ar
Feedback
Federal Ethics And Anti- Corruption Commission

Federal Ethics And Anti- Corruption Commission

الذهاب إلى القناة على Telegram

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Federal Ethics And Anti- Corruption Commission

تُعد قناة Federal Ethics And Anti- Corruption Commission (@feacc) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 10 338 مشتركاً، محتلاً المرتبة 4 925 في فئة السياسة والمرتبة 3 223 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 10 338 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 25 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 293، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 12، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 12.03‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 6.56‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 1 244 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 678 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Use This Link For More Information https://twitter.com/EthiopiaFeacc https://www.youtube.com/channel/UCO_WiCAiDIkMMwqsZGK47nw/?guided_help_flow=5/ https://www.facebook.com/feaccOfficial/

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 26 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة السياسة.

10 338
المشتركون
+1224 ساعات
+807 أيام
+29330 أيام
أرشيف المشاركات
መቀጠል አለበት - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ **** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሐምሌ 18/2018 ዓ.ም) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የክልሉን የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ አጽድቋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የተከበሩ አቶ ጥላሁን ከበደ ኮሚሽኑ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የሚደርሱትን ጥቆማዎች መነሻ በማድረግ የሕዝብና የመንግስት ሀብት ከብክነት ለመከላከል ያከናወናቸው ተግባራት አበረታች ናቸው ብለዋል። ተቋሙ ገለልተኛ ሆኖ ኃላፊነቱን እየተወጣ ለመሆኑ የክልሉ መንግስት እዉቅና ይሰጣል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልፀዋል። በክልሉ ለተለያዩ የልማት ስራዎች የሚመደበው ኃብት በአግባቡ ስራ ላይ እንዲዉል የፀረ-ሙስና ትግሉ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መናገራቸውን ከኮሚሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ከዞኖች የሚመጡ ጥቆማዎችን በመቀበልና በመተንተን ተቋሙን የማጠናከርና በዲጂታል አሰራር የማስደገፍ ስራ በመስራት ውስን የሆነዉን የመንግስት ኃብት ማዳን እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ በሰጡት አስተያየት አሳስበዋል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details...። #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

መቀጠል አለበት - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ **** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሐምሌ 18/2018 ዓ.ም) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የክልሉን የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ አጽድቋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የተከበሩ አቶ ጥላሁን ከበደ ኮሚሽኑ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የሚደርሱትን ጥቆማዎች መነሻ በማድረግ የሕዝብና የመንግስት ሀብት ከብክነት ለመከላከል ያከናወናቸው ተግባራት አበረታች ናቸው ብለዋል። ተቋሙ ገለልተኛ ሆኖ ኃላፊነቱን እየተወጣ ለመሆኑ የክልሉ መንግስት እዉቅና ይሰጣል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልፀዋል። በክልሉ ለተለያዩ የልማት ስራዎች የሚመደበው ኃብት በአግባቡ ስራ ላይ እንዲዉል የፀረ-ሙስና ትግሉ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መናገራቸውን ከኮሚሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ከዞኖች የሚመጡ ጥቆማዎችን በመቀበልና በመተንተን ተቋሙን የማጠናከርና በዲጂታል አሰራር የማስደገፍ ስራ በመስራት ውስን የሆነዉን የመንግስት ኃብት ማዳን እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ በሰጡት አስተያየት አሳስበዋል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details...። #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

300 ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሱት ግለሰብ ምስጋና ተቸራቸው **************** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም) በአማራ ክልል ደሴ ከተማ የ‘ሒጀር ሬስቶራንት’ ባለቤት የሆኑት አቶ
300 ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሱት ግለሰብ ምስጋና ተቸራቸው **************** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም) በአማራ ክልል ደሴ ከተማ የ‘ሒጀር ሬስቶራንት’ ባለቤት የሆኑት አቶ ኡመር እሸቱ በስህተት ወደ ባንክ ሂሳባቸው ገቢ የተደረገን 300 ሺህ (ሦስት መቶ ሺህ) ብር ለባለቤቱ በመመለስ የታማኝነትና የቅንነት አርዓያነትን አሳይተዋል። በስህተት 300 ሺህ ብር በባንክ አካውንታቸው የገባላቸው አቶ ኡመር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መናፈሻ ቅርንጫፍ በአካል በመገኘት ለገንዘቡ ባለቤት ለአቶ ሁሴን አህመድ ገቢ እንዲሆን ማድረጋቸው ተገልጿል። አቶ ኡመር ያሳዩት ተግባር የታማኝነትና ቅንነት እሴትን የሚያጎላና ለሌሎችም መልካም አርዓያ በመሆኑ ምስጋናና አክብሮት ይገባቸዋል ሲል የከተማው የመንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ዘግቧል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

ግንዛቤ ያሳድጉ፣ አስተያየት ይስጡበት! **** የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር የፀረ-ሙስና ሥርዓት ግንባታ እንደአንድ የምክክር አጀንዳ ለይቶ በማቅረቡ፣ ተመካካሪዎች እየመከሩበት መሆኑ ይታወቃል። ይህ በአገራችን የተቋማት የሙስና ችግር የመቋቋም እና የትውልድ ሥነምግባር ብልሽት የማስተካከል ምክረ-ሐሳብ የሚገኝበት እና መግባባት የሚፈጠርበት ታላቅ ምዕራፍ ነው። በኢትዮጵያ ሕዝብ በቂ ቅቡልነት ያለው የፀረ-ሙስና ትግል ሥርዓት ግንባታ የማስጀመሪያ ምዕራፍ ተደርጎ መታየት ይችላል። ዘንድሮ የኢትዮጵያ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን 25ኛውን ዓመት ምሥረታ እያከበረ ባለበት፣ ይህ ታሪካዊ መድረክ መፈጠሩ፣ ቀጣዩን ጉዞ ለማደስ የላቀ ዕድል ይፈጥራል። የፀረ-ሙስና ትግል ባለድርሻዎች በቀዳሚነት ዜጎች ናቸው። ዜጎች፣ ሥነምግባራዊነት የመላበስ እና ሙስናን በጽናት የመታገል አገራዊ ግዴታ አለባቸው። ይህን በተግባር ማረጋገጥ የሚቻለው ብቁ የፀረ-ሙስና ትግል ሥርዓት በመዘርጋት ብቻ ነው። አልያም፣ መፈክር ብቻ ሆኖ ይቀራል። በተቋማት ደረጃ፣ ሁሉም የመንግሥት አካላት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ የትምህርትና ማህበራዊ ተቋማት፣ ሚዲያ፣ ሲቪክ ማህበራት፣ እንዲሁም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አደረጃጀቶች እና የቢዝነስ ድርጅቶች መሆናቸውን መመልከት ይቻላል። የፀረ-ሙስና ትግል የሀገር ህልውና የማስጠበቅ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ልብ ማለት ያስፈልጋል። ከዚህ በታች አሳንሶ ማየት፣ ምናልባትም አገር ያለመችውን የብልጽግና ጉዞ አሳንሶ ከማየት ባሻገር፣ የአገር ሰላምና ዲሞክራሲ ግንባታን የሚያስተጓጉል ይሆናል። ሙስና አደገኛ ካንሰር ነው። ተቋማትን እንደነቀዝና ካንሰር ከሥር ቦርቡሮ ባዶ የሚያደርግ ጨካኝ ጉዳይ ነው። ተቋማት የዜጎች እና የሕዝብ የጋራ ሀብት እስከሆኑ፣ በጋራ ከሙስና የመታደግ ግዴታ ማበጀት ያስፈልጋል። ማንም ችግሩን ከዳር ቆሞ መመልከት አይገባም፤ ይልቁን ተባብሮ በመታገል አሽቀንጥሮ መጣል ያስፈልጋል። ከሥሩ መንቀል ግድ ይላል። ይሁን እንጂ፣ የፀረ-ሙስና ትግል የመንግስት ወይም አስፈጻሚው አካል ብቻውን የሚከላከለው ተደርጎ አጥብቦ የመረዳት ሁኔታዎች ይስተዋላሉ። በባለድርሻነት የተዘረዘሩት ተቋማት፣ በቅድሚያ የራሳቸውን ተቋማዊ አሰራር ሥርዓት የግልጽነትና ተጠያቂነት ባህል ማላበስ ይጠበቅባቸዋል። በጋራ ተቀናጅተው የአገር ህልውና ሥጋት የሆነውን ሙስና ያለማመንታት በባለቤትነት መታገልና መግታት ይገባቸዋል። በሌላ በኩል፣ የሙስና ወንጀል ከላይ በተዘረዘሩት ተቋማት ውስጥ በተሰገሰጉ ግለሰቦች ቢፈጸም የሕግ እና አስተዳደራዊ ተጠያቂነትን በግልጽነት እና ያለአድሎ ማረጋገጥ የግድ ያስፈልጋል። የሙስና ወንጀል ውስብስብነት፣ ሚስጢራዊነት እና ጣልቃ ገብነት የመከላከል እና ሕግ የማስከበር ሚና በተቀላጠፈ እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማከናወን ነጻና ገለልተኛ የሆነ አገራዊ ጥርስ ያለው የፀረ-ሙስና ኮሚሽን መፍጠር ዘመኑ የሚመጥን የብልህ እርምጃ ይሆናል። ለኢትዮጵያ የሚበጀው፣ ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን የሚያጠናክር፣ የሕግ የበላይነትን የሚያረጋግጥ፣ በየትኛውም የሥልጣን እርከን ያለ ግለሰብ እና የጥቅም ትስስር ቡድን ሙስና ወንጀል መፈጸሙ ቢጠረጠር እውነተኛ ማስረጃ በማመንጨት መርምሮ፣ ከሶና አስቀጥቶ፣ በሙስና የተመዘበረ ሀብት ከአገር ውስጥም ሆነ ከውጭ አገር መዳረሻዎች በውጤታማነት የሚያስመልስ ጥርስ ያለው የሕዝብ ቅቡልነትና ታማኝነት የሚያረጋግጥ ተቋማዊ ብቃት ለመፍጠር አገራዊ የጋራ መግባባት የሚያስፈልግበት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሰናል። የፀረ-ሙስና ትግል የሁሉም ባለድርሻዎች የጋራ እና አገራዊ ኃላፊነት በመሆኑ፣ ሁሉም የበኩሉን ሚና እንዲወጣ መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች በሕገ-መንግስቱ ጭምር በማመላከትና የፀረ-ሙስና ተለዋዋጭ ሁኔታን የሚያስተናግድ የመደበኛ ህጎች ተፈጻሚነት ማላቅ ለኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ አንገብጋቢ ሆኖ ይታያል። የኢትዮጵያ የፀረ-ሙስና ትግል ለመምራት ወሳኝ የሆኑ ዓለምአቀፍ ስታንዳርድ የሚያሟሉ እና አገራዊ ተጨባጭ ሁኔታዎችን ያማከሉ አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ያሉ ቢሆንም የማስፈጸም ውስንነት ይታይባቸዋል። ሕጎችን በላቀ ሁኔታ በማስፈጸም የሙስና ወንጀል ሕግ በውጤታማነትና ያለአድሎ ለማስከበር ምን ምን ማሻሻያዎች ያስፈልጋሉ? የእርስዎን ገንቢ አስተያየት ይስጡበት። ኢትዮጵያ እየመከረች ነው! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details...። #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

በኮሚሽኑ በየአስራ አምስት ቀን የሚዘጋጀው የሐምሌ ወር 1ኛ ዙር ፀረ-ሙስና ዲጂታል ጋዜጣ * ሙሉ ዲጂታል ጋዜጣውን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ 👇 https://heyzine.com/flip-book/5ec9
በኮሚሽኑ በየአስራ አምስት ቀን የሚዘጋጀው የሐምሌ ወር 1ኛ ዙር ፀረ-ሙስና ዲጂታል ጋዜጣ * ሙሉ ዲጂታል ጋዜጣውን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ 👇 https://heyzine.com/flip-book/5ec9c56839.html ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details...። #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

የኮሚሽኑ አመራሮች እና ሠራተኞች የደም ልገሳ መርሐ ግብር አካሄዱ **************** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራሮች እና ሠራተኞች በተለያየ ምክንያት ደም ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች የደም ልገሳ ኘሮግራም አካሂደዋል። መርሃ ግብሩ፣ ኮሚሽኑ በየዓመቱ የሚያካሂደው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አንዱ ተግባር ሲሆን፣ በህክምና ተቋማት ውስጥ የሚስተዋለውን የደም አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍና አስቸኳይ የህክምና ክትትል ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ፈጣንና አስተማማኝ ህይወት አድን ድጋፍ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። በቀጣይም ሌሎች የክረምት በጎ አድራጎት ተግባራት በተያዘላቸው መርሐ ግብር የሚካሄዱ ይሆናል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

photo content
+8

photo content
+9

የዲጂታል ሪፎርሙ በአዲስ አበባ የመሬት ዘርፍ ብልሹ አሰራርን በመቀነስ ገቢን አሳድጓል ****** ​ (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) በአዲስ አበባ የተተገበረው የዲጂታል ሪፎርም የመሬት አገልግሎትን በማዘመን፣ ብልሹ አሰራርን በመቀነስና የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱን በማጠናከር ውጤታማ ለውጥ ማምጣቱን የከተማው መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ገለጸ። የቢሮው ኃላፊ መኮንን ያኢ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን ሪፎርም ተከትሎ በከተማው የመሬት አገልግሎትን ዘመናዊ፣ ግልጽና ከሰው ንክኪ የተላቀቀ ለማድረግ ሰፊ የለውጥ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በሪፎርሙ ማዕቀፍ ከ720 ሺህ በላይ የመሬት ማህደራት ስካን ተደርገው ወደ ዲጂታል መረጃ ቋት መግባታቸውን ገልጸው፤ የመረጃ ደህንነትን ከማጠናከር ባለፈ ህገ ወጥ የካርታ ዝግጅትና የመሬት ወረራ ወንጀሎችን ለመቀነስ አስተዋፅኦ አበርክቷል ብለዋል። በተጨማሪም የመሬት አገልግሎቶችን በኦንላይን ስርዓት በማቅረብ የአገልግሎት ፍጥነትን ከማሳደግ በተጨማሪ ለሙስናና ብልሹ አሰራር የነበረውን ተጋላጭነት በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱን ገልጸዋል። በዘጠኝ ወራት ውስጥ 39 ሺህ የሚጠጉ ኢ-ካርታዎች መዘጋጀታቸውን ጠቅሰው፤ የይዞታ መረጃዎችም በዲጂታል ስርዓት እንዲመዘገቡና እንዲጠበቁ መደረጉን አመልክተዋል። በአስራ አንዱ ክፍለ ከተሞች ተበታትኖ የነበረውን የመሬት ቤዝማፕ ወደ አንድ ማዕከላዊ የመረጃ ቋት ማምጣት መቻሉንም ጨምረው አብራርተዋል። አቶ መኮንን እንዳሉት፤ ቢሮው በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ የተቀናጀ የመሬት መረጃ ስርዓት ወደ ስራ በማስገባት የሁለተኛ የመብት ፈጠራ፣ የካርታ ድርርቦሽና ሌሎች የማጭበርበር ሙከራዎችን ከመፈጸማቸው በፊት የሚለይና ለባለይዞታዎች ማስጠንቀቂያ የሚሰጥ የቴክኖሎጂ አቅም ገንብቷል ብለዋል። በአዲስ መሶብ አገልግሎት ማዕከላት 14 የመሬት አገልግሎቶችን ወደ ዘመናዊ የአንድ ማዕከል ስርዓት በማስገባት በቀጣዮቹ 90 ቀናት በአስራ አንዱም ማዕከላት ሙሉ በሙሉ እንዲሰጡ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አሰራሩ የአገልግሎት መዘግየትን በመቀነስ ሙስናን ለመግታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት አመልክተዋል። በመሬት ዘርፉ የሚፈጸሙ ህገ ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከልና ተጠያቂነትን ለማስፈን በርካታ አመራሮችና ሠራተኞች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ገልጸው፤ ይህም አገልግሎቱን ግልጽ፣ ተጠያቂና ለተገልጋዮች አስተማማኝ ለማድረግ ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር እንደሚገባ የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ ******************************* (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሀምሌ 10/2018 ዓ.ም) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አና የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ሁለተኛ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ገምግሟል። በመድረኩ የተገኙት የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ተወካይ አቶ ግርማ ጊቻሞ በክልሉ ተቋማትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማዘመን የብልሹ አሰራር ችግሮችን ለመፍታት የተደረገው ጥረት ውጤት እያመጣ ነው ብለዋል። ኮሚሽኑ 336 ሚሊዮን በላይ የሚገመት ብር በቅድመ መከላከል እንዲሁም ተመዝብሮ የነበረውን የህዝብ እና የመንግስት ሀብት ማዳን መቻሉ አበረታች መሆኑንም ተናግረዋል። የሥነምግባር ባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ ተጠያቂነት ማስፈን ላይ አሰራሩን ማጠናከር ተገቢ ነው፤ የተቋም አሰራር ወጥነትና ተቀራራቢነት እስከታችኛው መዋቅር ድረስ መጠናከር እንዳለበት ገልፀዋል። የሀገር ኢኮኖሚያዊ ሀብት የሚያወድመውን ሙስናን መታገልና ተጠያቂነት ማስፈን ጠንካራ ትግል የሚጠይቅ ነው፤ ለዚህም ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር ይገባል ብለዋል። ከሀብት ምዝገባ አንፃር ለውጥ መኖሩን አንስተው፣ ባላስመዘገቡት ላይ ተጠያቂነት የማስፈን ሥራው ተጠናክሮ መሠራት እንዳለበት አሳስበዋል። ኮሚሽኑ ሙስናና ብልሹ አሰራር ችግሮች በመፍታት ተጠያቂነትን በማስፈን የህዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመረውን ተግባር አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ ማሞ ቴጋ በበኩላቸው ተቋማዊ የሙስናና ብልሹ አሰራርን አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል አሰራር ስርዓት ለመዘርጋት በቅንጅት እየተሰራ ነው። ኮሚሽኑ ከመከላከል ባለፈ የሙስና ወንጀል ሲፈፀም ክትትል በማድረግ ለፍትህና ለፖሊስ አካላት የማሳወቅ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልፀው፣ የህግ ተጠያቂነት ስራው በሌላ ተቋም የሚፈፀም መሆኑ ውስንነቱን ለማረም በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል። የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ገብሬ ጋጌ የሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ለማረጋገጥ የተጀመረው ስራ በሂደት ላይ ነው፡፡ በክልሉ ከ70 ሺ በላይ የትምህርት ማስረጃዎችን በማሰባሰብ በመንግስትና በግል ተቋም ለመፈተሽ በወረፋ ላይ መሆኑን መናገራቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

በኢኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን ባለሥልጣን የአየር ትራፊክ መቆጣጠሪያ(ATC) ታወር ግንባታ ግዥ የጨረታ ሂደት ላይ የፌደራል የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በአስቸኳይ የሙስና መከላከል ጥናት ምክረ ሀሳብ አቀረበ ****** (የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሐምሌ 08/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) በኢኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን ባለሥልጣን የአየር ትራፊክ መቆጣጠሪያ(ATC) ታወር ግንባታ ግዥ የጨረታ ሂደት ላይ የፌደራል የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በአስቸኳይ የሙስና መከላከል ጥናት ምክረ ሀሳብ አቀርቧል። ኮሚሽኑ በአዋጅ ቁጥር 1236/2013 አንቀጽ 7 ንዑስ አንቀፅ 4 መሠረት ሙስና ለመፈፀም የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ሲጠረጥር ወይም ጥቆማ ሲደርሰው ድርጊቱ ከመፈፀሙ በፊት አስቸኳይ የሙስና መከላከል ጥናት በማካሄድ ሂደቱ እንዲቋረጥ የማድረግ ስልጣን አለው፡፡ በዚህም፣ መሠረት በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን በያቤሎ በደብረማርቆስ እና በሚዛን አማን ኤርፖርት የአየር ትራፊክ መቆጣጠሪያ(ATC) ታወር ግንባታ ግልጽ ጨረታ ሂደት ላይ የአስቸኳይ ሙስና መከላከል ጥናት በማካሄድ ምክረ ሀሳብ አቅርቧል፡፡ በግዥ ሂደቱ፣ ለአየር ትራፊክ መቆጣጠሪያ (ATC) ማማዎቹ ግንባታ ግልጽ ጨረታ አየር ላይ የቆየባቸው ቀናት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የጨረታ በአየር ላይ የመቆየት ጊዜን የመወሰን ኃላፊነት ያለው ቢሆንም ሰፊ ተወዳዳሪዎችን ከመሳብ አንጻር የቆይታ ጊዜው ቢሰፋ የተሻለ አማራጭ ያሰፋል የሚልና በሌሎች የክልል ከተሞች የተገነቡና በግንባታ ሂደት ላይ ያሉ የታወር ግንባታዎች የጥራት ችግር አላስፈላጊ የጊዜ መጓተት መንግስትን ለተጨማሪ ወጪና የጊዜ ብክነት የዳረጉ መሆኑ በጥናት ግኝቱ የተመላከተ ነው፡፡ በኮሚሽኑ የሙስና መከላከል ጥናት ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ እሸቴ አስፋዉና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ደንጌ ቦሩ፣ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ዋና ዳሬክተር አቶ ዮሃንስ እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የግዥ ጨረታ ሂደቱና አፈጻጸሙ የጥናት ግኝትና ምክረ ሀሳብ ሪፖርት ቀርቦ ዉይይት የተደረገ ሲሆን፣ በቀረቡት ግኝቶችና ምክረ ሀሳቦች መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ በቀጣይ በተቋሙ የሚከናወኑ የግዥ ሂደቶች ከሙስና እና ብልሹ አሠራር የጸዱ ሆነው እንዲፈጸሙ የሚያስችል ምክረ-ሐሳብ ተሰጥቷል። በተለይ በአየር ትራፊክ መቆጣጠሪያ(ATC) ታወር ሥራ ላይ የሚስተዋሉ የጥራትና በተቀመጠላቸው የጊዜ ሰሌዳ አለመጠናቀቅ ችግሮችን አመራሩ በየጊዜው ክትትል ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተመላክቷል፡፡ ለአብነት የአሶሳ፣ የጋምቤላና የሰመራ ታወር ግንባታ ተጠቃሽ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡ ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

photo content
+6

በሙስናና ብልሹ አሰራሮች ላይ ተሳትፈዉ በተገኙ 5 ሺህ 857 አመራሮችና ሠራተኞች ላይ እርምጃ ተወስዷል ****** ​ (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሐምሌ 5/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ) ሌብነትን፣ ዳተኝነትን እና የህዝብ እንግልትን በማስወገድ ጠንካራ የተጠያቂነት ሥርዓት ለማስፈን በተወሰደ እርምጃ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 5 ሺህ 857 አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ተገልጋዮች ላይ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2018 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም ሪፓርት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት ፤ አገልግሎት አሰጣጥን ግልፅና ተጠያቂነት የሰፈነበት ለማድረግ፣ አስተዳደሩ በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በኩል አዳዲስ አሰራሮችን ዘርግቷል። እነዚህም “አገልጋዩ” ፕሮግራም አመራሩ ከሕዝብ ለሚነሱ ጥያቄዎች በቀጥታ ስርጭት ምላሽ የሚሰጥበት እንዲሁም “ዋርካ” ፕሮግራም አገልጋዩ እና ሕዝቡ በአካል ተገናኝተው ፊት ለፊት የሚጠያየቁበት የውይይት መድረኮች ናቸው። በእነዚህ የሚዲያ መድረኮች ከተነሱት የተገልጋይ ጥያቄዎች እና ቅሬታዎች መካከል 89 በመቶ የሚሆኑት አፋጣኝ ምላሽ አግኝተው መፈታታቸውን ከንቲባዋ አመላክተዋል። ይህ አሰራር በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ሥር ሰዶ የቆየውን ዳተኝነት በመቅረፍ፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ክፍተት በፈጠሩ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ላይ አስተማሪ እርምጃ እንዲወሰድ አስችሏል ብለዋል። ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን በተጨባጭ ለመታገል በተያዘው ቁርጠኛ አቋም፣ በጥፋት ላይ ተሰማርተው በተገኙ 5 ሺህ 857 አካላት ላይ እንደ ጥፋታቸው ክብደት ከማስጠንቀቂያ እስከ ስንብት እና በህግ ተጠያቂ ማድረግ የሚደርሱ እርምጃዎች ተወስደዋል። እነዚህም 79 ሹመኛ አመራሮች፣ 213 ዳይሬክተሮች እና የቡድን መሪዎች፣ 5 ሺህ 430 ባለሙያዎች እንዲሁም 135 ተገልጋዮች መሆናቸውን ገልጸዋል። ተጠያቂነትን የማስፈን ስራ የመንግሥት ተቋማትን ብቃት እና አገልግሎት አሰጣጥ ወደ ተሻለ ደረጃ ያሸጋገሩ ውጤቶች ሆነው መመዝገባቸው በሪፓርቱ መገለጹን አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል። ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

photo content
+3

በኮሚሽኑ በየአስራ አምስት ቀን የሚዘጋጀው የሰኔ ወር 2018 ዓ.ም 2ኛ ዙር ዲጂታል የፀረ-ሙስና ጋዜጣ ****************** ሙሉ ዲጂታል ጋዜጣውን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ👇 h
በኮሚሽኑ በየአስራ አምስት ቀን የሚዘጋጀው የሰኔ ወር 2018 ዓ.ም 2ኛ ዙር ዲጂታል የፀረ-ሙስና ጋዜጣ ****************** ሙሉ ዲጂታል ጋዜጣውን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ👇 https://heyzine.com/flip-book/3a86d6d925.html ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

ኢትዮጵያ ለፀረ-ሙስና ሥርዓት ግንባታ አስቻይ ሁኔታ የሚፈጥር ወሳኝ አገራዊ ምክክር ልታደርግ ነው። ስለሆነም፣ የኢትዮጵያ የፀረ-ሙስና ትግል ሥርዓት ምን ዓይነት ቅርጽ እንዲይዝ ይፈልጋሉ። ገንቢ አስተያየትዎን በነጻነት ያካፍሉ! ****** ​ ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር! የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾 #NCRS ሞባይል መተግበሪያ #ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች https://play.google.com/store/apps/details... #ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231 ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/ ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/ ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/@federalethicsanti-corrupti149 ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።