uk
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Відкрити в Telegram

Показати більше
1 740
Підписники
Немає даних24 години
+17 днів
-630 день
Архів дописів
photo content
+5

በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት አማካኝነት ለኮሌጁ አስተዳደር ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው የሁለተኛ ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከድሬዳዋ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ለመስራት በገባው ውል መሰረት ለ2ኛ ዙር ለኮሌጁ የአስተዳደር ሰራተኞች ለ5 ቀናት ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል:: የአቅም ግንባታ ስልጠናው በEASE(Education and Skills for Employ Ability) ፕሮጀክት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን ይህ ስልጠናም በኢንስቲትዩቱ አሰልጣኞች ሲሰጥ የቆየና በአገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነት እና በስራ ሥነ-ምግባር ላይ ያተኮረ ስልጠናም ነበር:: የስልጠናው ዋነኛ አላማ የኮሌጁ የአስተዳደር ሰራተኞች የተለያዩ የስራ ላይ ስልጠናዎችን አግኝተው አቅማቸውን እንዲገነቡና በተመደቡበት የስራ ዘርፍ የተሻለ አገልግሎት በመስጠት ለተቋሙ ራዕይና ስኬት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ለማስቻል መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም ለስልጠናው ውጤታማነት የድሬዳዋ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት እያደረገ ላለው ትብብርም ምስጋና አቅርበዋል። በ2ኛ ዙር ስልጠናው ማጠቃለያ መርሀ-ግብር ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀይር ሀጂኑር አንደገለፁት ቢሮው ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንዱ በአስተዳደሩ የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች እና አመራሮችን በተለያዩ ስልጠናዎች አቅማቸውን መገንባት እንደሆነ ጠቅሰው ለዚህም ኮሌጁ ከኢንስቲትዩቱ ጋር በጋራ ለመስራት ውል ተፈራርሞ ወደ ትግበራ በመግባቱ አመስግነው ሰልጣኞችም የወሰዳችሁት ስልጠና በስራ ገበታቸው ላይ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል:: ኮሌጁ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ሲያደግና የተሰጠውን Resource ተፈፃሚ ለማድረግ አጠቃላይ የኮሌጁን ሰራተኛ ባስተፈ መልኩ በመሆኑ በEASE ፕሮጀክትም ቅድሚያ ትኩረት የተሰጠው ተግባር የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ለሰራተኛው መስጠት እንደሆነ የገለፁት የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ የሆኑት አቶ ፋሲል ማዘንጊያ አክለውም በቀጣይ በዝርዝር የተለዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች በተያዘላቸው መርሃ-ግብር ለሰራተኛው የሚሰጡ ይሆናልም ብለዋል:: የማጠቃለያ መርሃ-ግብሩ ላይ ስልጠናው በአግባቡ ተከታትለው ላጠናቀቁ ሰልጣኞች ከእለቱ ክብር እንግዶች የምስክር ወረቀት የተበረከተላቸው ሲሆን በቀጣይ ሶስተኛ ዙር ሰልጣኞችም ስልጠናውን የሚወስዱ ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት አማካኝነት በተቋሙ በሚከናወኑ Building & Infrastructure Renovation ስራዎች ላይ ውይይት ተካሄደ:: በመድረኩ በኮሌጁ አጠቃላይ የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን 21ኛውን ክፍለ ዘመን ባማከለ መልኩ ሳቢና ለስልጠና ምቹ ከማድረግ አንፃር የሚያስፈልጉ የRenovation ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በባለሙያዎች ተለይቶ ቀርቧል:: በዚህም በቀረበው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ላይ የኮሌጁ ማኔጅመንት ጨምሮ የስልጠና ክፍል ተጠሪዎችና የኮንስትራክሽን ዲፖርትመንት አ/መምህራን ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በዚህም በጥናቱ ላይ ሊካተቱ ይገባል ያሏቸውን ነጥቦችና ማሻሻያ ያስፈልጋቸዋል ባሏቸው ጉዳዮች ላይ ለጥናቱ ግብአት የሚሆኑ ሀሳቦችንም አስቀምጠዋል:: የRenovation ትግበራው የEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 5 አመት ከሚከውናቸው ትግብራዎች አንዱ ሲሆን ፕሮጀክቱ በተቋሙ በሚኖረው ቆይታም መሰል ተግባራትን የሚያካትት መሆኑም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም

photo content
+9

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 ዓ.ም የሩብ አመት የድጋፍ፣ክትትልና ግምገማ ተካሄደ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ በሚገኙ ዋና ስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎች ላይ በበጀት አመቱት የሩብ አመት የድጋፍ፣ክትትልና ግምገማ መርሃ-ግብር አካሂዷል:: የድጋፍ፣ክትትልና ግምገማ መመሪያው በቼክሊስት መልክ የተዘጋጀ ሲሆን ይህን መነሻ በማድረግም በበጀት አመቱ ለዋና ስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎች በተሰጡ የቁልፍ ውጤት አመላካች እስትራቴጂክ ተግባራት አንፃር የተገኘውን አፈፃፀም ለመገምገም እንዲሁም በአተገባር ወቅት የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር ወደሌሎች ክፍሎች ለማስፋት የታለመ መሆኑ ተግልፇል:: የድጋፍ፣ክትትልና ግምገማውን የኮሌጁ ማኔጅመንትና የISO Task force በጋራ በመሆን እንዲሁም ቼክሊስቶችን በማዘጋጀት በስራ ሂደቶችና ክፍሎች በመገኘት የበጀት አመቱ የሩብ አመቱን ግምገማ ያካሄዱ ሲሆን በዚህም ከተሰጡ ዋና ቁልፍ እስትራቴጂክ ተግባራት በተጨማሪ የISO ትግበራን ከማስቀጠል አኳያ ስራ ሂደቶችና ክፍሎች ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ መመልከት ተችሏል:: በተካሄደው የድጋፍ፣ክትትልና ግምገማው መሰረት በስራ ሂደቶችና ክፍሎቹ የታዩ የአፈፃፀም ውስንነቶችን እንዲሁም የተለዩ ምርጥ ተሞክሮችን በመሰብሰብ ግብረ-መልስ የተሰጠ ሲሆን በቀጣይ የድጋፍ ክትትልና ግምግማውን መነሻ በማድረግ እንደ ተቋም የተመዘገበው የአፈፃፀም ሪፖርት የሚቀርብም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ  ስልጠና ኤጀንሲ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት  በዚህ አመት በሁለቱ የመንግስት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና በግል ተቋማት ስልጠናቸውን ለሚያጠናቅቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች የስራ ፈጠራ ባህል ግንባታ ስልጠና ተሰጠ። በዚህም ስልጠና ላይ በድሬዳዋ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ውስጥ ስልጠናቸውን አጠናቀው ስኬታማ የሆኑትን  የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ  በረጅም አመት የኮሌጅ አሰልጣኝ መምህርነትና አመራርነት  ያላቸውን ልምድና ተሞክሮአቸውን አነቃቂ በሆነ ንግግር  ለስልጠና አጠናቃቂዎች  አካፍለዋል ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የአሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ለማስጀመር ከኮሌጆች ጋር የጋራ መድረክ አዘጋጀ፤ መድረኩ በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ከተሻሻሉ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አሰራር ስርአቶች መካከል የሙያ ደረጃ እና የሙያ ብቃት ምዘና አተገባበር ስርአት መነሻ በማድረግ በአስተዳደሩ በግልና በመንግስት ኮሌጆች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ የሚያሰለጥኑ አሰልጣኞችን በተያዘው የ2017 በጀት አመት ወደምዘና ለማስገባት የሚያስችል መግባባት ለመፍጠር ያለመ ሆኗል፡፡ በዚህም ከቢሮው የቴክኒክና ሙያ ትምህሮትና ስልጠና ኤጀንሲ እና የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ባለሙያዎች እንዲሁም ከኮሌጆቹ አባል የሆኑበት የስትሪንግ ኮሚቴ ጋር የአሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና ወጥነት ባለው፣ በተቀናጀ እና የስልጠና ስራውን በማይጎዳ አግባብ ለመፈጸም ውይይት የተደረገ ሲሆን በአስተዳደሩ ከሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች እና የ5ቱ የግል ኮሌጆች ለምዘና የተለዩ አሰልጣኞች ምዘና ለማከናወን ለውሳኔ የሚረዱ ሃሳቦች መለየታቸውን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት አማካኝነት ላለፉት 5ቀናት በድሬዳዋ የስራ አመራር ኢንስቲትዩት ለአስተዳደር ስራተኞች ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ:: በስልጠናው ማጠቃለያ መርሃ-ግብር ላይ የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት በተልምዶ ፕሮጀክቶች ሲመጡ በእብዛኛው ትኩርት የሚያደርጉት አ/ መምህራን ላይ ብቻ እንደነበር አስታውሰው የEASE ፕሮጀክት ቀረፃው ላይ የአስተዳደር ዘርፉንም እንዲያሳትፍና የፕሮጀክት ኢኒሼቲቩንም ስንቀርፅ ትኩርት እንዲደረግበት አስበን ነው ያሉ ሲሆን በዚህም ስልጠና በተሰጠው ግብረ-መልስ መሰረት በታቀደው አግባብ እንደተሰጠ በመረዳታችን ለስራ አመራር ኢንስቲትዩት አመራሮችና ስልጠናውን ለሰጡልን አሰልጣኞች ላቅ ያለ ምስጋና እናቀርባለንም ብለዋል:: ኮሌጁ የISO 9001:2015 የጥራት ማረጋገጫን ለማግኘት እንደ ትቋም ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እንዳከናወነ የገለፁት የኮሌጁ ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ አክለውም ተቋሙ እስካሁን ያከናወናቸው ትግበራዎች ወደኃላ እንዳይመለሱ እዚህ በሰለጠናችሁት አግባብ መሰረት ይበልጥ እንዲሻሻል ስልጠናውን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባም አመላክተዋል:: የድሬዳዋ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አወቀ ለገሰ በበኩላቸው ይህ የደምበኛ እገልግሎትና የስራ ሥነ-ምግባር ስልጠና ቀጥታ ሰራተኞች እለት ተእለት ከሚከውኑት የስራ ተግባር ጋር የሚገናኝ በመሆኑ የወሰዳችሁት ስልጠና ጠቀሜታው የጎላ ነው ያሉ ሲሆን ኮሌጁ ሰራተኞች በስራ ገበታቸው ላይ የሚሰጡት አገልግሎት እንዲሻሻል በማቀድ ይህንና መሰል ስልጠናዎችን እንዲወስዱ ማመቻቸቱ የሚበረታታ በመሆኑ የኮሌጁን አመራሮችም አመስግነዋል:: የማጠቃለያ መርሃ-ግብሩ ላይ ስልጠናው በአግባቡ ተከታትለው ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የምስክር ወረቀት የተበረከተ ሲሆን በቀጣይ ሁለተኛ ዙር ሰልጣኞችም ስልጠናውን የሚወስዱ ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም

photo content
+9

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa) - Статистика та аналітика Telegram каналу @eipc2001