 8:11-14 [11] ዛሬ እኔ አንተን የማዝዘውን ትእዛዙንና ፍርዱን ሥርዓቱንም ባለመጠበቅ አምላክህን እግዚአብሔርን እንዳትረሳ ተጠንቀቅ፤ [12] ከበላህና ከጠገብህ በኋላ፥ መልካምም ቤት ሠርተህ ከተቀመጥህበት በኋላ፥ [13] የላምና የበግ መንጋ ከበዛልህ በኋላ፥ ብርህና ወርቅህም ያለህም ሁሉ ከበዛልህ በኋላ፥ ልብህ እንዳይጓደድ፤ [14] ከግብፅም ምድር ከባርነት ቤት ያወጣህን፥ ነገር በተሳካልን ጊዜ እግዚአብሔርን አለመታዘዝ እግዚአብሔርን ከመርሳት እኩል ነው 7-8 ሊመጣ ያለው ፍርድ እግዚአብሔር እራሱን እንደ አንበሳ : እንደ ነብርና ግልገሎቿን እንደተነጠቀች ድብ ይመስላል ይሄ እግዚአብሔር ለኃጢያት ያለውን አመለካከት ያሳያል 9-11 እስራኤል እራሱን ያጠፋው በገዛ እጁ ነው! የጠፉት እግዚአብሔር ጠላት ሆኖባቸው ሳይሆን ኃጢአታቸው በገዛ ራሳቸው ላይ ጠላት እንዲሆኑ አድርጏቸው ነው ኃጢያት ሰውን የራሱ ጠላት (አጥፊ) እንዲሆን ያደረገዋል ብዙ ጊዜ ትልቁ ጠላታችን በውጪ ያሉ ኃይላት ሳይሆኑ በውስጣችን ያለ ንስሐ የማይገባ ልብ ነው የያዕቆብ መልእክት 1:14-15 [14] ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል። [15] ከዚህ በኋላ ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ትወልዳለች፤ ኃጢአትም ካደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች። ሰዋዊ መፍትሄ ሊታደግ አይችልም! "10 “ንጉሥንና አለቆችን ስጠኝ፤” ብለህ እንደ ጠየቅኸው፣ ያድንህ ዘንድ ንጉሥህ የት አለ? በከተሞችህ ሁሉ የነበሩ ገዦችህስ የት አሉ?"(አ.መ.ት) እግዚአብሔር ሰለንዝነዛችን ደስ ብሎትም ባይሆን በቁጣ የጠየቅነውን ሊሰጠን ይችላል "[14] ከሲኦል ኀይል እታደጋቸዋለሁን? ከሞትስ አድናቸዋለሁን? ሞት ሆይ! መቅሠፍቶችህ የት አሉ? ሲኦል ሆይ! አጥፊነትህ የት አለ? እኔኮ አልራራላቸውም፤"(አ.ት) 1 ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:54-55 [54] ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ፦ ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል። [55] ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ? ሆሴእ 13 በፍርድ መካከል እንኳን ወደ ትንሣኤ ተስፋ ይጠቁማል ምን እንማር ኃጢአት ውርደት እንጂ ክብር የለበትም ከመከራ ይልቅ ስኬት እግዚአብሔርን ያስረሳልና ሲሳካልን እግዚአብሔርን እንዳንረሳ እንጠንቀቅ ኃጢአትን እግዚአብሔር እንደሚያየው እንየው ኃጢአት ማንም ሳያጠፋን እራሳችንን እንድንናጠፋ ወይንም የራሳችን ጠላቶች እንድንሆን ያደርጋል ትንቢተ ሆሴእ ምዕራፍ 14 በረከትን ለማግኘት ንሰሐ መግባት 1-3 ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ " በኃጢአትህ ምክንያት ወድቀሃል " እግዚአብሔር ደህና ሳይሆኑ ደህና ናችሁ አይላቸውም ሰዎች ከክፉ መንገዳቸው እንዲመለሱ እውነቱ ሳይቀባባ ሊነገራቸው ይገባል "የኑዛዜ ቃል ይዛችሁ ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ" ሳታመካኙ (ሰበብ ሳትደረድሩ) ኃጢአታችሁን እመኑና ንስሐ ግቡ ኑዛዜ በደለኝነታችንን አምነን መቀበላችንንና እና ኃላፊነት መውሰዳችንን ያመለክታል የሉቃስ ወንጌል 15:18-21 [18] ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና፦ አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥ [19] ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም፤ ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ እለዋለሁ። [20] ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ። እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት፥ ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው። [21] ልጁም፦ አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም አለው። ሰዎችንም ይቅርታ ስንጠይቅ "አጥፍቻለው" ከማለት ባለፈ ምን እንደሆነ ጥፋታችን መናገርና እንዴት እንደምናስተካክለው ማሳወቅ ለግንኙነታችን ፈውስን ያመጣል "[4] ቍጣዬ ከእርሱ ዘንድ ተመልሶአልና ዓመፃቸውን እፈውሳለሁ፥ በገዛ ፈቃዴ እወድዳቸዋለሁ።" እግዚአብሔር የተበላሸ ግንኙነትን ብቻ ሳይሆን ዋናውን ችግር : ከዳተኛ ልብን ይፈውሳል እግዚአብሔር ከዳተኛነትን እንደጥፋት ብቻ ሳይሆን እንደበሽታም ነው የሚያየው የማርቆስ ወንጌል 2:17 [17] ኢየሱስም ሰምቶ፦ ሕመምተኞች እንጂ ብርቱዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም ኃጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም አላቸው። "እንዲሁ እወዳቸዋለሁ" ብቁ እስኪሆኑ ሳይጠብቅ ይወዳቸዋል 5-8 የተመለሰ ሕይወት ያብባል "5 እኔ ለእስራኤል እንደ ጠል እሆናለሁ፤ እንደ ውብ አበባ ያብባል፤ እንደ ሊባኖስ ዝግባም፣ ሥር ይሰዳል፤"(አ.መ.ት) በዚያን ዘመን ጠል በሕይወት ለመኖር እጅግ አስፈላጊ ነገር ነበር የተመለሰ ሰው :- እንደአበባ ያብባል እንደሊባኖስ ዝግባ ስር ይሰዳል ፍሬያማ ይሆናል ለ ሌሎች በረከት ይሆናል "8 ኤፍሬም ሆይ፤ ከእንግዲህ ከጣዖት ጋር ምን ጒዳይ አለኝ?b የምሰማህና የምጠነቀቅልህ እኔ ነኝ፤ እኔ እንደለመለመ የጥድ ዛፍ ነኝ፤ ፍሬያማነትህም ከእኔ የተነሣ ነው።”(አ.መ.ት) ኤፍሬም በመጨረሻ "ከእንግዲህ ከጣኦት ጋር ምን ጉዳይ አለኝ?" ይላል እውነተኛ ንስሐ በኃጢአት ማዘን ብቻ ሳይሆን ከዚያ ነገር ጋር ያለንን ግንኙነት ማቋረጥም ጭምር ነው

ትንቢተ ሆሴእ ምዕራፍ 11-14 ህዝቡ ባይታመንም የእግዚአብሔር ፍቅር ግን የታመነ ነው! “1 እስራኤል ገና ሕፃን ሳለ ወደድሁት፤ ልጄንም ከግብፅ ጠራሁት።"(አ.መ.ት) 1-4 እግዚአብሔር እንደ አባት ለእስራኤል ያለው ፍቅር (የእግዚአብሔር አባታዊ ፍቅር ለእስራኤል) ምዕራፉ የእግዚአብሔርን የፍቅር ልብ በእጅጉ የሚገልጥ ምዕራፍ ነው እግዚአብሔር እንደ አባት ህዝቡን ይወዳል ህዝቡ ግን በተደጋጋሚ ይክደዋል : በመጨረሻም ምህረቱ የመዳንን ተስፋ ያመጣል እግዚአብሔር በእስራኤል ላይ ያለውን ንጉሳዊ ስልጣን ሳይሆን አባታዊ ርህራሄውን ነው የሚናገረው መራመድ አስተማርኳቸው ተሸከምኳቸው ፈወስኳቸው በፍቅር ገመድ ሳብኳቸው ኦሪት ዘዳግም 1:31 በምድረ በዳው እንደ አደረገው ሁሉ። በዚያም አባት ልጁን እንደሚሸከም፣ እናንተን አምላካችሁእግዚአብሔር(ኤሎሂም ያህዌ) እዚህ ስፍራ እስክትደርሱ በመጣችሁበት መንገድ ሁሉ እንዴት እንደ ተሸከማችሁ አይታችኋል።” (አ.መ.ት) ትንቢተ ኢሳይያስ 63:9 በጭንቃቸው ሁሉ ተጨነቀ፤ የፊቱም መልአክ አዳናቸው፤ በፍቅሩና በምሕረቱ ዋጃቸው፤ በቀደመው ዘመን ሁሉ አነሣቸው፤ ተሸከማቸውም።(አ.መ.ት) ክፍሉ እስራኤል ከግብፅ መውጣቷን ከመተረክ ባሻገር መሲሀዊ መልእክትንም ይዞአል የማቴዎስ ወንጌል 2:13-15 እነርሱም ከሄዱ በኋላ እነሆ፥ የጌታ መልአክ በሕልም ለዮሴፍ ታይቶ፦ ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይፈልገዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ፥ እስክነግርህም ድረስ በዚያ ተቀመጥ አለው። [14-15] እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን በሌሊት ያዘና ከጌታ ዘንድ በነቢይ፦ ልጄን ከግብፅ ጠራሁት የተባለው እንዲፈጸም ወደ ግብፅ ሄደ፥ ሄሮድስም እስኪሞት ድረስ በዚያ ኖረ። የማቴዎስ ወንጌል 2:19-21 [19] ሄሮድስም ከሞተ በኋላ፥ እነሆ፥ የጌታ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ፦ [20] የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘህ ወደ እስራኤል አገር ሂድ አለ። [21] እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ያዘና ወደ እስራኤል አገር ገባ። 2-3 የተናቀ ፍቅርን እንያለን "በጠራኃቸው መጠን ከእኔ ራቁ" እግዚአብሔር ይጠራታል እስራኤል ትርቃለች : እግዚአብሔር ይወዳታል : እስራኤል ጣኦታትን ትከተላለች የዮሐንስ ወንጌል 1 [11] የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። የማቴዎስ ወንጌል 23: 37 “አንቺ ነቢያትን የምትገድዪ፣ ወደ አንቺ የተላኩትንም በድንጋይ የምትወግሪ ኢየሩሳሌም ሆይ፤ አንቺ ኢየሩሳሌም! ዶሮ ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሥር እንደምትሰበስብ፣ ልጆችሽን ለመሰብሰብ ስንት ጊዜ ፈለግሁ! እናንተ ግን ፈቃደኛ አልሆናችሁም፤(አ.መ.ት) ሰዎች የሚወዳቸውን አምላክ መግፋታቸው አዲስ ኃጢአት አይደለም "4 በሰው የርኅራኄ ገመድ፣ በፍቅርም ሰንሰለት ሳብኋቸው፤ ቀንበሩን ከጫንቃቸው ላይ አነሣሁላቸው፤ ዝቅ ብዬም መገብኋቸው።"(አ.መ.ት) ሰው እግዚአብሔር ካልሳበው ወደ እግዚአብሔር መምጣት አይችልም እግዚአብሔር ሲጠራ በተግሳፅ ሳይሆን በፍቅር ነው ሰዎችን የሚስብበት ሰንሰለቱም ፍቅር ነው ሰንሰለቱም :- ከባርነት ነፃ ማውጣት በምድረ በዳ መመገብ ከጠላቶቻቸው መጠበቅ አመፃቸውን ሳይታክት ይቅር ማለት ነው የእግዚአብሔር ቀዳሚ መሻቱ ፍርድ ሳይሆን ፍቅር ነው "ቀንበሩን ከጫንቃቸው ላይ አነሳሁላችሁ " እስራኤል በግብፅ የባርነት ቀንበር ከብዶበት ሲጮህ ነው እግዚአብሔር የደረሰለት ካለፈ በኃላ ግን ረሱት የማቴዎስ ወንጌል 11:28-30 [28] እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። [29] ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ [30] ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና። "ዝቅ ብዬ መገብኳቸው" "እኔ ራሴ ጎንበስ ብዬ መገብኳቸው" ሰው ሕፃን ልጁን ዝቅ ብሎ (በልጁ ትክክል) ሆኖ እንደሚመግብ የሰማይና የምድር ጌታ ሕዝቡን በሩቅ ሆኖ በመልክተኛ እጅ ሳይሆን እራሱ ዝቅ ብሎ መገባቸው ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:6-8 [6] እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቍኦጠረውም፥ [7] ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ [8] በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ። እራሳቸውን ማዳንና መርዳት የማይችሉ ቀንበር የከበደባቸውን ሰዎች ለማዳንና ለመርዳት ዝቅ ያለው አምላክ የወረደው ለመስቀል ሞት እስከ መታዘዝ ነው ሆሴእ 11 የሚያሳየን ኃጢአት ትእዛዝን ከመተላለፍ ባለፈ የእግዚአብሔርን ፍቅር መግፋት ጭምር መሆኑን ነው 5-7 ፍርድ እየመጣ ነው! እስራኤል ከእግዚአብሔር ነፃ መሆን መፈለጕ የአሶር ባርያ ወደ መሆን ነው ያስገባው ከእግዚአብሔር ነፃ መሆን ነፃነት ሳይሆን ባርነት ነው "5 “ታዲያ ንስሓ መግባትን እምቢ በማለታቸው፣ ወደ ግብፅ አይመለሱምን? አሦርስ አይገዛቸውምን?"(አ.መ.ት) ልንተወው የማንፈልገው ኃጢአት ባሮች ያደርገናል የዮሐንስ ወንጌል 8 [34] ኢየሱስ መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ኃጢአት የሚያደርግ ሁሉ የኃጢአት ባርያ ነው። 8-9 የእግዚአብሔር ልብ በፍርድ ይሰበራል እንጂ አይደሰትም እግዚአብሔር ኃጢአትን መቅጣት ያለበት እጅግ ቅዱስ አምላክ ቢሆንም ለህዝቡ ያለው ፍቅር ግን ልቡን ይሰብረዋል "ልቤ በውስጤ ተናወጠ" በአመፀኛ ልጁ መቀጣት የሚያዝን አባት እናያለን ሰቈቃወ ኤርምያስ 3: [22] ሔት። ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፥ ርኅራኄው አያልቅምና። በክርስቶስ መስቀል የእግዚአብሔር ፃድቅ ፍርድና ፍፁም ፍቅር በሙላት ተገልጧል ወደ ሮም ሰዎች 5 [8] ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል። 10-11 ከፍርድ በኃላ የመመለስ ተስፋ አለ "10 እግዚአብሔርን ይከተላሉ፤ እርሱም እንደ አንበሳ ያገሣል፤ እርሱ ሲያገሣ፣ ልጆቹ እየተንቀጠቀጡ ከምዕራብ ይመጣሉ።"(አ.መ.ት) "እግዚአብሔርን ይከተላሉ " የአንበሳው ማግሳት ለልጆቹ የማስፈራራት ሳይሆን ጥሪ ነው ምን እንማር አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደሰጠን እናስብ ጌታ ያነሳልንን ቀንበር አንርሳ የሰማይና የምድር ጌታ እኛን ደካሞቹን ለመርዳት እራሱ ዝቅ ብሎ እንደመጣ እናስብ ኃጢያት ማለት አለመታዘዝ ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔርን ወደር የሌለውን ፍቅር መግፋትም ነው ትንቢተ ሆሴእ ምዕራፍ 12 በትህትና እና በእውነተኛ ልብ ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ እግዚአብሔር ምዕራፍ 11 ላይ ጥልቅ አባታዊ ፍቅሩን ቢገልጥላቸውም እስራኤል ግን በማታለል በትእቢትና በራሷ በመተማመን መጏዝ ቀጥላ ነበር 1-2 እስራኤል አታላይ ነው "1 ኤፍሬም የነፋስ እረኛ ነው፤ ቀኑን ሙሉ የምሥራቅን ነፋስ ይከተላል፤ ሐሰትንና ዐመፅን ያበዛል። ከአሦር ጋር ቃል ኪዳን ያደርጋል፤ የወይራ ዘይትንም ወደ ግብፅ ይልካል።"(አ.መ.ት) የማያረካ : የማያድን : የማያስተማምንና ማለቂያ (መጨበጫ) የሌለው ነገር እያሳደዱ ነው ከእግዚአብሔር ዘንድ ሳይሆን ከሌላ ስፍራ እነዚህን ነገሮች ለማግኘት መሞከር ንፋስን እንደመከተል ነው ከ 3-6 እግዚአብሔር ወደ ያዕቆብ ታሪክ ይመልሳቸዋል የያዕቆብ ሕይወት የማታለል : የተንኮልና በራስ ጥበብ የመታመን ሕይወት ነበረ : ነገር ግን በቤተል እግዚአብሔር ተገናኘው እርሱም አልቅሶ ለመነውና ስሙ ተለወጠ

"9 ጥበበኛ የሆነ እነዚህን ነገሮች ያስተውላል፤ አስተዋይም እነዚህን ነገሮች ይረዳል። የእግዚአብሔር መንገድ ቅን ነውና፤ ጻድቃን ይሄዱበታል፤ ዐመፀኞች ግን ይሰናከሉበታል።"(አ.መ.ት) የእግዚአብሔር መንገድ ቅን ነው : ግን ማስተዋል ይጠይቃል ምክንያቱም ያው መንገድ ፃድቃን ይሄዱበታል ኃጢአተኞች ይሰናከሉበታል 1 የጴጥሮስ መልእክት 2: [7] እንግዲህ ለእናንተ ለምታምኑት ይህ ድንጋይ ክቡር ነው፤ ለማያምኑት ግን “ግንበኞች ንቀው የጣሉት ድንጋይ የማእዘን ራስ ሆነ።” [8] ደግሞም፥ “እነሆ! ሰዎችን የሚያሰናክል ድንጋይ፤ እነሆ! ሰዎችን አደናቅፎ የሚጥል አለት” ይላል። እነርሱ ቃሉን ባለማመናቸው ይሰናከላሉ፤ አስቀድመውም ለዚህ የተመደቡ ናቸው።(አ.ት) ምን እንማር ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ ምን ጊዜም አይረፍድም እውነትን ሰምተን እውነተኞች ሆነን እንመለስ እግዚአብሔር ኃጢአትን ይቅር ማለት ብቻ ሳይሆን ኃጢአተኝነትንም ይፈውሳል ንስሐ (መመለስ) በረከት አለው በኃጢአታችን ከማዘንና ከመፀፀት አልፈን ከዚያ ድርጊት ጋር ያለንን ግንኙነት ለማቋረጥ ድልድዩን መስበር ያስፈልጋል ማጠቃለያ የእግዚአብሔር ፍቅር ከሰዎች ውድቀት የላቀና እጅግ የታመነ ነው (ጎሜርና ሆሴእ) በኃጢአት እየኖርን ከሚያስከፍለው ዋጋ ማምለጥ አንችልም ምንም ያህል ርቀን ብንሄድ ወደ እግዚአብሔር መመለሻው በር ክፍት ነው : እግዚአብሔርም ያለማቋረጥ ይጣራል እግዚአብሔር ሃይማኖታዊ ስርዓትን ሳይሆን እውነተኛ ንስሐን ይፈልጋል እግዚአብሔር ቅዱስም አፍቃሪም ነው ወደ እርሱ ለሚመለሱ እግዚአብሔር በረከትና ፈውስን አዘጋጅቶአል ሆሴእ ጥላ ነው ኢየሱስ አካል ነው : ሆሴእ መልእክተኛ ነው ኢየሱስ ግን መልእክት ነው

"የያዕቆብን አታላይነቱን ሳይሆን ለውጡን ተከተሉ" "6 ስለዚህ ወደ አምላክህ ተመለስ፤ ፍቅርንና ፍትሕን ጠብቅ፤ ዘወትርም በአምላክህ ታመን።"(አ.መ.ት) የያዕቆብ መልእክት 4:10 በጌታ ፊት ራሳችሁን አዋርዱ፣ እርሱም ከፍ ከፍ ያደርጋችኋል። (አ.መ.ት) ከ 7-8 ሀብት ኃጢያትን ሊሸፍን አይችልም በሙስና እና በግፍ የሰበሰቡትን ሀብት የእግዚአብሔር ይሁንታ ማረጋገጫ እንደሆነ አድርገው ይቆጥሩ ነበር "[8] ከከነዓን ወገን ነው፥ በእጁ የተንኰል ሚዛን አለ፥ ሽንገላንም ይወድዳል።" እግዚአብሔር ምድራዊ ብልፅግናን ለህዝቡ ይሰጣል : ምድራዊ ብልፅግና ሁሉ ግን የእግዚአብሔር አብሮነት ማረጋገጫ አይደለም 9-14 እግዚአብሔር ሁልጊዜም ታማኝ ነበር ከግብፅ አወጣኃችሁ : በነቢዩ እጅ መራኃችሁ : በታሪካችሁ ሁሉ ጠበቅኃችሁ :: እናንተ ግን ደጋግማችሁ አመፃችሁብኝ 2 ወደ ጢሞቴዎስ 2 [13] ባናምነው፥ እርሱ የታመነ ሆኖ ይኖራል፤ ራሱን ሊክድ አይችልምና። የእግዚአብሔር ታማኝነት በሰው አለመታመን አይቀየርም ታማኝነት ፍፁም የሆነ በሁኔታም የማይለወጥ ባህሪው ነው ምን እንማር ከእግዚአብሔር ውጪ መታመኛ መፈለግ ንፋስን እንደመከተል ነው አታላዩ ያዕቆብ እውነተኛ ማንነቱን ለእግዚአብሔር ነግሮ እንደተለወጠ እንዲለውጠን በእግዚአብሔር ፊት እውነተኞች እንሁን ቁሳቁስ የእግዚአብሔር አብሮነት ማረጋገጫዎች አይደሉም እኛ ባንታመን እንኳን ለዘላለም ታማኝ በሆነው አምላክ እንደገፍ ትንቢተ ሆሴእ ምዕራፍ 13 የእግዚአብሔር ቁጣ በእስራኤል ላይ እግዚአብሔር የእስራኤልን ውድቀት ዋና ዋና ምክንያቶች ይናገራል ትእቢት : በራስ መታመን : ጣኦት አምልኮ : እግዚአብሔርን መርሳት ይህንን ሁሉ በደላቸውን ከዘረዘረ በኃላ ግን የመቤዠትን ተስፋ ይሰጣቸዋል 1-3 ከክብር ወደ ውድቀት ኤፍሬም (እስራኤል) በአንድ ወቅት የተከበረ ነበረ ባአልን ስላመለከ እንደጠዋት ጭጋግና ጠል እንደገለባና እንደጭስ ይጠፋል ኃጢአት ውርደት እንጂ ክብር የለበትም ከእግዚአብሔር ውጪ የሚገኝም "ክብር" ዘላቂነት የለውም 4-6 እግዚአብሔርን ራሱ! እግዚአብሔር "ከግብፅ ምድር ያወጣኅችሁ አምላካችሁ እኔ ነኝ " ብሎ ያስታውሳቸዋል "[5] በምድረ በዳ፥ እጅግ በደረቀ ምድር አውቄህ ነበር።" ብዙዎች እግዚአብሔርን የሚረሱት ሲርባቸው ሳይሆን ሲጠግቡ ነው ከመከራ ይልቅ ስኬት እግዚአብሔርን የማስረሳት ዝንባሌ አለው ኦሪት ዘዳግም 8:11-14 [11] ዛሬ እኔ አንተን የማዝዘውን ትእዛዙንና ፍርዱን ሥርዓቱንም ባለመጠበቅ አምላክህን እግዚአብሔርን እንዳትረሳ ተጠንቀቅ፤ [12] ከበላህና ከጠገብህ በኋላ፥ መልካምም ቤት ሠርተህ ከተቀመጥህበት በኋላ፥ [13] የላምና የበግ መንጋ ከበዛልህ በኋላ፥ ብርህና ወርቅህም ያለህም ሁሉ ከበዛልህ በኋላ፥ ልብህ እንዳይጓደድ፤ [14] ከግብፅም ምድር ከባርነት ቤት ያወጣህን፥ ነገር በተሳካልን ጊዜ እግዚአብሔርን አለመታዘዝ እግዚአብሔርን ከመርሳት እኩል ነው 7-8 ሊመጣ ያለው ፍርድ እግዚአብሔር እራሱን እንደ አንበሳ : እንደ ነብርና ግልገሎቿን እንደተነጠቀች ድብ ይመስላል ይሄ እግዚአብሔር ለኃጢያት ያለውን አመለካከት ያሳያል 9-11 እስራኤል እራሱን ያጠፋው በገዛ እጁ ነው! የጠፉት እግዚአብሔር ጠላት ሆኖባቸው ሳይሆን ኃጢአታቸው በገዛ ራሳቸው ላይ ጠላት እንዲሆኑ አድርጏቸው ነው ኃጢያት ሰውን የራሱ ጠላት (አጥፊ) እንዲሆን ያደረገዋል ብዙ ጊዜ ትልቁ ጠላታችን በውጪ ያሉ ኃይላት ሳይሆኑ በውስጣችን ያለ ንስሐ የማይገባ ልብ ነው የያዕቆብ መልእክት 1:14-15 [14] ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል። [15] ከዚህ በኋላ ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ትወልዳለች፤ ኃጢአትም ካደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች። ሰዋዊ መፍትሄ ሊታደግ አይችልም! "10 “ንጉሥንና አለቆችን ስጠኝ፤” ብለህ እንደ ጠየቅኸው፣ ያድንህ ዘንድ ንጉሥህ የት አለ? በከተሞችህ ሁሉ የነበሩ ገዦችህስ የት አሉ?"(አ.መ.ት) እግዚአብሔር ሰለንዝነዛችን ደስ ብሎትም ባይሆን በቁጣ የጠየቅነውን ሊሰጠን ይችላል "[14] ከሲኦል ኀይል እታደጋቸዋለሁን? ከሞትስ አድናቸዋለሁን? ሞት ሆይ! መቅሠፍቶችህ የት አሉ? ሲኦል ሆይ! አጥፊነትህ የት አለ? እኔኮ አልራራላቸውም፤"(አ.ት) 1 ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:54-55 [54] ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ፦ ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል። [55] ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ? ሆሴእ 13 በፍርድ መካከል እንኳን ወደ ትንሣኤ ተስፋ ይጠቁማል ምን እንማር ኃጢአት ውርደት እንጂ ክብር የለበትም ከመከራ ይልቅ ስኬት እግዚአብሔርን ያስረሳልና ሲሳካልን እግዚአብሔርን እንዳንረሳ እንጠንቀቅ ኃጢአትን እግዚአብሔር እንደሚያየው እንየው ኃጢአት ማንም ሳያጠፋን እራሳችንን እንድንናጠፋ ወይንም የራሳችን ጠላቶች እንድንሆን ያደርጋል ትንቢተ ሆሴእ ምዕራፍ 14 በረከትን ለማግኘት ንሰሐ መግባት 1-3 ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ " በኃጢአትህ ምክንያት ወድቀሃል " እግዚአብሔር ደህና ሳይሆኑ ደህና ናችሁ አይላቸውም ሰዎች ከክፉ መንገዳቸው እንዲመለሱ እውነቱ ሳይቀባባ ሊነገራቸው ይገባል "የኑዛዜ ቃል ይዛችሁ ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ" ሳታመካኙ (ሰበብ ሳትደረድሩ) ኃጢአታችሁን እመኑና ንስሐ ግቡ ኑዛዜ በደለኝነታችንን አምነን መቀበላችንንና እና ኃላፊነት መውሰዳችንን ያመለክታል የሉቃስ ወንጌል 15:18-21 [18] ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና፦ አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥ [19] ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም፤ ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ እለዋለሁ። [20] ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ። እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት፥ ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው። [21] ልጁም፦ አባቴ ሆይ፥ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፥ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም አለው። ሰዎችንም ይቅርታ ስንጠይቅ "አጥፍቻለው" ከማለት ባለፈ ምን እንደሆነ ጥፋታችን መናገርና እንዴት እንደምናስተካክለው ማሳወቅ ለግንኙነታችን ፈውስን ያመጣል "[4] ቍጣዬ ከእርሱ ዘንድ ተመልሶአልና ዓመፃቸውን እፈውሳለሁ፥ በገዛ ፈቃዴ እወድዳቸዋለሁ።" እግዚአብሔር የተበላሸ ግንኙነትን ብቻ ሳይሆን ዋናውን ችግር : ከዳተኛ ልብን ይፈውሳል እግዚአብሔር ከዳተኛነትን እንደጥፋት ብቻ ሳይሆን እንደበሽታም ነው የሚያየው የማርቆስ ወንጌል 2:17 [17] ኢየሱስም ሰምቶ፦ ሕመምተኞች እንጂ ብርቱዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም ኃጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም አላቸው። "እንዲሁ እወዳቸዋለሁ" ብቁ እስኪሆኑ ሳይጠብቅ ይወዳቸዋል 5-8 የተመለሰ ሕይወት ያብባል "5 እኔ ለእስራኤል እንደ ጠል እሆናለሁ፤ እንደ ውብ አበባ ያብባል፤ እንደ ሊባኖስ ዝግባም፣ ሥር ይሰዳል፤"(አ.መ.ት) በዚያን ዘመን ጠል በሕይወት ለመኖር እጅግ አስፈላጊ ነገር ነበር የተመለሰ ሰው :- እንደአበባ ያብባል እንደሊባኖስ ዝግባ ስር ይሰዳል ፍሬያማ ይሆናል ለ ሌሎች በረከት ይሆናል "8 ኤፍሬም ሆይ፤ ከእንግዲህ ከጣዖት ጋር ምን ጒዳይ አለኝ?b የምሰማህና የምጠነቀቅልህ እኔ ነኝ፤ እኔ እንደለመለመ የጥድ ዛፍ ነኝ፤ ፍሬያማነትህም ከእኔ የተነሣ ነው።”(አ.መ.ት) ኤፍሬም በመጨረሻ "ከእንግዲህ ከጣኦት ጋር ምን ጉዳይ አለኝ?" ይላል እውነተኛ ንስሐ በኃጢአት ማዘን ብቻ ሳይሆን ከዚያ ነገር ጋር ያለንን ግንኙነት ማቋረጥም ጭምር ነው

ትንቢተ ሆሴእ ምዕራፍ 11-14 ህዝቡ ባይታመንም የእግዚአብሔር ፍቅር ግን የታመነ ነው! “1 እስራኤል ገና ሕፃን ሳለ ወደድሁት፤ ልጄንም ከግብፅ ጠራሁት።"(አ.መ.ት) 1-4 እግዚአብሔር እንደ አባት ለእስራኤል ያለው ፍቅር (የእግዚአብሔር አባታዊ ፍቅር ለእስራኤል) ምዕራፉ የእግዚአብሔርን የፍቅር ልብ በእጅጉ የሚገልጥ ምዕራፍ ነው እግዚአብሔር እንደ አባት ህዝቡን ይወዳል ህዝቡ ግን በተደጋጋሚ ይክደዋል : በመጨረሻም ምህረቱ የመዳንን ተስፋ ያመጣል እግዚአብሔር በእስራኤል ላይ ያለውን ንጉሳዊ ስልጣን ሳይሆን አባታዊ ርህራሄውን ነው የሚናገረው መራመድ አስተማርኳቸው ተሸከምኳቸው ፈወስኳቸው በፍቅር ገመድ ሳብኳቸው ኦሪት ዘዳግም 1:31 በምድረ በዳው እንደ አደረገው ሁሉ። በዚያም አባት ልጁን እንደሚሸከም፣ እናንተን አምላካችሁእግዚአብሔር(ኤሎሂም ያህዌ) እዚህ ስፍራ እስክትደርሱ በመጣችሁበት መንገድ ሁሉ እንዴት እንደ ተሸከማችሁ አይታችኋል።” (አ.መ.ት) ትንቢተ ኢሳይያስ 63:9 በጭንቃቸው ሁሉ ተጨነቀ፤ የፊቱም መልአክ አዳናቸው፤ በፍቅሩና በምሕረቱ ዋጃቸው፤ በቀደመው ዘመን ሁሉ አነሣቸው፤ ተሸከማቸውም።(አ.መ.ት) ክፍሉ እስራኤል ከግብፅ መውጣቷን ከመተረክ ባሻገር መሲሀዊ መልእክትንም ይዞአል የማቴዎስ ወንጌል 2:13-15 እነርሱም ከሄዱ በኋላ እነሆ፥ የጌታ መልአክ በሕልም ለዮሴፍ ታይቶ፦ ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይፈልገዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ፥ እስክነግርህም ድረስ በዚያ ተቀመጥ አለው። [14-15] እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን በሌሊት ያዘና ከጌታ ዘንድ በነቢይ፦ ልጄን ከግብፅ ጠራሁት የተባለው እንዲፈጸም ወደ ግብፅ ሄደ፥ ሄሮድስም እስኪሞት ድረስ በዚያ ኖረ። የማቴዎስ ወንጌል 2:19-21 [19] ሄሮድስም ከሞተ በኋላ፥ እነሆ፥ የጌታ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ፦ [20] የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘህ ወደ እስራኤል አገር ሂድ አለ። [21] እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ያዘና ወደ እስራኤል አገር ገባ። 2-3 የተናቀ ፍቅርን እንያለን "በጠራኃቸው መጠን ከእኔ ራቁ" እግዚአብሔር ይጠራታል እስራኤል ትርቃለች : እግዚአብሔር ይወዳታል : እስራኤል ጣኦታትን ትከተላለች የዮሐንስ ወንጌል 1 [11] የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። የማቴዎስ ወንጌል 23: 37 “አንቺ ነቢያትን የምትገድዪ፣ ወደ አንቺ የተላኩትንም በድንጋይ የምትወግሪ ኢየሩሳሌም ሆይ፤ አንቺ ኢየሩሳሌም! ዶሮ ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሥር እንደምትሰበስብ፣ ልጆችሽን ለመሰብሰብ ስንት ጊዜ ፈለግሁ! እናንተ ግን ፈቃደኛ አልሆናችሁም፤(አ.መ.ት) ሰዎች የሚወዳቸውን አምላክ መግፋታቸው አዲስ ኃጢአት አይደለም "4 በሰው የርኅራኄ ገመድ፣ በፍቅርም ሰንሰለት ሳብኋቸው፤ ቀንበሩን ከጫንቃቸው ላይ አነሣሁላቸው፤ ዝቅ ብዬም መገብኋቸው።"(አ.መ.ት) ሰው እግዚአብሔር ካልሳበው ወደ እግዚአብሔር መምጣት አይችልም እግዚአብሔር ሲጠራ በተግሳፅ ሳይሆን በፍቅር ነው ሰዎችን የሚስብበት ሰንሰለቱም ፍቅር ነው ሰንሰለቱም :- ከባርነት ነፃ ማውጣት በምድረ በዳ መመገብ ከጠላቶቻቸው መጠበቅ አመፃቸውን ሳይታክት ይቅር ማለት ነው የእግዚአብሔር ቀዳሚ መሻቱ ፍርድ ሳይሆን ፍቅር ነው "ቀንበሩን ከጫንቃቸው ላይ አነሳሁላችሁ " እስራኤል በግብፅ የባርነት ቀንበር ከብዶበት ሲጮህ ነው እግዚአብሔር የደረሰለት ካለፈ በኃላ ግን ረሱት የማቴዎስ ወንጌል 11:28-30 [28] እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። [29] ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ [30] ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና። "ዝቅ ብዬ መገብኳቸው" "እኔ ራሴ ጎንበስ ብዬ መገብኳቸው" ሰው ሕፃን ልጁን ዝቅ ብሎ (በልጁ ትክክል) ሆኖ እንደሚመግብ የሰማይና የምድር ጌታ ሕዝቡን በሩቅ ሆኖ በመልክተኛ እጅ ሳይሆን እራሱ ዝቅ ብሎ መገባቸው ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:6-8 [6] እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቍኦጠረውም፥ [7] ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ [8] በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ። እራሳቸውን ማዳንና መርዳት የማይችሉ ቀንበር የከበደባቸውን ሰዎች ለማዳንና ለመርዳት ዝቅ ያለው አምላክ የወረደው ለመስቀል ሞት እስከ መታዘዝ ነው ሆሴእ 11 የሚያሳየን ኃጢአት ትእዛዝን ከመተላለፍ ባለፈ የእግዚአብሔርን ፍቅር መግፋት ጭምር መሆኑን ነው 5-7 ፍርድ እየመጣ ነው! እስራኤል ከእግዚአብሔር ነፃ መሆን መፈለጕ የአሶር ባርያ ወደ መሆን ነው ያስገባው ከእግዚአብሔር ነፃ መሆን ነፃነት ሳይሆን ባርነት ነው "5 “ታዲያ ንስሓ መግባትን እምቢ በማለታቸው፣ ወደ ግብፅ አይመለሱምን? አሦርስ አይገዛቸውምን?"(አ.መ.ት) ልንተወው የማንፈልገው ኃጢአት ባሮች ያደርገናል የዮሐንስ ወንጌል 8 [34] ኢየሱስ መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ኃጢአት የሚያደርግ ሁሉ የኃጢአት ባርያ ነው። 8-9 የእግዚአብሔር ልብ በፍርድ ይሰበራል እንጂ አይደሰትም እግዚአብሔር ኃጢአትን መቅጣት ያለበት እጅግ ቅዱስ አምላክ ቢሆንም ለህዝቡ ያለው ፍቅር ግን ልቡን ይሰብረዋል "ልቤ በውስጤ ተናወጠ" በአመፀኛ ልጁ መቀጣት የሚያዝን አባት እናያለን ሰቈቃወ ኤርምያስ 3: [22] ሔት። ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፥ ርኅራኄው አያልቅምና። በክርስቶስ መስቀል የእግዚአብሔር ፃድቅ ፍርድና ፍፁም ፍቅር በሙላት ተገልጧል ወደ ሮም ሰዎች 5 [8] ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል። 10-11 ከፍርድ በኃላ የመመለስ ተስፋ አለ "10 እግዚአብሔርን ይከተላሉ፤ እርሱም እንደ አንበሳ ያገሣል፤ እርሱ ሲያገሣ፣ ልጆቹ እየተንቀጠቀጡ ከምዕራብ ይመጣሉ።"(አ.መ.ት) "እግዚአብሔርን ይከተላሉ " የአንበሳው ማግሳት ለልጆቹ የማስፈራራት ሳይሆን ጥሪ ነው ምን እንማር አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደሰጠን እናስብ ጌታ ያነሳልንን ቀንበር አንርሳ የሰማይና የምድር ጌታ እኛን ደካሞቹን ለመርዳት እራሱ ዝቅ ብሎ እንደመጣ እናስብ ኃጢያት ማለት አለመታዘዝ ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔርን ወደር የሌለውን ፍቅር መግፋትም ነው ትንቢተ ሆሴእ ምዕራፍ 12 በትህትና እና በእውነተኛ ልብ ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ እግዚአብሔር ምዕራፍ 11 ላይ ጥልቅ አባታዊ ፍቅሩን ቢገልጥላቸውም እስራኤል ግን በማታለል በትእቢትና በራሷ በመተማመን መጏዝ ቀጥላ ነበር 1-2 እስራኤል አታላይ ነው "1 ኤፍሬም የነፋስ እረኛ ነው፤ ቀኑን ሙሉ የምሥራቅን ነፋስ ይከተላል፤ ሐሰትንና ዐመፅን ያበዛል። ከአሦር ጋር ቃል ኪዳን ያደርጋል፤ የወይራ ዘይትንም ወደ ግብፅ ይልካል።"(አ.መ.ት) የማያረካ : የማያድን : የማያስተማምንና ማለቂያ (መጨበጫ) የሌለው ነገር እያሳደዱ ነው ከእግዚአብሔር ዘንድ ሳይሆን ከሌላ ስፍራ እነዚህን ነገሮች ለማግኘት መሞከር ንፋስን እንደመከተል ነው ከ 3-6 እግዚአብሔር ወደ ያዕቆብ ታሪክ ይመልሳቸዋል የያዕቆብ ሕይወት የማታለል : የተንኮልና በራስ ጥበብ የመታመን ሕይወት ነበረ : ነገር ግን በቤተል እግዚአብሔር ተገናኘው እርሱም አልቅሶ ለመነውና ስሙ ተለወጠ

357ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ 10 - 12
357ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ  ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ  10 - 12 የዩቱብ  የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች  ታገኛላችሁ👇 YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316 TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu TIKTOK#2:-  tiktok.com/nikodimoschrstiancenter TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow

#ቶሎ_ና! 3 ቀን ብቻ ቀረው! የእህታችን አገልጋይ ትዕግሥት እጅጉ ቶሎ ና የተሰኘው የክርስቶስን ምፅአት እንድንናፍቅ የሚያስታውሰን፣ ኢየሱስን የሚሰብከን ቶሎ ና የተሰኘ ኢፒ (ግማሽ አልበም) የፊታ
#ቶሎ_ና! 3 ቀን ብቻ ቀረው! የእህታችን አገልጋይ ትዕግሥት እጅጉ ቶሎ ና የተሰኘው የክርስቶስን ምፅአት እንድንናፍቅ የሚያስታውሰን፣ ኢየሱስን የሚሰብከን ቶሎ ና የተሰኘ ኢፒ (ግማሽ አልበም) የፊታችን ቅዳሜ ነሀሴ 30 ከ8:30 ጀምሮ በታላቅ ድምቀት ሊመረቅ እነሆ 3 ቀን ብቻ ቀረው። በእለቱ የእግዚአብሔር ቃል እንዲሁም ዝማሬ ይቀርባል። ሁላችሁም ተጋብዛችኋል፡፡ #ኒቆዲሞስ_ክርስቲያን_ሴንተር!

#ና! #3_ቀናት_ብቻ_ቀሩን! "አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር ተስፋችን ይህ ነው!" መስከረም 1 ዘፍጥረት 1 ብለን የጀመርነው ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ ጉዞአችን በእግዚአብሔር ፈቃድና እርዳታ እነሆ
#ና! #3_ቀናት_ብቻ_ቀሩን! "አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር ተስፋችን ይህ ነው!" መስከረም 1 ዘፍጥረት 1 ብለን የጀመርነው ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ ጉዞአችን በእግዚአብሔር ፈቃድና እርዳታ እነሆ ራእይ 22 ብለን ነሐሴ 30፣ 2018 ልንጨርስና በአካል ልንገናኝ 3 ቀናት ብቻ ቀርተውናል። ቀን ፡- ነሐሴ 30/2018 ሰዓት :- ከ 8:00 ጀምሮ ቦታ :- ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን ቦሌ አጥቢያ #ጌታ_ኢየሱስ_ሆይ_ና! #መስከረም1_ዘፍጥረት1_ጿግሜ5_ራዕይ22 ኒቆዲሞስ ክርስቲያን ሴንተር

356ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ 7 - 9 የዩ
356ኛ ቀን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ  ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና:: ዛሬ የምናነበው ክፍል የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ  7 - 9 የዩቱብ  የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች  ታገኛላችሁ👇 YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316 TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu TIKTOK#2:-  tiktok.com/nikodimoschrstiancenter TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow

#ና! #4_ቀናት_ብቻ_ቀሩን! "ንጉሣችን ይመጣል! እኛም ዝግጁ እንሁን!" መስከረም 1 ዘፍጥረት 1 ብለን የጀመርነው ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ ጉዞአችን በእግዚአብሔር ፈቃድና እርዳታ እነሆ ራእይ
#ና! #4_ቀናት_ብቻ_ቀሩን! "ንጉሣችን ይመጣል! እኛም ዝግጁ እንሁን!" መስከረም 1 ዘፍጥረት 1 ብለን የጀመርነው ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ ጉዞአችን በእግዚአብሔር ፈቃድና እርዳታ እነሆ ራእይ 22 ብለን ነሐሴ 30፣ 2018 ልንጨርስና በአካል ልንገናኝ 4 ቀናት ብቻ ቀርተውናል። ቀን ፡- ነሐሴ 30/2018 ሰዓት :- ከ 8:00 ጀምሮ ቦታ :- ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን ቦሌ አጥቢያ #ጌታ_ኢየሱስ_ሆይ_ና! #መስከረም1_ዘፍጥረት1_ጿግሜ5_ራዕይ22 ኒቆዲሞስ ክርስቲያን ሴንተር

4 ቀን ብቻ ቀረው!
4 ቀን ብቻ ቀረው!