Dilla University Official
الذهاب إلى القناة على Telegram
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Dilla University Official
تُعد قناة Dilla University Official (@dprd9) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 17 641 مشتركاً، محتلاً المرتبة 11 269 في فئة التعليم والمرتبة 1 950 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 17 641 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 01 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 25، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -12، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 23.77%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.82% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 193 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 732 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 17.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“University of the Green Land”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 02 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
17 641
المشتركون
-1224 ساعات
+477 أيام
+2530 أيام
أرشيف المشاركات
እንኳን አደረሳችሁ!
===*****===
መላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1ሺህ 501ኛው የነቢዩ መሀመድ የመውልድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ በዓሉ የሰላም የፍቅር እና የአንድነት እንዲሆንላችሁ ይመኛል።
ኢድ ሙባረክ!
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
🔔አዲስ ማስታወቂያ📢
=====*****=====
በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል ለተመደባችሁ የድህረ ምረቃ መግብያ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ
በዩኒቨርሲቲው የምትፈተኑ ተፈታኞች በቀን 20/12/2018ዓ.ም ከጧቱ 3:00 ጀምሮ እስከ 6:00 ባለው ጊዜ ብቻ መሆኑን አውቃችሁ ለፈተናው እንድትዘጋጁ ስንል እናሳስባለን።
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland
#NGATEXAM
"ተቋሙ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ለአጀንዳ 2030 ግብ መሳካት ቁርጠኝነቱን እያሳየ ይገኛል" - ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር)
===========*************============
ዲ.ዩ: ነሐሴ 11/12/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
በዲላ ዩኒቨርሲቲ በመደራጀት ላይ የሚገኙ የስማርት መማሪያ ክፍሎች ያሉበትን ደረጃ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በዩኒቨርሲቲው በአራቱም ጊቢዎች እጅግ ዘመናዊ የማስተማሪያ ቁሳቁሶች የተሟላላቸው የስማርት መማሪያ ክፍሎችን በማደራጀት ለመጪው የትምህርት ዘመን ዝግጁ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
ፕሬዝዳንቱ በሀሴዴላ ጊቢ እና በማስተማሪያ ሆስፒታሉ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ደረጃ የተመለከቱ ሲሆን፣ ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን በማደራጀት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ለአጀንዳ 2030 ግብ መሳካት ቁርጠኝነቱን እያሳየ እንደሚገኝ አውስተዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ፕሮጀክቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ እና ክትትል እንደሚደረግም ገልፀዋል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ በአዲሱ የትምህርት ዘመን፣ በርካታ አዳዲስ የትምህርት ግብዓቶችን በማሟላት ተማሪዎቹን ለመቀበል ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ስለመሆኑ ተገልጿል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland
የኩላሊት እጥበት ማዕከል ግንባታ የመሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ
==============**********===========
ዲዩ: ነሐሴ 10/2018 አ.ም (ህ.ዓ.ግ)
በዲላ ከተማ በሜሪጆይ ኢትዮጵያ አማካኝነት ለሚገነባው የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ግንባታ፣ የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እና የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እንዲሁም የድርጅቱ ኃላፊዎች በተገኙበት የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጧል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው በማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት በኩል የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አንስተው፣ የሜሪጆይ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ተገንብቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ ተቋሙ የበኩሉን እንደሚወጣ አስረድተዋል።
ዩኒቨርሲቲው በሆስፒታሉ አማካኝነት ከሚሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ መሠል የማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ስራዎች ላይ ከወትሮው በተለየ መልኩ ድጋፍ እንደሚያደርግም አንስተዋል።
የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር)ሜሪጆይ የኩላሊት እጥበት ማዕከል በከተማው መገንባቱ በጤናው ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ እንደሚሆን ገልፀው፣ ተገንብቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ ባለድርሻ አካላትን ለማስተባበር እና ፕሮጀክቱ እውን እንዲሆን በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልፀዋል።
በከተማው የሜሪጆይ ኢትዮጵያ የኩላሊት እጥበት ማዕከል መገንባ፣ የማህበረሰቡን የጤና ዘርፍ ፍላጎት ለማሟላት ከፍተኛ ሚላ እንደሚኖረው የገለፁት ደግሞ የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የዲላ ቅርንጫፍ አስተባባሪ አቶ ግርማ ደብረ ናቸው።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ፣ የዲላ ከተማ አስተዳደር እና ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ማዕከሉ ተገንብቶ እስኪጠናቀቅ በትብብር ለመስራት እና ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር ማዕከሉን እውን ለማድረግ እንደሚሰሩ በመድረኩ ተገልጿል።
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲው
#UniversityOfTheGreenland
በዲላ ዩኒቨርሲቲ 11 ፕሮግራሞችን በሀገር አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው።
ከየትምህርት ክፍሎቹ የተውጣጡ መምህራን ስልጠና በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) በስልጠናው ቦታ በመገኘት ሂደቱን የተመለከቱ ሲሆን፣ መምህራኖቹ ጠንክረው እንዲሰሩ በማበረታታት ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠውላቸዋል።
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ!
#CALL_FOR_EXTERNAL_REVIEWERS
Dilla University cordially invites qualified professionals- university professors and industry experts to participate in an outcome based Educations (OBE) curriculum reviewer validation workshop scheduled for Aug 27, 2026GC.
See the poster for more information!
#UniversityOfTheGreenland!
"ተወዳዳሪ ዜጋ የሚፈልቅባቸው ሞዴል ትምህርት ቤቶች እንዲሆኑ በትኩረት ይሰራል" ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር)
=========*************=========
ዲ.ዩ: ነሐሴ 07/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
በዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር)የተመራ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራር ልዑክ ቡድን በዩኒቨርሲቲው ስር የሚገኙ የቅድመ መደበኛ፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና የሁለተኛ ደረጃ የኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
የየትምህርት ቤቶቹ የስራ ኃላፊዎችም ለልዑካኑ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በየትምህርት ቤቶቹ ያሉ የግብዓት እና ተያያዥ ችግሮችን ለመፍታት የተቋሙ አመራሮች ምልከታ በማድረጋቸው አመስግነው፣ ለተሻለ አፈፃፀም ከአመራሩ ጋር ተቀናጅተው ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር በየትምህርት ቤቶቹ ያሉ የፋሲሊቲ እጥረቶችን ማሟላት እና ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ዝግጁ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።
ነገ ላይ ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መጋቢ የሆኑ ትምህርት ቤቶችን መደገፍ ነገን ዛሬ ላይ መስራት በመሆኑ፣ አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍና ክትትል ይደረጋልም ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ። መሠረተ ልማት ላይ መስራት ካልተቻለ የሚታሰበውን ብቁ ዜጋ መፍጠር ስለማይቻል፣ ትምህርት ቤቶቹ ያሉበትን ቁመና ማዬታችን ቀጣይ የምንሰራቸውን የቤት ስራዎች እንድንለይ ይረዳናል ብለዋል።
ከምልከታው መልስ የኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤቶቹ የቅድመ ሁኔታ ግምገማን በተመለከተ የተዋቀረው ኮሚቴ፣ የጥናት ውጤቱን ለፕሬዝዳንቱና ለከፍተኛ አመራሩ አቅርቧል።
የሰው ኃይል እጥረት እንዲሁም የአይሲቲ መሠረተ ልማት ጉድለቶች እና ሌሎች እንቅፋቶች ቢኖሩም፣ የመምህራን ትምህርት ከዩኒቨርሲቲው የትኩረት መስኮች አንዱ መሆኑ፣ በቂ የሰው ኃይልና ቤተሙከራዎች መኖራቸው፣ ትምህርት ቤቱን ለመደገፍ ትልቅ አቅም እንደሚሆን በሪፖርቱ ተመላክቷል።
ለትምህርት ቤቶቹ የፋይናንስ ድጋፍ ቢደረግ፣ ለመምህራኖቹ ተከታታይ ድጋፍና ክትትል ቢደረግ፣ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ቢመለሱ አሁን ካለበት የተሻለ ማድረግ እንደሚቻል ተገልጿል።
ፕሬዝዳንቱ ትምህርት ቤቶቹ የሚያስፈልጋቸውን የትምህርት ግብዓቶች በቅርበት በመከታተል ተወዳዳሪ ዜጋ የሚፈልቅባቸው ሞዴል ትምህርት ቤቶች እንዲሆኑ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
በትምህርት ቤቶቹ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እና የመሠረተ ልማት ችግሮችን ለመፍታት በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ የገለፁት ፕሬዝዳንቱ፣ በቀጣዩ የትምህርት ዘመን የቅድመ ዝግጅት ስራ ላይ ሁሉም የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎችም ትምህርት ቤቶቹ ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ፣ የትምህርት ጥራት እንዲረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland
"በቀናነት ከሰራን፣ ችግሮች ሲኖሩ በመቀራረብ ከፈታን፣ ተቋማችንን ወደተሻለ ደረጃ ከፍ ማድረግ እንችላለን" - ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር)
============**************============
ዲዩ: ነሐሴ 05/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል በየዘርፉ የቀረቡ የ2018ዓ.ም የእቅድ ክንውን ሪፖርትን ገምግሟል።
በበጀት ዓመቱ በመማር ማስተማር ዘርፍ፣ በምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት፣ በዲጅታላይዜሽን ረገድ፣ አጠቃላይ መሠረተ ልማት ማስፋፊያ ስራዎች፣ የጤና ዘርፍ ተግባራት፣ በግንባታ ፕሮጀክቶች አፈፃፀምና በሌሎችም ዘርፎች ላይ የተከናወኑ ተግባራት ለካውንስሉ ቀርበዋል።
የካውንስል አባላት በቀረቡ ሪፖርቶች ላይ የተለያዩ ሀሳብና አስተያዬት ሰጥተዋል። አገልግሎት ያቆሙ መሳሪያዎችን ወደ አገልግሎት በመመለስ ረገድ የተሰራው ስራ፣ የስማርት መማሪያ ክፍሎች ግንባታ፣ በበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችና የነበሩ የጉድኝት ተግባራት የሚበረታቱ ስለመሆናቸው የካውንስሉ አባላት አንስተዋል።
የመምህራን የቤት ችግርን ለመቅረፍ የተጀመሩ ስራዎች እንደመኖራቸው መጠን በአጭር ጊዜ ለመፍታት እንዲሰራ፣ አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍና ክትትል እንዲደረግም የካውንስል አባላቱ ጠይቀዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ከካውንስሉ የተነሱ ሀሳቦችን እንደ ግብዓት በመውሰድ ቀሪ ተግባራቶቻችን ላይ በማከል የተሻለ ተቋማዊ አፈፃፀም እንዲኖር ጠንክረን እንሰራለን ብለዋል።
የትምህርት ሴክተር ሪፎርምን መሬት የማውረድ ስራ በትኩረት መሠራት እንዳለበት የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ፣ ከሪፎርሞቹ አንዱ የሆነው የትኩረት አቅጣጫ እና የልየታ ስራ ላይ የቀሩ ተግባራትን መከወን የአዲሱ የትምህርት ዘመን ቀዳሚ ስራ መሆኑን ገልፀዋል። ቤተሙከራዎች እና ፕሮግራሞቻችንን በሀገር አቀፍ እና በዓለምአቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኙ ለማድረግ በትኩረት መስራት ይኖርብናልም ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ።
የራስ ገዝነት ስራ ቀጣዩ የቤት ስራችን ሊሆን ይገባል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ወደዚህ ለመግባት በሚያስችሉ አመቺ ሁኔታዎች ላይ ማተኮር ይገባል ብለዋል። የመማሪያ ክፍሎችን ዲጂታላይዝ ለማድረግ መሠረተ ልማቶችን ለማሟላት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አክለዋል።
ከመምህራን ቤቶች ጋር ተያይዞ ከካውንስሉ ለተነሳው ጥያቄ፣ የመምህራንን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል።
በቀናነት ከሰራን፣ ችግሮች ሲኖሩ በመቀራረብ ከፈታን፣ ተቋማችንን ወደተሻለ ደረጃ ከፍ ማድረግ እንችላለን ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ የታቀዱ ስራዎች ሁሉ ከግብ እንዲደርሱ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል ድጋፉን እንድያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል።
የኮምፒውተር ቤተ-ሙከራዎች ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ በአዲስ መልክ ለማደራጀት እየተሰራ እንደሚገኝ የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ፣ የበይነ መረብ ትምህርት ስርዓትን እውን ለማድረግ በተቋም ደረጃ ስቱዲዮ ለመገንባት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል። የፀጥታ ስራዎችን የበለጠ የማጠናከር፣ አዲሱ ሆስፒታልን ወደ ስራ የማስገባት ስራ የቀጣይ ጊዜያት የትኩረት ዘርፎች አካል ስለመሆናቸውም አንስተዋል።
የአመራር ብቃትን የበለጠ ለማጎልበት እንዲሁም በሁሉም ዘርፎች ላይ የተለያዩ ተከታታይ ስልጠናዎች እንደሚዘጋጁ ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል። በዩኒቨርሲቲው የተጀመሩ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ከወትሮ በተለየ መልኩ እንደሚሰራም አውስተዋል። በዩኒቨርሲቲው ስር ያሉ የምርምር ጣቢያዎች አስፈላጊው ሁሉ መሠረተ ልማት እንዲሟላላቸው መስራት እንደሚያስፈልግም ፕሬዝዳንቱ አንስተዋል።
በሪፖርቱ ላይ የቀረቡ መልካም ስራዎችን ለማስቀጠል፣ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይም በየደረጃው ያለው የዩኒቨርሲቲው አመራር በመቀናጀት ለተሻለ አፈፃፀም አብሮ እንዲሰራ ጥሪ ቀርቧል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
የተቋሙ ዓለምአቀፍ ታይታ እንዲጨምር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
===========***********=========
ዲ.ዩ: ሐምሌ 30/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሶስት ጆርናሎች በሀገር አቀፍ ደረጃ እውቅና ማግኘታቸውን ተከትሎ በስራው ለተሳተፉ አካላት ዩኒቨርሲቲው እውቅና ሰጥቷል።
እውቅና ያገኙ የዩኒቨርሲቲው ጆርናሎችም Ethiopian Journal of Environment and Development (EJED), African Journal of Health Sciences and Medicine (AJHSM) እና Dilla Journal of Education (DJE) የተሰኙ ናቸው።
የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር ሶስቱንም ጆርናሎች እውቅና እንድያገኙ መደረጉ እጅግ የሚያስደስት እንደሆነ ገልፀው፣ የጆርናሎቹ ታይታ እንዲጨምር በትጋት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።
በየጊዜው ምንም አይነት ትዕዛዝ ሳይጠበቅ የሚመጡ ለውጦችን እየተከታተሉ መስራት ያስፈልጋል ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፣ አሁን ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተገኘውን እውቅና በዓለም አቀፍ ደረጃም እውቅና መስራት እንደሚጠበቅ ገልፀዋል።
ምክትል ፕሬዝዳንቱ በመጪዎቹ ጊዜያት ላይ ዓለምአቀፍ እውቅና የሚያገኙ ጆርናሎች እንዲኖሩን ካሁኑኑ መታተር ይገባናል ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል። አክለውም ይህንን ስራ በበላይነት ሲመሩ የነበሩ እና ሲለፉ የነበሩ አካላትን አመስግነዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምር፣ ህትመት፣ ስነ ምግባርና ስርፀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ምስጋኑ ለገሰ በበኩላቸው፣ በትምህርት ሚኒስቴር በየደረጃው አስፈላጊውን የግምገማ ሂደት በማለፍ እውቅና ያገኙ ሶስቱም ጆርናሎች ከዩኒቨርሲቲው የትኩረት አቅጣጫ ጋር የተያያዙ መሆናቸውን ገልፀዋል። ጆርናሎቹ ወቅታዊ የሆኑ ከሀገር ውስጥ ብሎም ከውጭ ሀገርም ጭምር ችግር ፈቺ የሆኑ ምርምሮች እንዲሁም ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ የምርምር ውጤቶች የሚታተምባቸው መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
አሁን ላይ እውቅና ያገኙ የዩኒቨርሲቲው ሶስቱም ጆርናሎች ሀገራዊ እና ተቋማዊ ፋይዳቸው የጎላ እንደሆኑ የገለፁት ዶ/ር ምስጋኑ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃም የተቋሙን ቅቡልነት እንደሚያሳድግ ተናግረዋል። በጆርናሎቹ ላይ በየጊዜው የሚታተሙ የምርምር ውጤቶች በሀርድኮፒ በየመጻህፍት ቤቱ አልያም በዩኒቨርሲቲው ዌብሳይት ላይ ማግኘት እንደሚቻልም ገልፀዋል።
ለስራው መሳካት ከፍተኛ አበርክቶ የነበራቸው የኤዲቶሪያል ቦርዱ፣ ገምጋሚዎች፣ የቋንቋ አርታኢዎች፣ የለይአውት ዲዛይነሮች እንዲሁም ይህ ስራ እዚህ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ከፍተኛ ድጋፍ ያበረከቱ የዩኒቨርሲቲው አመራር አካላት እና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን ዶ/ር ምስጋኑ አመስግነዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ስርፀት ዴስክ ሀላፊ የሆኑት አቡኑ አረጋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የጆርናል እውቅና ማግኘት መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን በመግለጽ፣ ትልቁ ጉዳይ ጆርናሎቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታይታቸው እንዲጨምር መስራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።
ይህንን ስራ ከፍ ባለ ደረጃ ለመምራት ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ የገለፁት ዶ/ር አቡኑ፣ የአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ በትኩረት መስራት ስራውንም አካታች በሆነ መንገድ ማስኬድ ያስፈልጋል ብለዋል።
በመድረኩ በስራው ለተሳተፉ አካላት የእውቅና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland
የተቋሙን የሪፎርም ስራዎች ልያሳኩ በሚችሉ ዘርፎች ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት እንዲሰሩ ጥሪ ቀረበ
==========**************=========
ዲ.ዩ: ሐምሌ 30/2018ዓ.ም(ህ.ዓ.ግ)
የዲላ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት በስሩ ካሉ ኮሌጆችና ዳይሬክተሮች ጋር የዘርፉን የ2018ዓ.ም የዕቅድ አፈፃፀም ገምግሟል።
በበጀት ዓመቱ በመማር ማስተማር፣ በመምህራን ልማት፣ በስርዓተ ትምህርት ክለሳ፣ በፕሮግራም እውቅና የዲጂታላይዜሽን ስራዎች እና በአካቶ ትምህርት ረገድ የተሰሩ ስራዎች ዙሪያ የቀረበው ሪፖርት ላይ ምክክር ተደርጓል።
በሌላ በኩል በደሊቨሮሎጂ፣ የውስጥ ገቢ ማጠናከር እና ሌሎችም በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራት ላይ የኮሌጅ ዲኖችና ዳይሬክተሮች የአፈፃፀም ሪፖርት አቅርበዋል።
በቀረቡት ሪፖርቶች ላይም ጥያቄዎችና ሀሳቦች ተነስተው በሚመለከታቸው የስራ ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ታምራት በየነ (ዶ/ር) በበጀት ዓመቱ የዘርፉን ስራዎች በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱት መምህራን፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ ኮሌጅ ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ዩኒቨርሲቲው የተሰጠውን የተግባር ሳይንስ ተልዕኮ፣ የስርዓተ ትምህርት ክለሳ ስራ አጠናቆ ወደ ተግባር በመግባት እንዲሁም ለዘርፉ ተቆጥሮ የተሰጠውን የቁልፍ ውጤት አመላካቾች (KPIs )በአግባቡ በመተግበር የትምህርት ዘመኑን በጥሩ ውጤት ማገባደዱን ምክትል ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል።
በአዲሱ የትምህርት ዘመን በሂደት ያሉትን የተጓዳኝ የስርዓተ ትምህርት ክለሳ፣ የበይነ መረብ ትምህርት፣ የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ግምገማ፣ የአካዳሚክ ፕሮግራሞች እውቅና ማግኘት፣ የስማርት መማሪያ ክፍሎች ግንባታ፣ የመምህራን ልማት እና በሌሎች ዘርፎችም ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።
አክለውም የመምህራንና ተማሪዎች ኤክስተርንሺፕ፣ የኢንዱስትሪ እና የዩኒቨርሲቲ ትስስር፣ የወረቀት ፈተናን ወደ በይነመረብ መቀየርና ሌሎች የትምህርት ጥራት የሚያግዙ እንዲሁም የተቋሙን የሪፎርም ስራዎች በሚያሳኩ ዘርፎች ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ትኩረት በማድረግ መስራት ይገባል ሲሉ ምክትል ፕሬዝዳንቱ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመድረኩ ኮሌጅ ዲኖችና ምክትል ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች እንዲሁም ሌሎች ተጠሪ ጽ/ቤቶች ተገኝተዋል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland
በቀርጫንሼ ግሩፕ የደበቃ ዘመናዊ የቡና እርሻ ልማት ላይ ምልከታ ተደረገ
============*************=============
ዲዩ: ሐምሌ 30/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)
በዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) የተመራ የዩኒቨርሲቲው ልዑክ ቡድን በቀርጫንሼ ግሩፕ ስር ከሚገኙ የቡና እርሻዎች መካከል የደበቃ ዘመናዊ የቡና እርሻ ልማት እንዲሁም በዲላ ዩኒቨርሲቲ፣ ቀርጫንሼ ግሩፕ እና ስታርባክስ የጋራ ቅንጅት ለቆላማ አከባቢዎች የሚስማሙ የቡና ዝርያ ልየታ ጥናት የምርምር ስራ ላይ ምልከታ አድርጓል።
የቡና እርሻው በ400 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፣ ያለምንም የዛፍ ጥላ በክፍት መሬት ላይ እየለማ የሚገኝ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃም ተምሳሌት የሆነ የቡና እርሻ እንደሆነ ተመላክቷል።
ከቡና እርሻ ጉብኝቱ ባሻገር በአንድ ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ እና ከ1.5ሚሊዮን በላይ ችግኞችን የማፍላት አቅም ያለው ዘመናዊ የደበቃ ችግኝ ጣቢያ ላይም ምልከታ የተደረገ ሲሆን፣ ዲላ ዩኒቨርሲቲ አራት የሚደርሱ የኮስታሪካ የቡና ዝርያዎች እንዲሁም ሌሎች በሀገር ውስጥ ባሉ የቡና ዝርያዎች ላይ እያደረገ የሚገኘውን የጋሪዮሽ ጥናትን ተመልክተዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደተናገሩት፣ የቀርጫንሼ ግሩፕ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከተለመደው የቡና እርሻ ለየት ባለ መልኩ ያለምንም የጥላ ዛፍ በክፍት መሬት ላይ ቡናን ማምረት እንደሚቻል ያረጋገጠ ተቋም ነው። በዘርፉ የሚገኙ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የሚታይ ለውጥ እያመጣ ስለመሆኑም አንስተዋል።
በግሩፑ እየተሰራ ያለው ስራ በሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ የሚጫወተው ሚና ቀላል እንዳልሆነ የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ፣ ተቋሙ ትልቅ የምርምር ተቋም ሆኖ የሚያገለግል ስራ መስራቱን ተናግረዋል። በእርሻው ላይ ያዩት ነገር ከቃልም በላይ እንደሆነ በመግለጽ፣ ተቋሙ ለዩኒቨርሲቲው ላሳየው ትብብር አመስግነዋል።
የሁለቱ ተቋማት ባለሙያዎችን በማቀናጀት የትብብር ፕሮጀክቶችን መስራት እንደሚገባ የገለፁት ዶ/ር ቶሎሳ፣ ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ የሚያሰለጥናቸውን ተማሪዎች ወዲህ በማምጣት የተግባር ትምህርት እንዲወስዱ ብሎም የተጀመሩ የትብብር ተግባራትን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።
ዩኒቨርሲቲው በቡና ላይ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የገለፁት ፕሬዝዳንቱ፣ ከዚህ ቀደም ሁለቱ ተቋማት በተፈራረሙት የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር፣ ወደፊት በጋራ በሚሰራባቸው ጉዳዮች ላይም ከግሩፑ ጋር የጋራ መድረኮችን ማመቻቸት እንደሚገባ ገልፀዋል።
የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ሀብታሙ ተመስጌን (ዶ/ር)፣ የቀርጫንሼ ግሩፕ ዲላ ዩኒቨርሲቲ በቡናው ዘርፍ ላይ እየሰራ የሚገኘውን ተግባራት ከግምት በማስገባት ከዩኒቨርሲቲው ጋር በርካታ የምርምር ስራዎችን በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልፀው፣ ከሌሎች ተቋማትም ጋር የትብብር መንገዶችን እየከፈቱ እንደሆነ ገልፀዋል።
ምክትል ፕሬዝዳንቱ የተግባር ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ የሚፈልገውን ሽግግር ለማፋጠን በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
የቀርጫንሼ ግሩፕ ቡናን ከጓሮ በማውጣት የቡና ነፃነትን ያወጀ ተቋም እንደሆነ የገለፁት ዶ/ር ሀብታሙ፣ ይህንን ልምድ ማሳደግ እና ወደ ማህበረሰቡም ማውረድ እንደሚገባ ገልፀዋል። ዩኒቨርሲቲው የሚሰራቸውን የጋሪዮሽ ጥናትን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አውስተዋል።
የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ማቲዎስ ሀብቴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የቀርጫንሼ ግሩፕ እያለማ የሚገኘው የቡና እርሻ ትምህርት የሚወሰድበትና ተቋማት ልምድ ሊቀስሙበት የሚገባ መሆኑን ጠቁመው፣ እዚህ ያለውን ቴክኖሎጂ ወደ ማህበረሰቡም ለማውረድ እንተቋም ትልቅ ስራ ይጠብቀናል ብለዋል። መምህራንና ተማሪዎችም ሳይቱ ላይ በመምጣት ልምድ የሚወስዱበትን አጋጣሚ መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል።
በክፍት መሬት ላይ የተተከሉ ዝርያቸው የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ያሉበት ደረጃ ጥሩ ተሞክሮ የሚወሰድባቸው እንደሆነም በምልከታው ላይ ተገልጿል።
===###===
#የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ
#UniversityOfTheGreenland
