uk
Feedback
Federal Ethics And Anti- Corruption Commission

Federal Ethics And Anti- Corruption Commission

Відкрити в Telegram
9 948
Підписники
+1324 години
+577 днів
-230 день
Архів дописів
ኮሚሽኑ የስልጠና ተገቢነትና ጥራት ማረጋገጫ ኮንፈረንስ አካሄደ ********************** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ የሰጣቸውን ስልጠናዎች ጥንካሬና ክፍተት የገመገመበት የስልጠና ተገቢነትና ጥራት ማረጋገጫ ኮንፈረንስ አካሂዷል። ኮሚሽኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለያዩ ደረጃዎች ለሚገኙ አካላት የሰጣቸውን ስልጠናዎች ከቅድመ-ዝግጅት ስራዎች ጀምሮ በስልጠና አሰጣጥ ሂደት እና ድህረ-ስልጠና ስራዎች አንጻር ተገቢነቱንና ጥራቱን ገምግሟል። በመድረኩ ሙስናን ለመከላከል የሥነ-ምግባር ግንባታ ስራ ዋነኛውና ቀዳሚው መሆኑ ተገልጿል፡፡ የሥነ-ምግባር ግንባታ ስልጠናዎችም ከመርሃ-ግብር ባለፈ በሰልጣኞች ላይ የባህሪና የአመለካከት ለውጥ የሚያመጡ መሆን እንዳለባቸው ተመላክቷል። የሥነ-ምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ስራዎችን ውጤታማነት ለማረጋገጥ የስልጠናዎችን ጥራትና ተገቢነት በየደረጃው ማረጋገጥ አስፈላጊ መሆኑ ተነስቷል። የስልጠና ጥራትና ተገቢነት ማረጋገጥ በቀጣይ ለሚሰሩ የትውልድ ሥነ-ምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ስራዎች ስኬታማነት ጠንካራ መሰረት የሚጥል መሆኑም መገለጹን በኮሚሽኑ የፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

ኮሚሽኑ የስልጠና ተገቢነትና ጥራት ማረጋገጫ ኮንፈረንስ አካሄደ ********************** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስ
+7
ኮሚሽኑ የስልጠና ተገቢነትና ጥራት ማረጋገጫ ኮንፈረንስ አካሄደ ********************** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ የሰጣቸውን ስልጠናዎች ጥንካሬና ክፍተት የገመገመበት የስልጠና ተገቢነትና ጥራት ማረጋገጫ ኮንፈረንስ አካሂዷል። ኮሚሽኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለያዩ ደረጃዎች ለሚገኙ አካላት የሰጣቸውን ስልጠናዎች ከቅድመ-ዝግጅት ስራዎች ጀምሮ በስልጠና አሰጣጥ ሂደት እና ድህረ-ስልጠና ስራዎች አንጻር ተገቢነቱንና ጥራቱን ገምግሟል። በመድረኩ ሙስናን ለመከላከል የሥነ-ምግባር ግንባታ ስራ ዋነኛውና ቀዳሚው መሆኑ ተገልጿል፡፡ የሥነ-ምግባር ግንባታ ስልጠናዎችም ከመርሃ-ግብር ባለፈ በሰልጣኞች ላይ የባህሪና የአመለካከት ለውጥ የሚያመጡ መሆን እንዳለባቸው ተመላክቷል። የሥነ-ምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ስራዎችን ውጤታማነት ለማረጋገጥ የስልጠናዎችን ጥራትና ተገቢነት በየደረጃው ማረጋገጥ አስፈላጊ መሆኑ ተነስቷል። የስልጠና ጥራትና ተገቢነት ማረጋገጥ በቀጣይ ለሚሰሩ የትውልድ ሥነ-ምግባር ግንባታ እና የሙስና መከላከል ስራዎች ስኬታማነት ጠንካራ መሰረት የሚጥል መሆኑም መገለጹን በኮሚሽኑ የፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.

ከሙስናና ብልሹ አሰራር የጸዳ የግብር ሥርዓት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት መሠረት ነው! ********************* ግብር የአንድ ሀገር የልማትና የሉዓላዊነት የጀርባ አጥንት ነው። ይሁን እንጂ ይህ የገቢ ምንጭ ለሀገር ዕድገት እውነተኛ መሠረት መሆን የሚችለው የግብር ሥርዓቱ ከሙስናና ከብልሹ አሰራር የጸዳ ሲሆን ብቻ ነው። የግብር ሥርዓቱ ግልጽና ታማኝ ሲሆን፣ መሰብሰብ ያለበት የመንግሥት ገቢ ሳይባክንና በጥቂት ግለሰቦች እጅ ሳይገባ ለመሠረተ-ልማቶች ግንባታ ይውላል። ብልሹ አሰራር ባለበት ሥርዓት ውስጥ ሕግ አክባሪ ግብር ከፋዮች ይጎዳሉ፤ ታማኝ ያልሆኑት ደግሞ ያለአግባብ ይበለጽጋሉ። ከሙስና የጸዳ አሰራር ግን ለሁሉም ግብር ከፋይ እኩልና ፍትሐዊ መድረክ ይፈጥራል። ይህም የአገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች በሥርዓቱ ላይ እምነት ጥለው በስፋት እንዲሳተፉ የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ ያበረታታል። የግብር አሰባሰቡ ሂደት ዘመናዊ፣ ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት ሲሆን፣ ሕብረተሰቡ የሚከፍለው ግብር ለሀገር ልማት በትክክል መዋሉን ይረዳል። ይህም ዜጎች በግዴታ ሳይሆን በባለቤትነትና በኃላፊነት ስሜት ግብራቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ ያደርጋል። ስለሆነም የግብር ሥርዓታችንን በማጽዳት፣ ሙስናንና ብልሹ አሰራርን በጋራ በመታገል የሀገራችንን የኢኮኖሚ በማሳደግ የብልጽግና ጉዟችን ማፋጠን ይኖርብናል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ በቤተሰብ እና ማህበራዊ ተቋማት አማካኝነት ለማጎልበት በትብብር ለመሥራት የሚያስችል ምክክር ከወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ አመራሮች ጋር ተደርጓል ***************** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ በቤተሰብ እና ማህበራዊ ተቋማት አማካኝነት ለማጎልበት በትብብር ለመሥራት የሚያስችል ምክክር ከወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ አመራሮች ጋር አድርጓል፡፡ ኮሚሽኑ አገራዊ የፀረ-ሙስና ትግል ውጤታማ እና ዘላቂ እንዲሆን በትኩረት ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ የትውልድ ሥነምግባር ግንባታ ነው። በዚህ ወሳኝ አገራዊ አጀንዳ በርካታ ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉ ቢሆንም፣ በቀጣይ በትብብር የሚመራበት የአሰራር ሥርዓት እየተዘረጋ ይገኛል። ትውልዱን በሥነምግባር ማነጽ ከሥር መሠረቱ መሆን እንዳለበት እና ቤተሰብ እንዲሁም ቅድመ-መደበኛ እና መደበኛ የትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ከተለመደው የዕውቀት እና ክህሎት ግንባታ ባሻገር የመልካም ባህሪ ግንባታ በአርዓያነት የሚፈጽሙበት ተገማች አገራዊ የአሰራር ሥርዓት ማጠናከር የትብብሩ ትኩረት ጉዳይ እንደሆነ በውይይቱ ተመላክቷል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

የግንባታ ፈቃድ ለመስጠት 50 ሺህ ብር መደለያ የተቀበሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ **************** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) ግለሰቦቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር ህንፃ ውስጥ ነው። ዘነበ ንጉሴ የተባለው ግለሠብ በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድ የህንፃ መጠቀሚያ ባለሙያ ሲሆን፣ የግል ተበዳይ የግንባታ ፍቃድ ለማውጣት 100 ሺህ ብር ተጠይቀው በድርድር 50 ሺህ ብር ይዘው እንዲመጡ ተስማምተዋል። የግል ተበዳይ የደረሰባቸውን በደል ለክፍለ ከተማው ፖሊስ የወንጀል መከላከል መምሪያ በሰጡት ጥቆማ ተጠርጣሪው በክትትል አባሎች ገንዘቡን ሲቀበል እጅ ከፍንጅ ተይዟል። ከጉዳዩ ጋር ተሳትፎ የነበረው በክፍለ ከተማው የግንባታ ፈቃድ የመጠቀሚያ ፈቃድ ባለሙያ የሆነው አድምቀው ውቤ የተባለው ግለሰብ የግል ተበዳይን ጉቦ ካልከፈልክ አገልግሎት እንደማይሰጠው በመንገርና ለአንድ ወር በማጉላላት 50 ሺህ ብሩን እንዲሰጥ በማድረግ የማግባባት ስራ ሲስራ እንደነበር ፖሊስ ገልጿል። ህብረተሰቡ መብቱን በገንዘብ መግዛት እንደሌለበት ያሳሰበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መሰል የወንጀል ድርጊት ሲፈጸም ጉዳዩን በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (citizen engagement application) በመጠቀም መረጃ መስጠት እንደቻልም የከተማው ፖሊስ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል፡፡ ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

አዋጅ ቁጥር 1425/2018 ዓ.ም ለሙሰኞች ወሳኝ መድሃኒት ነው! ******** የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው 24ኛ መደበኛ ስብሰባው የጉምሩክ አዋጅን ቁጥር 1425/2018 ዓ.ም መርምሮ አፅድቋል። እንዲህ አይነት የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚወጡ ጠንካራ የሕግ ማዕቀፎች የሀገርን ሀብትና የሕዝብን ጥቅም ለማስጠበቅ ትልቅ ሚና አላቸው። በተለይም ተጠያቂነትን በማስፈን፣ የአሰራር ግልጽነትን በመፍጠር እና የሀገርን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ የዕድገት ጉዞ በመደገፍ ረገድ ፋይዳቸው ከፍተኛ ነው። ​ እንዲሁም የሰውና የገንዘብ ግንኙነትን የሚቀንሱ የዲጂታል አሰራሮችን በስፋት መዘርጋት ለሙስና ቀዳዳዎችን ሁሉ ይደፍናሉ። ግልጽ የሆኑ የቴክኖሎጂ አሰራሮች መረጃን ለሕዝብ ተደራሽ ስለሚያደርጉ የተጠያቂነት ስርዓቱን ያጠናክራሉ። ​ለዚህ ደግሞ ሕጉን የሚያስፈጽሙ አካላት ሙሉ በሙሉ ነፃ፣ ገለልተኛና በጠንካራ የሰው ኃይልና ቴክኖሎጂ የተደራጁ መሆን አለባቸው። ሕግ ባለበት አቅምና ቁርጠኝነት ሲታከልበት ለውጡ ፈጣን ይሆናል። ዛሬ የጸደቀው አዋጅ እቃዎችን ለመደበቅ የሚያስችል ቴክኖሎጂ የተገጠመለት ሲሆን፣ ተሽከርካሪ እና ሙሉ በሙሉ የኮንትሮባንድ እቃ ጭኖ ሲጓጓዝ የተገኘ አካል ንብረቱ እንዲወረስ ደንግጓል፡፡ ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ(ፒ.ኤች.ዲ) ከኮሪያ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (KOIKA) የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሄዱ ************************ (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 02/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ(ፒ.ኤች.ዲ) ከኮሪያ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (KOIKA) የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ቀጣይነት ያለው ሥራ በጋራ ለመስራት ውይይት አካሂደዋል፡፡ በውይይቱም በፀረ-ሙስና ህጎች ትግበራ፣ በተቋማት የጥቅም ግጭት መከላከል፣ በሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፣ በሀብት ምዝገባ መረጃ የማጣራት አፈጻጸም፣ በተቋማት ኃላፊዎች የሥነምግባር ኮድ አፈፃፀም፣ በፀረ-ሙስና ትግል ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራ ተመላክቷል። የኮሪያ የሥነምግባር ግንባታና የፀረ-ሙስና ትግል ልምድ ለሀገራችን ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለውና ትግሉን በውጤታማነት ለመምራት እንደሚያግዝ ተጠቁሟል፡፡ እንዲሁም ሙስናን ለመከላከል ዲጂታል አሰራሮችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ የተጠቆመ ሲሆን፣ ይህም የሀገር ውስጥ ኢንቨስትምንትን ለመሳብ አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጠርና ለሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጽኦ እንዳለው ተገልጿል፡፡ ኮሚሽኑ እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (KOIKA) በትብብር የሚሰሩ ሲሆን፣ በዚህም ለኮሚሽኑ የሥራ ኃላፊዎች በኮሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

ማዕከሉ የብልሹ አሰራርና የሙስና ስጋቶችን በመቅረፍ ረገድ ያለውን ሚና ከፍተኛ ነው - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ************************ (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሰኔ 02/2018 ዓ.ም) በክልሉ ሁለተኛ የሆነው የአርባምንጭ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ተገልጿል። በምረቃው የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ማዕከሉ መጀመሩ በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው ብለዋል። «መሶብ» የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተበታተነ መልኩና በባህላዊ አሰራር ሲሰጡ የነበሩ በርካታ የመንግስት አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማስደገፍ በአንድ ጣሪያ ስር የሚያስተሳስር በመሆኑ፣ ለዘመናት ህብረተሰቡን ሲያማርሩ የነበሩ የቢሮክራሲ ማነቆዎችን ሙሉ በሙሉ እንደሚፈታ ተናግረዋል። ይህ ማዕከል ዜጎች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውንና አላስፈላጊ ወጪያቸውን እንዲቆጥቡ ያደርጋል ብለዋል። አገልግሎቱ የመንግስትን አገልግሎት ተደራሽነትና ቀልጣፋነት ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር የህዝብን እርካታ እንደሚያረጋግጥ ያብራሩ ሲሆን፣ ማዕከሉ የብልሹ አሰራርና የሙስና ስጋቶችን በመቅረፍ ረገድ ያለውን ሚና ከፍተኛ መሆኑንም አብራርተዋል። የ«መሶብ» ሥርዓት ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መሠረተ ልማትና በቴክኖሎጂ የተደገፈ በመሆኑ፣ የአገልግሎት ሰጪና የነዋሪዎችን ቀጥተኛ ንክኪ በመቀነስ የአገልግሎት አሰጣጡን ግልጽ፣ ተጠያቂነት የሰፈነበትና ከሙስና የጸዳ እንደሚያደርገውም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል። ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት መዘርጋቱ ብቻውን በቂ እንዳልሆነ በመግለጽ፣ በማዕከሉ የሚመደቡ አመራሮችና ባለሙያዎች የህዝብ አገልጋይነት ስሜትን በተግባር ሊያሳዩ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበው፤ ይህንን የተቀናጀ አሰራር በላቀ የኃላፊነት ስሜትና በታማኝነት በመምራት የክልሉን ነዋሪዎች የዘመናት የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በዘላቂነት መመለስ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኢፌዴሪ ሲቭል ሰርቪስ ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ወ/ሮ አልማዝ መሰለ ፥ የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችንን ራዕይ ከማሳካት አንጻር እስካሁን 51 የ'MESOB' አንድ ማዕከላት በ11 ክልሎችና በ2ቱ ከተማ መስተዳድሮች ተመርቀው ወደ ስራ የገቡ ሲሆን፣ ዛሬ የሚመረቀው የአርባምንጭ ማዕከል ሲጨመር ቁጥሩን 52 እንደሚደርስ ገልፀዋል። በክልሉ ከወላይታ ሶዶ ማዕከል ቀጥሎ የአርባምንጭ መሶብ 2ኛው ወደ አገልግሎት የገባ ማዕከል ሲሆን፣ ይህም ሃገራችን አገልግሎቶችን ተደራሽ እና ግልጽ ከማድረግ አንጻር አንድ ደረጃ ከፍ ያደርጋታል ነው ያሉት። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቃሬ በበኩላቸው ይህ ማዕከል የዲጂታል ሕልም ፍቺ ነው ያሉ ሲሆን፣ መንግስት መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የገባውን ቃል መተግበሩን የሚያሳይ ምስክር መሆኑን አስገንዝበዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አራት የፌደራል እና አምስት የክልሉ ቢሮዎች 32 አገልግሎቶች እንደሚሰጡ ገልፀው፤ ከዚህ በፊት ዜጎች የሚገጥማቸውን እንግልት በጥራትና ፍጥነት የሚሰጥ መሆኑን መገለፃቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል፡፡ ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

መልካም ሥነምግባርን መርህ ያደረገ የአገልግሎት አሰጣጥ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ያለው አስተዋጽኦ ላቅ ያለ ነው! ******* ​መልካም ሥነምግባርን መሠረት ያደረገ የአገልግሎት አሰጣጥ ለአንድ ተቋምም ሆነ ለሀገር ዕድገት የጀርባ አጥንት ነው። ይህ መርህ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን ከጅምሩ ለማጥፋት የሚኖረው አስተዋጽኦ እጅግ ላቅ ያለ ከሚሆንባቸው ምክንያቶች የሚከተሉት ተጠቃሽ ናቸው። 👉 ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፍናል፦ የሥነምግባር መርሆዎች በሥራ ቦታ ላይ ሲሰርጹ፣ እያንዳንዱ የሕዝብ አገልጋይ ለሚሰጠው ውሳኔና አገልግሎት ኃላፊነት መውሰድን ይለምዳል። አሠራሮች ግልጽና ለሕዝብ ክፍት ሲሆኑ፣ በምስጢርና በድብቅ የሚሰሩ የሙስና እና የጥቅም ግጭት ዕድሎች ይዘጋሉ። ​👉 ለአድሎዓዊ አሰራር በር ይዘጋል፦ ሙስና የሚፈጸመው "ሰውን በሰው" አሊያም ባልተገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት ነው። መልካም ሥነ-ምግባር ደግሞ ሁሉንም ዜጋ በእኩልነት፣ በቅንነት እና በፍትሃዊነት ማስተናገድን ያስገድዳል። ይህም አድሎዓዊነትን ያስቀራል። ​👉 የተቋማትን ታማኝነትና የሕዝብ አመኔታን ይገነባል፦ አንድ ተቋም ቀልጣፋ፣ ፍትሃዊ እና ከሙስና የፀዳ አገልግሎት ሲሰጥ፣ ተገልጋዩ ማኅበረሰብ በተቋሙ ላይ ያለው አመኔታ ይጨምራል። ይህ አመኔታ ደግሞ ሕዝቡ ራሱ የብልሹ አሠራር ተባባሪ ከመሆን ይልቅ፣ ሙስናን በጋራ የሚዋጋና የሚያጋልጥበትን ንቃተ-ሕሊና ይፈጥራል። ​👉 የሀብት ብክነትን ይከላከላል፦ ሙስና እና ብልሹ አሠራር የሀገርንና የሕዝብን ውስን ሀብት ለጥቂት ግለሰቦች ፍላጎት ማሟያ ያደርጋሉ። በአንጻሩ በሥነ-ምግባር የታነጸ አገልጋይ የሕዝብን ሀብትና ንብረት እንደ ገዛ ንብረቱ በመቆጠብ፣ ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል ያደርጋል። ​በአጠቃላይ፣ ሙስናን በሕግና በቅጣት ብቻ ማጥፋት ስለማይቻል፤ ዘላቂው መፍትሔ በየደረጃው በሚገኘው አመራርና ሠራተኛ ልብ ውስጥ መልካም ሥነ-ምግባርን እና የሐቀኝነትን ባህል መገንባት ነው። ስለሆነም ተቋማት መልካም ሥነምግባርን መርህ ያደረገ አገልግሎት ለተገልጋዩ ህብረተሰብ በመስጠት እና ሙስናና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ተቋማቸውን ውጤታማ ማድረግ ይኖረባቸዋል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

እጁ ንጹህ የሆነ ሰውና በስልጣኑ ማግበስበስ የማይፈልግ ሰው በሆኑ ኃይሎች ሊጠለፍ አይችልም! ****************** ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

በኮሚሽኑ በየአስራ አምስት ቀን የሚዘጋጀው ዲጂታል የፀረ-ሙስና ጋዜጣ *** ዲጂታል ጋዜጣውን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ 👇 https://heyzine.com/flip-book/0fcd16fbb0
በኮሚሽኑ በየአስራ አምስት ቀን የሚዘጋጀው ዲጂታል የፀረ-ሙስና ጋዜጣ *** ዲጂታል ጋዜጣውን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ 👇 https://heyzine.com/flip-book/0fcd16fbb0.html ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

አሰራርን ከግል ፍላጎት ማጽዳት ለሙስና መከላከል ዋነኛው መፍትሔ ነው! ******* ​ አሠራርን ከግል ፍላጎት ለማጽዳት ውሳኔዎችን በግለሰቦች ፍላጎት ሳይሆን ግልጽ በሆኑ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና ደረጃዎች ላይ የተመሰረቱ እንዲሆኑ ማድረግ ይገባል። ሙስና የሚመነጨው በአብዛኛው ግለሰቦች የተሰጣቸውን ኃላፊነት ተጠቅመው የራሳቸውን ወይም የዘመዶቻቸውን ፍላጎት ለማስቀደም ሰፊ ክፍተት ሲያገኙ ነው። ​አንድ አመራር ወይም ባለሙያ የሕዝብን/የተቋምን ኃላፊነት ከግል ወይም ከቤተሰብ የንግድ ጥቅም ጋር የሚያጋጭበትን ዕድል ሙሉ በሙሉ መዝጋት ይኖርበታል። አሠራር ከግል ተጽዕኖ ሲጸዳ ተቋማዊ ሥርዓቱ ግልጽና ሊተነበይ የሚችል ይሆናል። ማንኛውም ተገልጋይ ጉዳዩ የሚታይለት በጉዳዩ ይዘት ላይ ተመስርቶ እንጂ ሰጪውን አካል በማወቅ ወይም ባለማወቅ ላይ መሆን የለበትም። ​ለዚህ ደግሞ ዲጂታላይዜሽን (በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሠራር) በመጠቀም ሰዋዊ ንክኪን በመቀነስ የግል ፍላጎትን ለማስቀደም የሚደረጉ ሙከራዎችን በቀላሉ ለመቆጣጠር ያስችላል። ይህ መፍትሔ ተቋማዊ አደረጃጀትን ብቻ ሳይሆን የአስተሳሰብ ለውጥንም ይፈልጋል። የሕዝብ አገልጋይነትን ከግል ሀብት ማከማቻነት ለይቶ ማየት፣ የተቋምን ክብርና ተዓማኒነት ከግል ዝና በላይ ማስቀደምን ይጠይቃል። ​ሰዎችን መለወጥና መቆጣጠር አስቸጋሪ በሚሆንበት ጊዜ፣ ሥርዓቱን የማይበገር አድርጎ መገንባት ቀጣይነት ያለው የሙስና መከላከያ ስትራቴጂ ነው። ​አሠራርን ከግል ፍላጎት በማጽዳት ውሳኔዎችን ከግለሰቦች በጎ ፈቃድና ስሜት አውጥቶ፣ ሙሉ በሙሉ በተቋማዊ አዋጅና ደንብ፣ ግልጽ መመሪያና በቴክኖሎጂ ላይ በመመስረት ስራዎችን መስራት ይገባል። ይህም ሙስና የሚመነጨው ከአሠራር ክፍተትና ከግል የጥቅም ግጭት በመሆኑ፣ ሥርዓትን የማይበገር አድርጎ መገንባት ለሙስና ዕድል የማይሰጥ አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሔ ነው። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።