uk
Feedback
Higher 12 Secondary School.

Higher 12 Secondary School.

Відкрити в Telegram

Online teaching

Показати більше
2 167
Підписники
Немає даних24 години
+37 днів
-2030 день
Архів дописів
#Grade12 #NationalExam ከመጪው ሰኔ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች የተዘጋጀ የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ (Admission Ca
#Grade12 #NationalExam ከመጪው ሰኔ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች የተዘጋጀ የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ (Admission Card) በፈተና አስተዳደር ሲስተም (https://exam.eaes.et/) ከ03/09/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለክልል ትምህርት ቢሮ፣ ለዞን ትምህርት መምሪያዎች እና ለትምህርት ቤት ተወካዮች መለቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። አገልግሎት መ/ቤቱ ፦ 1. እያንዳንዱ ተፈታኝ ተማሪ በአድሚሽን ካርዱ ጀርባ ላይ የትምህርት  ቤቱን ወይም የወረዳው አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ማህተም የተደረገበትን አድሚሽን ካርድ ከትምህርት ቤቱ ወስዶ በእጁ መያዝ መያዝ እንዳለበት አሳስቧል። 2. በምዝገባ ወቅት በተፈታኙ ወይም በመዝጋቢው የተከሰተ የትምህርት መስክ ፣ የጾታ ፣ የፎቶ እና መሰል ማስተካከያዎች ካሉ ከግንቦት 30/2018 ዓ.ም በፊት ለትምህርት ቤቱ ማሳወቅና ሂደቱን ጠብቆ መስተካከሉንም ከትምህርት ቤቱ ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጿል። 3. እያንዳንዱ ተፈታኝ አድሚሽን ካርዱን ወደ መፈተኛ ማዕከል ሆነ መፈተኛ ክፍል ለመግባት የሚጠቀምበት በመሆኑ በአግባቡና በጥንቃቄ እንዲይዝ አሳስቧል። 4. ተፈታኞች ፈተና ላይ ከአድሚሽን ካርድ በተጨማሪ የፋይዳ መታወቂያ መያዝ እንደሚጠበቅባቸው ገልጿል። #EAES ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘና
+1
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል። በሌላ በኩል ፦ - የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ - የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም - የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም - የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም @tikvahethiopia

#NationalExam 🔠🔠🅰️🔠🔠1️⃣2️⃣ ➡️የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸውን የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደ
#NationalExam 🔠🔠🅰️🔠🔠1️⃣2️⃣ ➡️የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸውን የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎች ይፋ ማድረጉን የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። በዚሁ መሠረት ፡- ✅1) ፈተና የሚሰጥባቸው የትምህርት ዓይነቶች
➡️በተፈጥሮ ሳይንስ ፦ - እንግሊዘኛ - ሒሳብ - ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ - ባዮሎጂ - ኬሚስትሪ - ፊዚክስ
➡️በማህበራዊ ሳይንስ ፦ ° እንግሊዘኛ፣ ° ሒሳብ፣ ° ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ° ታሪክ፣ ° ጂኦግራፊ ° ኢኮኖሚክስ ናቸው
➡️2) ፈተናው በየትምህርት ዓይነቱ ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች የሚሸፍን ይሆናል። ➡️የዝግጅት አግባቡም 9ኛ ክፍል ላይ የቀድሞውና የአዲሱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘት (Common Contents) ላይ ያተኩራል። ➡️ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ያለው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ይሆናል። 📌የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት ሆኖ ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን የሚሸፍን ይሆናል። (የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት) 🔠🔠🔠🅰️  🔤🔤🔤 ቻናላችን ይህ ነው 👇👇👇👇👇👇👇 ❤️❤️❤️❤️❤️❤️ https://t.me/dam76

ማስታወቂያ ✍✍በ2018  ዓ.ም በሚሰጠው  የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በድጋሜ ተፈትናቹህ ውጤታቹህን ማሻሻል የምትፈልጉ ተማሪዎች ከዚህ በታች ባለው ሊንክ መሰረት በመግባት በራሳቹህ ከ16/06/2018 ዓ.ም ጀምሮ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን Private registration link https://Regester.eaes.et

እስቸኳይ ማስታወቂያ ለ2018 ዓ/ም ከፍተኛ 12 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ብቻ ቀን 13/4/18 ዓ/ም ከዚህ ቀደም የፋይዳ መታወቂያ ቁጥር ማስመዘገባችሁ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን የተመዘገበው ቁጥር 16 ዲጂት እና 12 ዲጂት በመሆኑ ሲስተም ላይ ማስገባት አልተቻልም፡፡ ስለሆነም ነገ ማስኞ ታህሳስ 14/4/2018 ዓ/ም ጠዋት አንድ ጉርድ ፎቶ እና የፋይዳ ቁጥር ከፊት እና ከኋላ ኮፒ አድርጋችሁ እስከ ጠዋት 2.31 ደቂቃ ድረስ ብቻ ቢሮ ቁጥር 2/ሁለት/ እንድታሳሞሉ እያሳሰብን ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚያጋጥም ማኛውም ችግር ትምህርት ቤቱ ሃላፊነት እንደማይወስድ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ የመማር ማስተማር ዝርፍ ሃላፊ!

ማስታወቂያ ለቀድሞ ተማሪዎች በሙሉ ከ2015 ዓ.ም እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት ዓመታት የ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ ትራንስክሪብት ያልወሰዳችሁ ተማሪዎች ት/ቤቱ በልዮ ሁኔታ ከየካ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ጋር በመተባበር ከደረጃ 1 - እሰከ ደረጃ 5 ድረስ እንድትሰለጥኑ ሁኔታዎችን አመቻችቷል። ስለሆነም ኦረንቴሽን በተቋሙ አመራሮች ህዳር 2/2018 ዓ.ም በከፍተኛ 12 ት/ቤት ከጠዋቱ 3:00 ላይ ስለሚሰጥ እንድትገኙ እናሳውቃለን።

" ተማሪዎች ምደባቸውን በድረ-ገፅ፦ https://student.ethernet.edu.et እና በቴሌግራም ቦት፦ @moestudentbot መመልከት ይችላሉ " - ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የሪሚዲ
" ተማሪዎች ምደባቸውን በድረ-ገፅ፦ https://student.ethernet.edu.et እና በቴሌግራም ቦት፦ @moestudentbot መመልከት ይችላሉ " - ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ምደባ ተለቋል፡፡ በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ብሔራዊ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባቸው ዛሬ ይፋ ተደርጓል። ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ተማሪዎች ምደባቸውን ማየት የሚችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡ በድረ-ገፅ፦ https://student.ethernet.edu.et በቴሌግራም ቦት፦ @moestudentbot Via @tikvahuniversity

የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይዘቶች ይፋ ሆኑ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይዘቶችን ይፋ አድርጓል፡፡ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ÷ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ አለባቸው፡፡ ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት አመራር ለፈተና ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ፈተና የሚሸፍናቸውን የይዘት አካባቢዎች ማወቅ አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በዚህ መሰረትም ለፈተና ዝግጅት የሚደረግባቸውን የትምህርት ዓይነቶችን በተመለከተ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች እንግሊዘኛ፣ ሒሳብ፣ እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስ እና ባዮሎጂ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ለማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ደግሞ እንግሊዘኛ፣ ሒሳብ፣ እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊ እና ኢኮኖሚክስ ናቸው ብለዋል፡፡ ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ደረጃዎችን እና በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል ነው ያሉት፡፡ ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ሁሉም የትምህርት ዓይነት ፈተና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት እየተዘጋጀ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡ የ9ኛ ክፍል ደግሞ የሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተናዎች ከቀድሞውና ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘቶችን ብቻ አካቶ እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ፈተናው ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ከተማረው ሥርዓተ ትምህርት እና ከተማሪው መጽሐፍ ላይ ብቻ ተመስርቶ እየተዘጋጀ ይገኛል ነው ያሉት፡፡ የፈተናው አስተዳደር በበይነ መረብና በወረቀት ጎን ለጎን እንደሚሰጥ ጠቁመው ÷ አብዛኛው ተፈታኝ በበይነ መረብ እንዲፈተን እየተሠራ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ ስለሆነም ተፈታኞች ፈተናውን በበይነ መረብ ለመፈተን እራሳቸውን ከወዲሁ ሊያዘጋጁ እንደሚገባ ዋና ዳይሬክተሩ በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡ @sheger_press @sheger_press

photo content

የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅበት ካሪክለም ይፋ ሆኗል የፈተና ዝግጅቱ: 1. ከ9ኛ ክፍል በነባሩ እና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ተመሳሳይ ይዘቶች፣ 2. ከ10 - 12ኛ ከፍ
የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅበት ካሪክለም ይፋ ሆኗል የፈተና ዝግጅቱ: 1. ከ9ኛ ክፍል በነባሩ እና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ተመሳሳይ ይዘቶች፣ 2. ከ10 - 12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ ይሆናል።

photo content

#MoE በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች የሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ
#MoE በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች የሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም  ድረስ ማስተካከል እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡ የሪሚዲያል ፕሮግራም #የማያስተናግዱ ዩኒቨርሲቲዎች ፦ 1.  አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 2.  አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 3.  አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 4.  ሲቪል ሰርቪርስ ዩኒቨርሲቲ 5.  ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 6.  ጅማ ዩኒቨርሲቲ 7.  ኮተቤ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ናቸው። ተማሪዎች የሞሉትን ምርጫ በ student.ethernet.edu.et በኩል ማረጋገጥ የሚችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ Via @tikvahuniversity

ለ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች ኦርጅናሉ ሰርተፊኬት ስለመጣ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ባስቸኳይ ቅሬታችሁን እንድትሞሉ
ባስቸኳይ ቅሬታችሁን እንድትሞሉ

የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆነ። በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላ
+1
የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆነ። በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለሚከታተሉ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ መደረጉን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። ተማሪዎች ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ፦ ➡️ በዌብሳይት፦ https://student.ethernet.edu.et ➡️ በቴሌግራም ቦት @moestudentbot ምደባቸውን ማየት እንደሚችሉ ገልጿል። የRemedial ፕሮግራም ምደባ በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። #MoE @tikvahethiopia

የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ። ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን
+1
የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ። ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የRemedial ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸውን አሳውቋል። 1. በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የRemedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት አለባቸው። 2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡን ያሟሉ ብቻ ይሆናሉ። የመቁረጫ ነጥብ ፦ ➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216 ➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204 ➡️ ታዳጊ ክልል እና አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198 ➡️ የማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198 ➡️ ማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዓይነስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165 #MoE @tikvahethiopia

ለትምህርት ቤታችን ከፍተኛ 12 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች በሙሉውጤታችሁ ከ297 በላይ የሆነ ወደ ዩኒቨርሲቲ እንድትገቡ ስለተወሰነ ከ297 በላይ ያመጣችሁ ተማሪዎች ባስቸኳይ ለት/ቤቱበአካልም ሆነ በቴሌ ግራም እስከ መስከረም 22/2018 ኣ/ም ድረስ ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳስባለን፡፡ የ መማር ማስተማር ዘርፍ ሃላፊ!

photo content
+6

photo content

photo content