uk
Feedback
Higher 12 Secondary School.

Higher 12 Secondary School.

Відкрити в Telegram

Online teaching

Показати більше
2 152
Підписники
+124 години
-47 днів
-1530 день
Архів дописів
⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️ ❤️ ለ ውድ የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ መልካም ፈተና እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ !! 🙏🙏🙏            አዩ  አለም ⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️

የማህበራዊ ሳይንስ 5ኛ ዙር ላይ ነው በቀጣይ እናሳውቃለን:: ሀምሌ 9,10 እና 13 (ሐሙስ ፣አረብ እና ሰኞ)

photo content
+1

photo content
+9

ሰላም ውድ የሀገር አቀፍ ተፈታኝ ተማሪዎች ይህንን መልዕክት ለሁሉም ተፈታኞች አድርሱ ግልጽ ካልሆነ ጠይቁን ለእናንተ መልስ ለመስጠት አንሰለችም የመፈተኛ ቦታ: 5 ኪሎ አዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ (CBTE) ተፈታኞች : የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ዙር : ሁለት (ሰኔ 26 - 30) አርብ፣ ሰኞ እና ማክሰኞ በት/ቤት መገኘት ያለባችሁ : 12:30 መኪና ተፈታኞችን ይዞ የሚነሳው : 12:50 መፈተኛ ቦታ የሚደረሰው : 1:15 ተፈታኞች በፈተናው ዕለት መያዝ  ያለባቸው 1. ዩኒፎርም ፣ የት/ቤት መታወቂያ ፣ የመፈተኛ ካርድ 2. የማሰቢያ ወረቀት ፣ እስኪርቢቶ/እርሳስ 3. የምሳ ገንዘብ ከዚህ ውጪ ያሉት የተከለከሉ ናቸው ሁሉም የተፈጥሮ ሳይንስ 2ኛ ዙር ተፈታኞች በ5 ኪሎ  ቤተ-መጽሐፍት በዚህ መልክ ተደልድለዋል:: ::::::::::::::መልካም ፈተና:::::::::::

photo content

photo content

photo content

photo content
+1

ከፍተኛ 12 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአዲሱ ስረዓት ትምህርት በ6 የሙያ ዘርፎች ማለትም ➯ Accounting and Financing ➯ Marketing and Sales Management ➯ physcosocial ➯ Constraction and Finishing ➯ Computer Maintenance ➯ Wbe design የስልጠና መስኮች ያሰለጠናቸውን በቀንእና በማታ በድምሩ 546 ተማሪዎችን በየካ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ባማረ ሁኔታ አስመረቀ። በመርሐግብሩ ላይ የየካ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ምክትል ዲን የሆኑት አቶ ዚያድ ለተመራቂዎቹ መጻኢ ዕድል ንግግር አድርገዋል።የትምህርት ቤቱ ር/መ/ር አቶ ባንታዬሁ ግርማ ለተመራቂዎች አዲሱ የትምህርት ስረዓት የፈጠረውን ዕድል እንዲጠቀሙበት አስረድተዋል።የትምህርት ቤቱ የመማር ማስተማር ዘርፍ ሃላፊ አቶ ቸረኝ ገላምጤ የሚሰራ እጅ የሚያስብ አዕምሮ እንዲኖራችሁ ጭላንጭልም ብትሆን ይህንን የደረጃ አንድ ማረጋገጫ ሰጥተናችኃል።ይህን ዕድል የፈጠረው ደግሞ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት ነው ብለዋል።ዕድሉ እንዳይመክን ተጠቀሙበት ትልቅ ነገር እና ትልቅ ሀገር አልሙ።ህይወት ትፈትናችኃለች።በስራ ግን ፈተናውን ትደመስሱታላችሁ የሚሰራ ዕጅ በመፍጠራችን ላቅ ያለ ደስታ ይሰማናል ብለው በመጨረሻም ተቋማችን ከፍተኛ 12 ከነበረበት ስብራት አሻግረን የልህቀት ማዕከል አድርገነዋል ብለዋል።

photo content

photo content
+1

#Grade12 #NationalExam የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበት የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ሆነ። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞች በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል። ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል።

የ12ኛ ክፍል የ2018 ዓ.ም ብሔራዊ ፈተና ፕሮግራም
+1
የ12ኛ ክፍል የ2018 ዓ.ም ብሔራዊ ፈተና ፕሮግራም

#Grade12 #NationalExam ከመጪው ሰኔ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች የተዘጋጀ የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ (Admission Ca
#Grade12 #NationalExam ከመጪው ሰኔ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች የተዘጋጀ የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ (Admission Card) በፈተና አስተዳደር ሲስተም (https://exam.eaes.et/) ከ03/09/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለክልል ትምህርት ቢሮ፣ ለዞን ትምህርት መምሪያዎች እና ለትምህርት ቤት ተወካዮች መለቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። አገልግሎት መ/ቤቱ ፦ 1. እያንዳንዱ ተፈታኝ ተማሪ በአድሚሽን ካርዱ ጀርባ ላይ የትምህርት  ቤቱን ወይም የወረዳው አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ማህተም የተደረገበትን አድሚሽን ካርድ ከትምህርት ቤቱ ወስዶ በእጁ መያዝ መያዝ እንዳለበት አሳስቧል። 2. በምዝገባ ወቅት በተፈታኙ ወይም በመዝጋቢው የተከሰተ የትምህርት መስክ ፣ የጾታ ፣ የፎቶ እና መሰል ማስተካከያዎች ካሉ ከግንቦት 30/2018 ዓ.ም በፊት ለትምህርት ቤቱ ማሳወቅና ሂደቱን ጠብቆ መስተካከሉንም ከትምህርት ቤቱ ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጿል። 3. እያንዳንዱ ተፈታኝ አድሚሽን ካርዱን ወደ መፈተኛ ማዕከል ሆነ መፈተኛ ክፍል ለመግባት የሚጠቀምበት በመሆኑ በአግባቡና በጥንቃቄ እንዲይዝ አሳስቧል። 4. ተፈታኞች ፈተና ላይ ከአድሚሽን ካርድ በተጨማሪ የፋይዳ መታወቂያ መያዝ እንደሚጠበቅባቸው ገልጿል። #EAES ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘና
+1
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል። በሌላ በኩል ፦ - የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ - የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም - የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም - የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም @tikvahethiopia

#NationalExam 🔠🔠🅰️🔠🔠1️⃣2️⃣ ➡️የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸውን የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደ
#NationalExam 🔠🔠🅰️🔠🔠1️⃣2️⃣ ➡️የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸውን የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎች ይፋ ማድረጉን የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። በዚሁ መሠረት ፡- ✅1) ፈተና የሚሰጥባቸው የትምህርት ዓይነቶች
➡️በተፈጥሮ ሳይንስ ፦ - እንግሊዘኛ - ሒሳብ - ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ - ባዮሎጂ - ኬሚስትሪ - ፊዚክስ
➡️በማህበራዊ ሳይንስ ፦ ° እንግሊዘኛ፣ ° ሒሳብ፣ ° ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ° ታሪክ፣ ° ጂኦግራፊ ° ኢኮኖሚክስ ናቸው
➡️2) ፈተናው በየትምህርት ዓይነቱ ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች የሚሸፍን ይሆናል። ➡️የዝግጅት አግባቡም 9ኛ ክፍል ላይ የቀድሞውና የአዲሱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘት (Common Contents) ላይ ያተኩራል። ➡️ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ያለው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ይሆናል። 📌የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት ሆኖ ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን የሚሸፍን ይሆናል። (የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት) 🔠🔠🔠🅰️  🔤🔤🔤 ቻናላችን ይህ ነው 👇👇👇👇👇👇👇 ❤️❤️❤️❤️❤️❤️ https://t.me/dam76

ማስታወቂያ ✍✍በ2018  ዓ.ም በሚሰጠው  የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በድጋሜ ተፈትናቹህ ውጤታቹህን ማሻሻል የምትፈልጉ ተማሪዎች ከዚህ በታች ባለው ሊንክ መሰረት በመግባት በራሳቹህ ከ16/06/2018 ዓ.ም ጀምሮ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን Private registration link https://Regester.eaes.et