uk
Feedback
Dilla University Official

Dilla University Official

Відкрити в Telegram

University of the Green Land

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Dilla University Official

Канал Dilla University Official (@dprd9) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 17 569 підписників, посідаючи 11 406 місце в категорії Освіта та 1 912 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 17 569 підписників.

За останніми даними від 04 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 167, а за останні 24 години на 3, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 16.29%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 10.87% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 2 863 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 911 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 10.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
University of the Green Land

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 05 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Освіта.

17 569
Підписники
+324 години
+347 днів
+16730 день
Архів дописів
የኤሌክትሪካል ስራዎች ማጠናቀቂያ ግብአቶች ሳይት መድረሳቸው ተገለፀ ==========****========== ዲ.ዩ: ሰኔ 26 /2018 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) ለአዲሱ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል እና ማስተማሪያ ሆስፒታል ቀሪ የኤሌክትሪካል ስራዎች ማጠናቀቂያ ግብአቶች (ኤሌክትሪካል ፊቲንግ) ወደ ሳይት ገብተዋል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ  (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፣ ለአዲሱ ሆስፒታል ማጠናቀቂያ የሚሆኑ የኤሌክትሪካል ግብአቶች በዛሬው እለት ተጠናቀው ወደ ሳይት መግባታቸው እንዳስደሰታቸው ገልጸው፣ ግብአቶቹ ሳይት ላይ ሳይቆዩ በፍጥነት ወደ ገጠማ ስራ መግባት አለባቸው። ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ አሁን ላይ በአዲሱ ሆስፒታል እየተሰሩ ያሉ የፍኒሽንግ ስራዎች በአብዛኛው እየተጠናቀቁ መሆናቸውን በመግለጽ ቀሪ ውስን ስራዎችንም በአጭር ጊዜ ለማገባደድ ስራዎች ተጠናክረው እየተሰሩ መሆኑን አብራርተዋል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር በፍቃዱ መኩሪያ በበኩላቸው፣ በዛሬው እለት ወደ አዲሱ ሆስፒታሉ የገቡ እቃዎች ቀደም ሲል ቻይና ላይ ከአምራች ድርጅቱ ጋር ውል በተገባው መሰረት የሆስፒታሉን ሙሉ የኤሌክትሪክ ፊቲንግ ማጠናቀቅ የሚያስችሉ ከ5 ሺህ በላይ ግብአቶችን የያዙ ሁለት ተሳቢ ኮንቲነሮች እንደሆኑ ገልጸዋል። የገቡ ግብአቶች ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ ትልቅ አስተዋጽኦ ያላቸው መሆናቸውንም ተናግረዋል። ኢንጅነር በፍቃዱ አክለውም፣ የሆስፒታሉን የኤሌክትሪክ መስመር የሚያዘረጉ ሲስተሞች እንዲሁም ቀሪ የፍኒሽንግ ግብአቶችን የያዙ ወደ 5 የሚደርሱ ኮንቲነሮች ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ጉምሩክ ላይ የሚገኙ መሆናቸውን ገልፀዋል። ግብዓቶቹ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠቃለው ወደ ሳይት እንዲገቡ ጥረት እንደሚደረግ ተናግረዋል። የፊሊንትስቶን ኢንጂነሪንግ የዲላ ማስተማሪያ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ዘገየ ቶሎሳ በአንጻሩ፣ በሳይት ላይ የደረሱ ግብዓቶችን በፍጥነት ወደ ስራ ለማስገባት እንደወትሮው ሁሉ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ቶሎሳ ዳዲ ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን የአዲሱ ሆስፒታል የፍኒሽንግ ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ===###=== #የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ #UniversityOfTheGreenland

photo content
+8

ፕሬዝዳንቱ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሂደትን ጎበኙ =========************======== ‎ ‎ዲ.ዩ: ሰኔ 26/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) ‎ ‎የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) እና የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ሁለተኛውን ዙር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሂደትን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ‎ ‎የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) እንደገለፁት፣ ዩኒቨርሲቲው ሀገራዊ ተልዕኮውን ለመወጣት የሚያስችለውን በቂ ቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ በፈተናዎች አገልግሎት በወጣው መርሐግብር መሰረት የመጀመሪያውን ዙር ፈተና በሰላምና በተሳካ ሁኔታ አጠናቋል። ‎ ‎በዛሬው ዕለት የተጀመረው ሁለተኛው ዙር በሰላም እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ዝግጅት መደረጉን ያወሱት ፕሬዝዳንቱ፣ በምልከታው የፈተና አሰጣጥ ሃደቱን ለመገምገምና በፈተናው የሚሳተፉ ባለድርሻ አካላትን ለማበረታታት መሆኑን ጠቁመዋል። ‎ ‎ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ፈተናው በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረጉ ያሉት የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የትምህርት ሚኒስቴር ተወካዮችና፣ ፈታኝ መምህራኖች፣ የፀጥታ አካላት፣ የአይሲቲ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላትን አመስግነዋል። ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ከዛሬ ጀምሮ በመካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ያለ ምንም የፀጥታ ችግር በመሠጠት ላይ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው ለተፈታኝ ተማሪዎች መልካሙን ሁሉ ይመኛል። ===###=== #የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ #UniversityOfTheGreenland

photo content
+3

ለዲላ ዩንቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ ======*********======= ዲዩ፡ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ ጋዜጠኞችና ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ  ስልጠና ተሰጥቷል። ስልጠናውን የዩኒቨርሲቲው የጋዜጠኝነት እና ስነ ተግባቦት መምህራን የሰጡ ሲሆን፣ ከሙያው ስነ ምግባር ጋር የተያያዙ እንዲሁም የሚታዩ የሙያ ክፍተቶችን ለመቅረፍ በሚያስችል መልኩ መሠጠቱ ነው የተገለፀው። በስልጠናው ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የዩንቨርሲቲው የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይመኑ ዳካ፣ በየጊዜው የሚሰጡ ስልጠናዎች የባለሙያውን አቅም በማጎልበት የሚፈለገውን ውጤት ለማረጋገጥ ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን ገልፀዋል። አቶ ይመኑ አክለውም ወቅቱን የጠበቀ ስልጠና በማዘጋጀት ጥራት ያለውና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ባለሙያዎች ላይ ቀጣይነት ባለው መልኩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል። በተለይም በሬዲዮ ጣቢያው የሚታዩ የሰው ኃይል እጥረት እና የግብዓት ችግርን ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አስረድተዋል። የዲላ ዩንቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ እንዳሻው መለሰ በበኩላቸው፣ ባለሙያዎች ከስልጠናው ያገኙትን ግንዛቤ እንደ ግብዓት በመጠቀም ተቋሙን ውጤታማ ለማድረግ በትጋት እንዲሰሩ አሳስበዋል። ስልጠናው መሰረታዊ የዜና አጻጻፍ የፕሮግራም እና የሬድዮ ይዘት አቀራረብ ባህሪያትን ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል። ስልጠናውን ከሰጡት መካከል የዩኒቨርሲቲው የጋዜጠኝነት እና ስነ ተግባቦት ትምህርት ክፍል ባልደረባ የሆኑት መምህርት ሰላማዊት ታፈረ፣ ከስልጠና ባለፈ የዳሰሳ ጥናት በማካሄድ ማህበረሰቡን ያማከሉ ፕሮግራሞችን መቅረጽ እንደሚገባ ገልፀው፣ ሰልጣኞች የሙያ ጊዴታቸውን በብቃት እንዲወጡ መሠል ስልጠናዎች ቀጣይነት ሊኖራቸው እንደሚገባ አሳስበዋል። ===###===

photo content
+8

photo content
+8

ዕድሜ፣ እናትነት ከትምህርት ያልገታቸው ብርቱ እናት =========*************========= ዲ.ዩ: ሰኔ 24/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) ዕድሜና እናትነት ከትምህርት ያልገታቸው፣ ለብዙዎች አርዓያ የሆኑ ብርቱ እናት፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተናን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። ወ/ሮ አልማዝ አሻራው ይባላሉ። የገደብ ወረዳ ነዋሪ ሲሆኑ፣ በቤተሰብ ጫና ምክንያት በ1982ዓ/ም ከ4ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እንዳቋረጡ ይገልፃሉ። የረጅም ጊዜ ህልማቸው የነበረውን ትምህርት ለማቋረጥ ሲገደዱ፣ አንድ ቀን ግን ተመልሰው ህልማቸውን እንደሚኖሩ እርግጠኛ እንደነበሩ አጋርተውናል። በ1983ዓ.ም ትዳር መስርተው መኖር የጀመሩት እኚህ እናት፣ የተለያዩ ፈተናዎችንና ተግዳሮቶችን ተሻግረው እዚህ ደርሰዋል። ስምንት ልጆችንም አፍርተዋል። ወ/ሮ አልማዝ አራት ልጆቻቸውን እሰከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ አስተምረው፣ ለወግ መዓረግ ያበቁ፣ የልጅ ልጆቻቸውን ያዩ ስለመሆናቸውም ነግረውናል። የቀሩት አራት ልጆቻቸው ደግሞ ከ5ኛ እሰከ 12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተናግረዋል። ትምህርታቸውን ዳግም መማር ያሰቡት ትላንት ያላሳኩትን፣ ያልኖሩትን ህልማቸውን ዳግም ለመኖር እንደሆነ ወ/ሮ አልማዝ ይገልፃሉ። እኚህ ብርቱ እናት ለትምህርት ያላቸው ፍቅር ልዩ እንደሆነ፣ ከህይወት ጉዟቸው መረዳት ይቻላል። ወ/ሮ አልማዝ በዘንድሮው ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው በመጀመሪያው ዙር በበይነ መረብ ፈተናቸውን መውሰድ ጀምረዋል። ጥሩ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ተምረው መመረቅ ህልማቸው እንደሆነም ገልፀውልናል። ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለወ/ሮ አልማዝ መልካሙን ሁሉ ይመኛል። ===###=== #የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ #UniversityOfTheGreenland

photo content

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን እየተቀበለ ነው ===========***********=========== ዲ.ዩ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም(ህ.ዓ.ግ) ዲላ ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ በዩኒቨርስቲው የፈተና ማዕከላት የተመደቡ ተፈታኞችን እየተቀበለ ነው። ከተለያዩ የጌዴኦ ዞን አከባቢዎች እንዲሁም አጎራባች ክልሎች በዘንድሮው ዓመት በዲላ ዩኒቨርሲቲ በሁለቱም የፈተና ማዕከላት ላይ የተመደቡ ተማሪዎች ከረፋድ ጀምሮ በመግባት ላይ ይገኛሉ። ፈተናው ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ በስድስት ዙሮች የሚሰጥ ሲሆን፣ በስድስቱም ዙሮች 7ሺህ የሚደርሱ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው እንደሚፈተኑ ይጠበቃል። ዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ፈተናው በሰላም እንዲጠናቀቅ ባዋቀራቸው ግብረ ሀይሎች አማካኝነት ውጤታማ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለተፈታኞች መልካም ፈተና እንዲሆን ይመኛል። #የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ #universityofthegreenland #EntranceExams

photo content
+8

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የተገነቡ ቤቶችን አስረከበ ============*************============ ዲ.ዩ: ሰኔ 20/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) ዲላ ዩኒቨርሲቲ በዲላ ከተማ በተለያዩ አከባቢዎች ለአቅመ ደካማ ወገኖች ያስገነባቸው ቤቶችን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አበባዬሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) በተገኙበት አስረክቧል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት እና አጋርነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተካልኝ ታደሰ፣ በተለያዩ ጊዜያት ላይ በዩኒቨርሲቲው በርካታ የበጎ ተግባር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው፣ በአሁኑ ጊዜም አራት ለሚደርሱ አቅመ ደካማ ወገኖች አዲስ ቤት በመገንባት እና አስፈላጊ የቤት ዕቃዎችንም ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር አሟልተው ማስረከባቸውን ጠቁመዋል። ተመሳሳይ የበጎ ተግባራትን ከሜሪ ጆይ እንዲሁም ከሌሎች ተባባሪ አካላት ጋር በመቀናጀት በስፋት ሲሰራ መቆየቱን እና አሁንም እየተሰራ እንደሚገኝ ያነሱት ደግሞ የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር)ናቸው። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶላሳ ዳዲ (ዶ/ር)ስራው እጅግ የሚያስመሰግን መሆኑን አንስተው፣ ችግር ያለባቸው ቦታዎችን በጥናት በመለየት የተሰራው ስራ የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል። በተለይ እጅጉን እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ወገኖችን መለየት ትልቅ ስራ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ከዚህም ባለፈ የሰው ሀይል እና ሀብትን በማንቀሳቀስ ፈፅማችሁ ስላሳያችሁ ላቅ ያለ ክብር አለኝ ሲሉ በስራው የተሳተፉ አካላትን አመስግነዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ ከዚህ በኃላ ይህ በጎ ተግባር እንደ ስራ ክፍል ብቻ ተወስኖ እንዳይቀር የዩኒቨርሲቲው አመራር የቤት ስራውን ወስዶ የበለጠ ስራውን እንደሚያሰፋ በመግለፅ፣ ስራውን ለማስቀጠል በትኩረት እንደሚሰራ ቃል ገብተዋል። የቤት እድሳት የተደረገላቸው ወገኖች ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው በመግለጽ፣ ዩኒቨርሲቲው ላደረገላቸው መልካም ስራ አመስግነዋል። በስራው ሁሉ ተባባሪ የነበሩ አካላትንም ባርከዋል። በመድረኩ ስራው እንዲሳካ ተባባሪ ለነበሩ አካላትም የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል። ===###=== #የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ #universityofthegreenland

photo content
+8

ዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1064 ተማሪዎችን አስመረቀ ============************============ ዲ.ዩ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) ዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 1064 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር )፣ ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልእክት በዩኒቨርሲቲው በነበራቸው ቆይታ ላሳዩት ትጋትና መልካም ሥነ ምግባር ምስጋና አቅርበው በርካታ ፈታኝ ሁኔታዎችን አልፈው ለምረቃ ቀን በመብቃታቸው እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተግባራዊ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ በሚል ተለይቶ ስራውን ከጀመረ አንስቶ በተመደበበት ልየታ ዘርፍ ይበልጥ ሙሉ ትኩረቱን በማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ ዩኒቨርሲቲው በተለይ በመንግስት የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት በመወጣት እንደ ሀገር የተጀመረውን የዕድገት እና የብልጽግና ጉዞ በትምህርት ዘርፉም ለማምጣት የበኩሉን ኃላፊነት እንደሚወጣ ተናግረዋል። ለአካባቢው ማህበረሰብ የተሻለ የጤና አገልግሎት ይሰጣል ተብሎ ከረዥም ጊዜ በፊት የተጀመረው የማስተማሪያ ሆስፒታሉ አዲሱ የሕንጻ ግንባታ ስራም ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት በአሁን ሰዓት በመጨረሻ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም፤ ተመራቂዎች ከዛሬ በኃላ ወደየ አካባቢያቸው ሲመለሱ ወይም ወደ ስራው ዓለም ሲሰማሩ ማህበረሰባቸውን በታማኝነት እና በጥሩ ስነ ምግባር እንዲያገለግሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የእለቱ የክብር እንግዳ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር)፣ ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት ሁኔታ በርካታ የተማረ የሰው ሀይል የሚያስፈልጋት ጊዜ ላይ ትገኛለች ያሉ ሲሆን፣ ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲው የነበራችሁን ቆይታ ከብዙ ውጣ ውረድ በኃላ በውጤታማነት ተወጥታችሁ ደስታችሁን በምታጣጥሙበት በዚህ የደስታችሁ ቀን ከእናንተ ጋር በመገኘቴ ታላቅ ክብርና ደስታ ይሰማኛል ብለዋል። ለተመራቂዎችና ተመራቂ ወላጆችና ቤተሰቦችም እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋቸዋል። ዶ/ር አበባየሁ አያይዘውም፤ ተመራቂ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያገኙትን እውቀትና ክህሎት ለሀገራቸው እድገትና ብልጽግና እንዲሁም ለልማት፣ ለሰላምና ለሀገር ግንባታ እንዲጠቀሙበት መልዕክት አስተላልፈዋል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ዋና ሬጅስትራር አስናቀ ይማም (ዶ/ር)፣ በዕለቱ በድህረ ምረቃ መርሃግብር በሶስተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ስድስት ምሩቃን፣ በሁለተኛ ዲግሪ 56፣ እና በመደበኛ ትምህርት በተለያዩ መስኮች፣ የዲፕሎማ ሴርተፊኬትን ጨምሮ በአጠቃላይ 816 ወንድ እና 248 ሴት በድምሩ 1064 ተማሪዎች ለምረቃ መብቃታቸውን አብስረዋል። በምረቃ መርሐ ግብሩ ከተመራቂ ተማሪዎች መካከል ከህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሜዲካል ላብራቶሪ ትምህርት ክፍል ተማሪ የቻለ ኑሬ አጠቃላይ ውጤት 3.93 በማምጣት ከወንዶች የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ የሆነ ሲሆን እንዲሁም፣ ከህግ ትምህርት ቤት በ3.81 ከፍተኛ ውጤት ያመጣችው ተማሪ ሊያ ብርሃኑ ደግሞ ከሴቶች የወርቅ ዋንጫ ተሸላሚ በመሆን ከዕለቱ የክብር እንግዳ እና ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ልዩ ሽልማታቸውን ተቀብለዋል። በምረቃው ላይ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች፣ የሴኔት አባላት፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አመራሮችና መምህራን፣ የጌዴኦ አባገዳዎችና የኃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል። ===###=== #የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ #universityofthegreenland #Congratulations

photo content
+8

#Only_Four_days_to_go! #classof2026 #universityofthegreenland #alumni Congratulations!
#Only_Four_days_to_go! #classof2026 #universityofthegreenland #alumni Congratulations!

#Only_Five_days_to_go! #classof2026 #universityofthegreenland #alumni
#Only_Five_days_to_go! #classof2026 #universityofthegreenland #alumni

photo content

photo content

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የምስጋና መልዕክት =========**********========= ዲ.ዩ: ሰኔ 12/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶላሳ ዳዲ (ዶ/ር) ከሰኔ 4 ጀም
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የምስጋና መልዕክት =========**********========= ዲ.ዩ: ሰኔ 12/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶላሳ ዳዲ (ዶ/ር) ከሰኔ 4 ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው የተሰጠውን የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መጠናቀቁን በማስመልከት የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል። ዩኒቨርሲቲው ፈተናው ከመጀመሩ በፊት በርካታ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ስያከናውን መቆዩቱን ያስታወሱት ዶ/ር ቶላሳ፣ በፈተናው ወቅትም አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍና ክትትል ሲደረግ እንደነበር አንስተዋል። እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለፃ፣ በዩኒቨርሲቲው የተሰጠው የመውጫ ፈተና ያለ ምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ የበርካታ ባለድርሻ አካላት ርብርብ ነበረበት። ፈተናው በስኬት ተጀምሮ እንዲያልቅ በዩኒቨርሲቲው የተቋቋመው ግብረ ሀይል፣ በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡት የፈተና ማዕከላት አስተባባሪዎች፣ የአይሲቲ ባለሙያዎች፣ የፌደራል እና የካምፓስ ፖሊስ አባላት እንዲሁም ሌሎችም ተሳታፊዎች ሚና የጎላ እንደነበር በማስታወስ አመስግነዋል። አሁን ላይ በዩኒቨርሲቲዎች እየተሰጡ የሚገኙ ፈተናዎች በዘርፉ የነበሩ ክፍተቶች እንዲቀንሱ እያደረጉ መሆናቸውን የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ፣ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ዩኒቨርሲቲው ከትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም ከትምህርት ዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አንስተዋል። የመውጫ ፈተናውን የወሰዱ ተማሪዎች መልካም ውጤት እንዲገጥማቸውም ፕሬዝዳንቱ ያላቸውን ምኞት ገልፀዋል። ===###=== #የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ #universityofthegreenland