Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
Відкрити в Telegram
Показати більше
1 745
Підписники
+224 години
+57 днів
-230 день
Архів дописів
የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎፈቃድ ስራዎች ማስጀመሪያ እና የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በኮሌጁ ተካሄደ።
በዘንድሮ ክረምት "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ የችግኝ ተከላ ንቅናቄ መጀመሩ የሚታወስ ሲሆን ይህን ምክንያት በማድረግም በተቋም ደረጃ በኮሌጁ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩን በዛሬው ዕለት ማከናወን ተችሏል::
በዛሬው ዕለት በኮሌጁ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የኮሌጁ አመራሮችና ሰራተኞች የተሳተፉ ሲሆን በተቋሙ ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው ስፍራ ላይም አሻራቸውን እኑረዋል::
በቀጣይም በኮሌጁ የክረምት የበጎፍቃድ ስራዎች ላይ ዘርፈ ብዙ ተግባራት የሚያከናውኑ ሲሆን በዚህም የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ፣ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግን ጨምሮ መሰል ማህበረሰብ ተኮር ንቅናቄዎች ላይ እንደሚሰራ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 9/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+9
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን ለኮሌጁ የቦርድ አባላት አቀረበ፡፡
በበጀት አመቱ የተቋሙን አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም ሪፖርት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ለቦርዱ የቀረበ ሲሆን በዚህም ኮሌጁ ከዝግጅት ምእራፍ አንስቶ በበጀት አመቱ የነበረውን የእቅድ አፈፃፀምና አጠቃላይ በኮሌጁ የተሰሩ የለውጥ ስራዎችን እንዲሁም የተገኙ ውጤቶችን ለቦርዱ ሪፖርት አቅርበው ገለፃ ያደረጉ ሲሆን አያይዘውም በቀጣይ በተቋሙ ሊሰሩ በእቅድ የተያዙ ዘርፈ ብዙ ስራዎችንም ለቦርድ አባላቱ በዝርዝር አመላክተዋል፡:
በመድረኩ የቀረበውን ሪፖርት መነሻ በማድረግም የቦርድ አባላቱ ግብረ- መልሳቸውን የሰጡበት ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በቀጣይ በሚኖረው የስራ እንቅስቃሴ ላይ ምክረ-ሃሳባቸውን አስቀምጠዋል::
በመጨረሻም የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ በቀረበው የኮሌጁ አጠቃላይ የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ማጠቃለያ እንዲሁም የቀጣይ ስራ አቅጣጫና መመሪያን በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል፡፡
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ ለሚገኙ ወጣቶች የክረምት ወቅት የሙያ ስልጠና በኮሌጁ መስጠት ተጀመረ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በክረምት ወቅት አንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ በሚል መርሃ-ግብር በአስተዳደሩ እረፍት ላይ ለሚገኙ የአጠቃላይ የ1ኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ ስልጠናዎችን መስጠት ጀምሯል::
ለወጣቶቹ በተዘጋጀ ኦረንቴሽን ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለወጣቶች ባስተላለፉት መልዕክትም የዚህ የክረምት ወቅት ስልጠና የተዘጋጀበት ዋና አላማ ወጣቶች እረፍታችሁን ቁምነገር ላይ በማዋል ቢያንስ በክረምቱ የአንድ ሙያ ባለቤት እንድትሆኑ ለማስቻል ነው ያሉ ሲሆን አክለውም የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ክረምቱን በኮሌጃችን በሚኖራችሁ ቆይታ ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት የምትገነዘቡ በመሆኑ በቀጣይ ምዕራፋችሁ ለሙያ ተኮር ስልጠናዎች ቅድሚያ እንድሰጡ ያግዛችኃልም ብለዋል::
የአንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ የክረምት ስልጠና ላይ ለመሳተፍ ወደ ኮሌጁ የመጡ ወጣቶች በቅድሚያ የህይወት ክህሎት ስልጠና ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚወስዱ ሲሆን የህይወት ክህሎት ስልጠናው ወጣቶች የቀጣይ ህይወታቸውን የመምራት ክህሎት፣ችግሮችን የመፍታት ክህሎት እንዲሁም የውሳኔ አሰጣጥ ክህሎቶችን እንደሚያገኙበት የተገለፀ ሲሆን የህይወት ክህሎት ስልጠናውን እንዳጠናቀቁ በቀጣይ በመረጡት የሙያ ዘርፍ ላይ ስልጠናቸውን የሚጀምሩም ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 7/12/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+9
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት የ2017 ዓ.ም ማጠቃለያ ሪፖርት መድረክ አካሄደ::
በትምህርትና ስልጠና አካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት የሁለተኛው ተርም መጠናቀቁን ተከትሎ በአመቱ የተከናወኑ ተግባራትን አፈፃፀም የሚገመግም ማጠቃለያ ሪፖርት መድረክ ተካሂዷል::
በሂደቱ ሀላፊና የኮሌጁ ም/ል ዲን አቶ ኢልያስ አህመድ የተመራው የማጠቃለያ መድረኩ በሂደቱ ስር ያሉ የክፍል ተጠሪዎች በተገኙበት በአካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት በአመቱ የነበረውን የትምህርትና ስልጠና አሰጣጥ፣ የትብብር ስልጠናዎች፣ የሰልጣኞች የተቋም ምዘናን ጨምሮ ለትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የተሰጡ ተጨማሪ ተልዕኮዎች አፈፃፀምን በዝርዝር መመልከት ተችሏል::
በተጨማሪም መድረኩ በከሰዓት ውሎው በዲፓርትመንቶች የቀረበውን የ2018 ዓ.ም የትምህርትና ስልጠና ማቴሪያል የግዢ ፍላጎት ጥያቄዎች ላይ የአካዳሚክ አባላቱ በጥልቀጥ የተወያዩበት ሲሆን በቀረቡት የግዢ ፍላጎቶች ላይ አስፈላጊውን ማስተካከያ በማድረግ ለግዢና ፋይናንስ እንዲላክም ተደርጎል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ነሃሴ 1/12/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ከትላንት ጀምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በክህሎት መር ሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ የተሰሩ ስራዎችን የሚቃኝ የልምድ ልውውጥ እና የተሞክሮ ሽግግር እያረጉ የሚገኙት ከሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የመጡ አመራሮችና ባለሙያዎች በዛሬው ዕለትም ቀጥለው በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ምልከታ አድርገዋል።
በዚህም በኮሌጁ በመገኘት አጠቃላይ የክህሎት ልማቱ ከስራ ዕድል ፈጠራው ጋር ያለው መስተጋብር ምን እንደሚመስል በቢሮው አመራሮች እንዲሁም በኮሌጁ ዲን ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሀምሌ 25/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
3 ቀን ቀረው!
ሐምሌ 24 ፣2017 700 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀንበር። እንዘጋጅ!
#አረንጓዴዐሻራ
#GreenLegacy
የአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት በአስተዳደሩ የገጠር ክላስተሮች ላይ ለሚገኙ ወጣቶች የSolar PV Installation & Maintenance ስልጠና በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ::
ፕሮጀክቱ ባለፉት አመታት ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመቀናጀት በሁለት ዙሮች በከተማ አአስተዳደሩ የሚገኙ ወጣቶችን አሰልጥኖ ከስራ ጋር የማስተሳሰር ስራ እየሰራ ሲሆን በዚህ በ3ኛ ዙር ስልጠና የMobile training እሳቤን ወይም ወጣቶች ስልጠናውን ለመውሰድ ወደ ኮሌጅ መምጣት ሳይጠበቅባቸው ባሉበት የገጠር ክላስተር(የአርዳሌ ክላስተርና የቢያዋሌ ክላስተር)የስልጠና ቦታዎችን በማመቻቸት እንዲሁም የስልጠና ግብዓቶችን በማሟላት በቃልቻ የገጠር ጤና ጣቢያ ግቢ ውስጥ በተመቻቸው ቦታ ስልጠናውን በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በSolar PV Installation & Maintenance ላይ በአጫጭርና መደበኛ ፕሮግራም ሰልጣኞችን ተቀብሎ እያሰለጠነ እንደሚገኝ የገለፁት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት ምክትል ዲን አቶ ኢልያስ አህመድ ሲሆኑ አክለው በፕሮጀክቱ በመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዙር በድምሩ 91 ለሚሆኑ የአስተዳደሩ ወጣቶች በSolar PV Installation & Maintenance ስልጠና መሰጠቱን ጠቅሰው የ3ኛውን ዙር ስልጠና በአስተዳደሩ የገጠር ክላስተሮች ላይ በመሄድ በአካባቢው ለሚገኙ ወጣቶች እየተሰጠ የሚገኝ ስልጠና በመሆኑ ካለፉት ዙሮች ለየት ያደርገዋልም ብለዋል::
የአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት አላማ ወጣቶችን አሰልጥኖ የሙያ ባለቤት ማድረግ ብቻ ሳይሆን ወጣቶቹ የስራ እድል ተመቻችቶላቸው ራሳቸውን፣ቤተሰባቸውን እንዲሁም ማህበረሰባቸውን እንዲጠቅሙና ህይወታቸውን እንዲቀይሩ ለማስቻልም ነው ያሉት የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ በየነ አክለውም በዚህ ሂደት ውስጥም የአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት አጠቃላይ የስልጠናውን በጀት ከመሸፈን ጀምሮ የስልጠና ግብአቶችን በማሟላት የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ በመግለፅ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም ወርክሾፖችን ከማዘጋጀት ጀምሮ አሰልጣኝ መምህራንን በመመደብና የተለያዩ ለስልጠናው ውጤታማነት አስፈላጊ የሆኑ ተግባራት በማከናወን ረገድ እንደ ተቋም የሚጠበቅበትን በማበርከት በቅንጅት የሚሰራበት ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀዋል::
በአርዳሌ ክላስተር እና በቢያዋሌ ክላስተር በSolar PV Installation & Maintenance ስልጠናቸውን የወሰዱ ወጣቶች በቀጣይ ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲገቡ አስፈላጊው ትብብር የሚደረግላቸው መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ወጣቶቹ የራስቸውን ህይወት ከመለወጥ በተጨማሪ የአካባቢያቸውን ማህበረሰብ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚያስችላቸውም ተገፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሐምሌ 18/11/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
LMIS Website Guide Amharic
በብቁ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት ድረ-ገጽ በቀላሉ ለመመዝገብ ይህን ቪዲዮ ይመልከቱ።
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
ELMIS Website Guide Oromiffa
Karaa salphaa ta'een biquu gabaa hojii karaa marsariitii galmaa'uuf viidiyoo kana daawwadhaa
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
ELMIS Website Guide Somali
"ADEEGA ELMIS EE BOGA XOGAHA SUUQA SHAQADA IYO SHAQALAHA SII AAD ISAGA DIWAAN GALISO DAAWO MUQALKANI"
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
