Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
Відкрити в Telegram
Показати більше
1 740
Підписники
Немає даних24 години
+17 днів
-630 день
Архів дописів
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
በአገር አቀፍ ደረጃ ለቴክኒክና ሙያ ስልጠና አሰልጣኞችና አስተባባሪዎች እየተሰጠ ያለው ስልጠና ቀጥሎ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ሥር የሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ማለትም ድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና ኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ላይ የሚያሰለጥኑ አሰልጣኝ መምህራን በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማዕከል ስልጠናቸውን እየተከታተሉ የሚገኝ ሲሆን ከስልጠናው ጎን ለጎን በበጎ አድራጎት ስራዎች የደም ልገሳ መርኃግብር አካሂደዋል፤
ዘርፉን ከስልጠና በላይ በማሰብ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ላይ በምንሰራው ስራ አጠቃላይ ኢኮኖሚውን ትራንስፎርም የሚያደርግ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠርም አልፎ የዘርፉን አቅም በመጠቀም ፈጥነን ከድህነት እንድወጣም የሚያስችል ነው፤ ከዚህ በመነሳት እነዚህን እሳቤዎች የዘርፉ ሁሉም አሰልጣኝ መምህራን በግንዛቤ የጨበጧቸውን ወደ ተግባር በመቀየር በቀጣይም በስልጠና ማዕከሉ አካባቢ የሚገኙ ማህበረሰቦችን በበጎ አድራጎት ስራዎች ተደራሽ ለማድረግ መዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
የአስተዳደሩን አሰልጣኝ መምህራን በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና እና የዘርፉ እሳቤ ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ እንዲሁም የአሰልጣኞችን ባህሪያዊና ቴክኒካዊ ብቃት ለማሳደግ ያለመ ስልጠና በሀገር አቀፍ ደረጃ በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማዕከል እየተሰጠ ይገኛል።
በሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ም/ኃላፊ ክብርት ፈጡም ሙስጠፋ ሀሮማያ ዩኒሸርሲቲ በመገኘት የስልጠና ሂደቱን ተመልክተዋል። በምልከታው ላይ ከድሬዳዋ አስተዳደር በስልጠናው የሚሳተፉ አሰልጣኝ መምህራን ጋር በመነጋገር አበረታቸዋል፡፡
የቢሮው ኃላፊዎች በቆይታው ከሰልጣኞችና ከስልጠና አስተባባሪዎች ጋር ቆይታ ያደረጉ ሲሆን ስልጠናው በጥሩ ሁኔታ እየሄደ እንደሆነ እና እንደ አስተዳደር የተሰሩ ስራዎች በተሞክሮ መቅረባቸው ተጠቁሟል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት" በሚል መሪ ሃሳብ በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራንና የስልጠና አስተባባሪዎች ስልጠና ተጀመረ፡፡
በዘርፉ ፖሊሲ፣ ስትራቴጂዎችና አዳዲስ እሳቤዎች ላይ የአሰልጣኞችን ግንዛቤ ከማሳደግ ባለፈ ቴክኒካዊና ባህሪያዊ ብቃቶችን በማሳደግ ለላቀ ውጤት ማዘጋጀት ዓላማ ያደረገ ሲሆን እንደ አገር 17 የስልጠና ማዕከላት 24 ሺህ የሚጠጉ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ተሳታፊ የሚሆኑ ሲሆን ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 12 ቀናት ይካሄዳል፡፡
በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ላይ የሚያሰለጥኑ 285 የሚሆኑ አሰልጣኝ መምህራንና የስልጠና አስተባባሪዎች በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማዕከል ስልጠናውን የሚከታተሉ ይሆናል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኮሌጃችን የቀድሞ አሰልጣኝ መምህርት የተለያዩ መፅሃፍቶችን በስጦታ መልክ ለኮሌጁ አበረከቱ::
ላለፉት 30 አመትና ከዚያ በላይ በቢዝነስ መምህርነት በኮሌጃችን እንዲሁም በተለያዩ የትምህርት ተቋማት ሲያገለግሉ የቆዩትና በቅርቡ የአገልግሎት ዘመናቸውን አጠናቀው በክብር የተሸኙት መ/ርት ገነት መኮንን በመምህርነት ዘመናቸው ሲገለገሉባቸው የነበሩ የተያዩ ከ200 በላይ መፅሃፍቶችና የተለያዩ ዶክመንቶችን በማሰባሰብ የኮሌጁ ማህበረሰብ እንደግብዓትነት ይጠቀምባቸው ዘንድ በዛሬው እለት በአካል በመገኘት መፅሃፍቶቹን ለኮሌጁ አስረክበዋል::
መፅሃፍቶቹን የተረከቡት የኮሌጁ ም/ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት ሀላፊ አቶ ኤልያስ አህመድ ሲሆኑ ይህ አይነት ተግባር የሚያስመሰግንና ለሌሎችም አርዓያ የሚሆን ተግባር መሆኑን በመግለፅ ለመ/ርት ገነት መኮንን ላበረከቱት በዋጋ የማይተመን ስጦታ በኮሌጁ ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል::
ኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ነሃሴ 11/2016 ዓ.ም
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ "ክረምትን በክህሎት"በሚል በተዘጋጀው የክረምት ስልጠና ለመሰልጠን የተመዘገቡ የአስተዳደሩ ወጣቶች በኮሌጁ ተገተው ስልጣናቸውን ጀመሩ::
ወጣቶቹ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የክህሎት ስልጠና ለመሰልጠን የተመዘገቡ ሲሆን ወደ ስልጠና ከመግባታቸው አስቀድሞ በኮሌጁ ስለሚሰጡ ስልጠናዎችና በክረምቱ በሚወስዱት የሙያ ክህሎት ስልጠናዎች ዙሪያ በኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና ሀላፊና በኮሌጁ ም/ዲን አማካኝነት ሰፋ ያለ ገለፃ ተደርጎላቸዋል::
የክረምት ሰልጣኞቹ ይበልጥ ግንዛቤው እንዲኖራቸው ትምህርትና ስልጠና የሚሰጥባቸውን ወርክሾፖች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በዚህም በትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ሙያዊ ገለፃና ማብራሪያ በመስጠት ግንዛቤ እንዲያገኙ ተደርጏል::
"የክረምትን በክህሎት" ሰልጣኝ ወጣቶች ቀጣዮቹን ወራት በኮሌጁ በመረጡት ሙያዊ ስልጠና እየወሰዱ የሚቆዩ ሲሆን በስልጠናው ማጠናቀቅያ ላይም ለቀጣይ ምዕራፋቸው መሰረት የሚሆናቸውን ሙያዊ ክህሎት ጨብጠው እንደሚወጡም ተገልፇል::
ኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ነሃሴ 7/2016 ዓ.ም
አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በSolar PV Installation Maintenance በመጀመርያ ዙር ያሰለጠናቸውን ሰልጣኝ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
የዛሬ ተመራቂዎች በአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በአጫጭር ስልጠና በSolar PV Installation Maintenance ላለፉት 8 ወራት ሲሰለጥኑ የቆዩ ሲሆን በዚህም 30 ወንድ እና 18 ሴት እንዲሁም 3 አካል ጉዳተኞች በድምሩ 48 ሰልጣኝ ተማሪዎች በዛሬው እለት ለምረቃ በቅተዋል::
ተመራቂ ተማሪዎቹ በሰለጠኑት ስልጠና የሶላር ሲስተም ጥገናን በሚፈለገው ልክ ተደራሽ ለማድረግ የብቃት ምዘና(COC) በብቃት በማጠናቀቅ ወደ ስራ አለም ለመግባት መዘጋጀታቸውም ተገልፇል::
በምረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ ለመገኝት የአድራ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የተለያዩ ሀላፊዎች ከአዲስ አበባ የተግኙ ሲሆን ከምረቃ ፕሮግራም መጠናቀቅ በኃላ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በኮሌጁ አካሂደዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ነሃሴ 2/2016 ዓ.ም
የአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ፕሮጀክት የ2016ዓ.ም የፕሮጀክቱን አመታዊ አፈፃፀም ሪፖርት ለኮሌጁ ማኔጅመት አቀረበ::
በዕለቱ በቀረበው ሪፖርት አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ)ፕሮጀክት በአመቱ የተሰሩ ስራዎችንና የተመዘገቡ ውጤቶች በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም በፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና የተወሰዱ መፍትሄዎችም ጭምር በፕሮጀክቱ ሀላፊ አማካኝነት ለኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል::
የማኔጅመንት አባላቱ በመቀጠል በአመቱ የአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ፕርጀክት በሰልጣኝ ተማሪዎቹ የተሰሩ ፕሮጀክቶችንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል::
በመጨረሻም አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በዘንድሮ ዓመት በSolar PV Instalation ያሰለጠናቸውን 48 ሰልጣኝ ተማሪዎቹን ነሃሴ 2/2016 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ የሚያስመርቅ መሆኑም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ሐምሌ 28/2016 ዓ.ም
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
