Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
Відкрити в Telegram
Показати більше
1 744
Підписники
+224 години
+37 днів
-130 день
Архів дописів
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመላው ዓለም ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን ለ2014 ዓ.ም ዘመን መለወጫ በዓል በሰላም፣በጤና፣በፍቅር አደረሳችሁ ይላል።🌻🌻🌻🌻🌻
አዲሱ አመትም የሰላም፣የአብሮነት እና የእድገት ይሆንላችሁ ዘንድ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።🌻🌻🌻
#መልካም_አዲስ_አመት🌻🌻
የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች እና ሰራተኞች የደሞዛቸውን ከ10 እስከ 50 ፐርሰንት ለኢ.ፌ.ድ.ሪ መከላከያ ሰራዊት ለመስጠት ወስነዋል።
…………………………………………………
ነሀሴ 10/2013 ዓ.ም የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች የደሞዛቸውን 50% እንዲሁም የተቋሙ ሰራተኞች የደሞዛቸውን 10% ለኢ.ፌ.ድ.ሪ መከላከያ ሰራዊት ድጋፍ ለማድረግ ወስነዋል።
በቀጣይም ለሰራዊቱ የሚያደርጉትን ድጋፍ በተለያዩ መንገዶች አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልፀዋል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች በዛሬው ቀን በተካሄደው በአስተዳደራችን በአንድ ጀምበር 500 ሺ ችግኝ የመትከል መርሀ ግብር ላይ በመሳተፍ እንደ ተቋም አሻራቸውን አኑረዋል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1442ኛው የኢድ አል አድሃ በዓል አደረሳችሁ ይላል።
የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ዋና የስራ ሂደት አዘጋጅነት በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን እና የፈጠራ አስተባባሪዎች በቴ/ሙ/ት/ስ ስትራቴጂ ገለጻ በማድረግ STEM እና INNOVATION እንዲሁም ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ግንዛቤ በመፍጠር የ2014 ረቂቅ ሰነድ ላይ በመወያየት የጋራ ስምምነት መድረስ ተችሏል፡፡
ሰኔ 11/2013 ዓ.ም
…………………………………………………
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አዲስ ተቀብሎ ለሚያሰለጥናቸው ሰልጣኝ ተማሪዎች ምዝገባ እያካሄደ ሲሆን እርሶም በቀሩት ጥቂት ቀናቶች መተው እንዲመዘገቡ እንጋብዛለን።
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
