uk
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Відкрити в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 13 323 підписників, посідаючи 1 756 місце в категорії Транспорт та 2 541 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 13 323 підписників.

За останніми даними від 16 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 90, а за останні 24 години на 8, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 40.85%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 15.40% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 439 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 050 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 17.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 17 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Транспорт.

13 323
Підписники
+824 години
+217 днів
+9030 день
Архів дописів
የሙስሊ - ኮሪ - ቴሩ ምዕራፍ አንድ የመንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ እየተከናወነለት ነው ሰመራ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኢ መ አ):- በአፋር ክልል የሙስሊ - ኮሪ - ቴሩ መንገድ ፕሮጀክት የመጀመሪያው ምዕራፍ ከኪሎሜትር 00 እስከ ኪሎሜትር 84 ያለው የአስፋልት ንጣፍ እየተከናወነለት ነው። የመንገድ ግንባታው 84 ነጥብ 2 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ በአፋር ክልል አውሲረሱ እና ፋንቲረሱ ዞኖች ውስጥ የሚገኙ ሁለት ወረዳዎችን እና በርካታ ቀበሌዎችን ያስተሳስራል። አሁን ላይ የ20 በመቶ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ፣ የ21 በመቶ የስትራክቸር፣ የ98 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ34 በመቶ ሰብቤዝ እንዲሁም የ10 በመቶ የአስፋልት ንጣፍ ሥራዎች ተከናውነዋል። የሰባት ድልድዮች ግንባታም በፕሮጀክቱ ተካትቷል። በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 56 በመቶ ደርሷል። የተመዘገበውን አበረታች አፈጻጸም አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። የመንገድ ግንባታው የአካባቢውን የአርብቶ አደር ማኅበረሰብ ባማከለ መልኩ፣ የቁም እንስሳት በተለይ ግመሎች መንገዱን በሚያቋርጡበት ጊዜ ጉዳት እንዳይገጥማቸው ተገቢው የጥንቃቄ ሥራ እየተሠራ ይገኛል። ግንባታውን ዓለም-አቀፋ ቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጅነሪንግ ከፌደራል መንግስት በተመደበ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ወጪ ያከናውናል። ኢንስራድ ሲቪል ሲስተም ኢንጅነሪንግ ፕሮጀክቱን በማማከር እና በመቆጣጠር በኩል ይሳተፋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የኮሪ እና መባይ ወረዳዎችን ጨምሮ በመስመሩ የሚገኙ በርካታ ቀበሌዎችን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ያስተሳስራል። የጤና፣ የትምሕርት እና መሰል የማኅበራዊ ተቋማት ተደራሽነትን በማስፋት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታል። የዚሁ መንገድ ትስስር ቀጣይ ክፍል የኾነው ከኪሎሜትር 84 እስከ ኪሎሜትር 156 ድረስ ያለው የፕሮጀክቱ ምዕራፍ ሁለት በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አካሄዶች ላይ ውይይት ተካሄደ የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚንስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የኢ መ አ መንገድ ምርምር ማዕከልን ጎብኝተዋል አዲስአበባ፣ መጋቢት 09፣ 2017 (ኢ መ አ):- የመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አካሄዶች ላይ በኢ መ አ የመንገድ ምርምር ማዕከል ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ ላይ በመንገድ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶች፣ ዘርፉን የገጠሙት ተግዳሮቶች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ ገለጻ ተደርጓል። በተጨማሪም ከሚንስቴር መ/ቤቱ ድጋፍ ሊደረግባቸው የሚችሉ ጉዳዮችም ተለይተው ቀርበዋል።  በዚህም ረገድ የሀገሪቷን የመንገድ ሽፍን የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራሙ በ1989 ከነበረበት 23 ሺህ ኪሎሜትር አሁን ላይ ወደ 171 ሺህ ማድረስ እንደተቻለ ገላጻው ላይ ተጠቁሟል። ሆኖም ባለፉት ጊዜያት የገጠሙ የበጀት እጥረት፣ የግንባታ ግብዓት ዋጋ መናር፣ የወሰን ማስከበር፣ የጸጥታ ስጋት፣ የመንገድ ጥገና ላይ ያሉ ክፍተቶች(የማሽነሪ እና የባለሞያ እጥረት)፣ ደካማ የፕሮጀክት አመራር እና የሀገር በቀል የሥራ ተቋራጮች ተወዳዳሪነት ማነስ ዘርፉን እንደፈተኑት ተነስቷል። ይህም ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ዋጋ እና በቀመጠላቸው ጊዜ እንዳይጠናቀቁ እንዲሁም ብቁ እና ተወዳዳሪ ተቋራጮች ገበያ ላይ እንዲቀንሱ ተጽዕኖ አሳድሯል ተብሏል። የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ማድረግ፣ መጠናቀቅ በሚችሉ ፕሮጀክቶች ላይ ቅድሚያ ትኩረት መስጠት እንዲሁም የግብዓት አቅርቦት ላይ ያሉ ችግሮችን መቅረፍ እንደሚገባ በገለጻው ላይ ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራህማን (ኢ/ር)፤ ዘርፉ ላይ የሠው ኃይል እጥረት መኖሩን ጠቁመው፣ አሁን ካለው በተሻለ ዘርፉ ብቁ እና ሥልጡን በኾኑ ባለሞያዎች በሳይንሳዊ መንገድ መመራት ይኖርበታል ብለዋል። የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚንስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ፤ መንገድ በሀገሪቱ ዕድገት ላይ የማይተካ ሚና እንዳለው አንስተው፣ የዘርፉ ተግዳሮቶች ውስብስብ በመኾናቸው ለመሠረታዊ ችግሮች ቅድሚያ መስጠት ይገባል ብለዋል።  ካለው የሥራ ስፋት እና ውስብስብነት አንጻር ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ በመፍትሄዎቹ ላይ መምከር እንደሚገባም ገልጸዋል። ቀሪ የወሰን ማስከበር ሥራዎችን ማጠናቀቅ እና ከአዋጁ ጋር በተገናኘ ያሉ ክፍተቶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መሥራት፣ የመንገድ ጥገና ዘርፉን ለግል ተቋራጮች ሳቢ ማድረግ እንዲሁም ተቋማዊ ባሕልን ዳግም ማጤን እንደሚገባ ክብርት ሚንስትሯ አሳስበዋል። በቀጣይም በሚንስቴር መ/ቤቱ በኩል ድጋፍ ሊደረግባቸው የሚቻልባቸውን ጉዳዮች በመለየት አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግም አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል የኢ መ አ የመንገድ ምርምር ማዕከል አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ ላይ ገለጻ እና ጉብኝት ተደርጓል። ማዕከሉ አዳዲስ ሐሳቦችን የሚያመነጭ እና ዘመኑን የዋጀ መኾን እንደሚገባው እንዲሁም ከምርምር በዘለለ የመንገድ ዘርፉን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተጠቁሟል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የላሊበላ - ኩልመስክ - ሙጃ መንገድ ፕሮጀክት እየተከናወነ ይገኛል አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4 ፣ 2017 (ኢ መ አ) 48 ነጥብ 78 ኪሎሜትር የሚረዝመው የላሊበላ - ኩልመስክ - ሙጃ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ፕሮጀክት በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ የዲዛይን ፣ የአፈር ጠረጋ ፣ የቆረጣ ፣ የሙሌት ፣ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦ ቀበራ፣ የሰብ ቤዝ ሥራዎች እንዲሁም የድልድይ ግንባታ ጨምሮ እየተከናወነ ነው፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ዓለም አቀፉ ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪነግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ሲሆን የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራ ቤዛ ኢንጅነሪንግ ኬኒያ ሊሚትድ እየሰራው ነው፡፡ የመንገዱ አጠቃላይ የጎን ስፋት በገጠር ከ8-10 ሜትር ፣ በቀበሌ 16 ሜትር እንዲሁም በወረዳ 20.5ሜትር ስፋት ያለው ነው፡፡ ለግንባታ የሚውለው 1,888,292,297 (አንድ ቢሊየን ስምንት መቶ ሰማንያ ስምንት ሚሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ ሁለት መቶ ዘጠና ሰባት ብር ) ብር በኢትዮጵያ መንግስት ወጪ የተደረገ ነው፡፡ በአካባቢው በሚስተዋለው ወቅታዊው የፀጥታ ችግር ምክንያት አስፈላጊ የሆኑ የግንባታ ግብዓቶችን እና ማሽሪዎችን በበቂ ሁኔታ ለማማጓጓዝ የስራ ተቋራጩ መቸገሩ ፣ የኮንስትራክሽ ፈንጂ እና የፈንጂ ተቀፅላዎች ማስገባት አለመቻል እንዲሁም በመንገዱ ክልል ውስጥ የተካተቱ ንብረቶች በወቅቱ አለመነሳት በግንባታው የሥራ ሂደት ላይ ተጽዕኖ አሳድረው ቆይተዋል፡፡ እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ የአትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከአካባቢው አስተዳደር እና ከማህበረሰቡ ጋር በመተባበር አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ በማድረጉ አሁን ላይ የተሻለ የፕሮጀክት አፈፃፀም የተመዘገበ ሲሆን ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ይጠበቃል፡፡ መንገዱ ሲጠናቀቅ በዋናነት የላሊበላ ፣ የኩልመስክ እና የሙጃ ከተሞችን በቅርበት የሚያስተሳስር ሲሆን ወደ ላሊበላ ፍልፍል አብያተ-ክርስቲያናት መዳረሻ በመሆን ለቱሪስቶች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የሚያግዝ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው የሚመረቱትን የዘንጋዳ ፣ የገብስ እና ባቄላ ውጤቶች ወደ ማዕከላዊ ገበያ በቀላሉ ለማድረስ ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የአካባቢውን ማህበረሰብ የኢኮኖሚ እንቀስቃሴ ያፋጥናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የአጋርፋ - አጋርፋ   ኮሌጅ  - አምቤንቱ  መንገድ  ሥራ  ፕሮጀክት በማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 3 ፣ 2017 ዓ.ም (ኢመአ):-  በኦሮሚያ   ክልል  ባሌ   ዞን  የአጋርፋ  ወረዳ  እና   አምቤንቱ  ቀበሌ    የሚያገናኘው   የአጋርፋ  - አጋርፋ  ኮሌጅ -  አምቤንቱ  የአስፋልት  ኮንክሪት  የመንገድ  ሥራ  ፕሮጀክት  እየተጠናቀቀ ይገኛል። ከመንገድ   ፕሮጀክቱ  ሥራ  95.85  በመቶ  የሚሆነው  የተገባደደ  ሲሆን ፣ ቀሪ  የማጠቃለያ  ስራዎችን  ለማከናወን   እየተሰራ  ነው። 15  ኪሎ  ሜትር  ርዝማኔ  ያለው  ይኸው  መንገድ  በከተማ   21.50  ሜትር ፣በቀበሌ  12  ሜትር  እንዲሁም በገጠር 10  ሜትር  የሚሆን  ስፋት  አለዉ። በግንባታው  የሥራ  ሂደት  ላይ  የአፈር  ስራ፣  የሰቤዝ  ስራ፣ የቤዝ ኮርስ፣ የአነስተኛ  የውሀ ማስተላለፊያ  ቱቦ ፣የስላብ  ከልቨርት  ስራዎች  እና  የ 12 ኪሎ ሜትር  አስፓልት  ንጣፍ  ሥራ  ሙሉ  በሙሉ  የተጠናቀቁ  ሲሆኑ   አሁን  ላይ   የድልድይ    ኮንክሪት    እንዲሁም  የማጠናቀቂያ   ስራዎች   በመከናወን  ላይ  ናቸው ፡፡ ግንባታውን   እያካሄደ   የሚገኘው   የስራ  ተቋራጭ  ቻይና  ኮሙኒኬሽን  ኮንስትራክሽን  ካምፓኒ  ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር  ስራውን   ደግሞ   ሆንግ   ኣይኬ  ከልደት  አማካሪ  ጋር   በጣምራ  በመሆን  እያከናወኑት  ይገኛል። ለመንገዱ  ግንባታ    የተመደበው 1,052,976,513 (አንድ  ቢሊዮን  ሃምሳ ሁለት ሚሊዮን  ዘጠኝ  መቶ  ሰባ ስድስት  ሺህ  አምስት  መቶ  አስራ  ሶሰት  ብር  ወጪ  የተሸፈነው   በኢትዮጵያ   መንግስት  ነው። የመንገዱ  መገንባት   አጋርፋ   ከተማን ፣ አጋርፋ  ኮሌጅን  እና  አምቤንቱ  ከተማን  በቅርበት  በማገናኘት የማህበራዊና  ኢኮኖሚያዊ  ትስስርን  ለማጠናከር  የሚያስችል  ነው። ከዚህም   ባሻገር   በአካባቢው   የሚገኙ  እንደ በርበሬ   እና  ገብስ  ያሉ  የግብርና  ውጤቶችን  ለገበያ  አንዲቀርቡ ለማድረግ  ያግዛል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጂጋ - ቋሪት - አርብ ገበያ - ሰከላ - ቲሊሊ ክፍል 2፡ አርብ ገብያ - ሰከላ - ቲሊሊ አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን አስፋልት ወደ ማንጠፍ ስራ ተሸጋገረ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2017 (ኢ መ አ):- በአማራ ክልል በምዕራብ ጎጃም የሚገኘው 62 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የአርብ ገበያ - ሰከላ - ቲሊሊ ክፍል ሁለት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አስፋልት የማንጠፍ ስራ ተጀመረ። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱን መነሻውን በምዕራብ ጎጃም አርብ ገበያ ላይ በማድረግ አዊ ዞን ቲሊሊ ከተማ ድረስ የሚዘልቅ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪውዎች እና የመስመሩ ተጠቃሚዎች የመሰረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ ይሰጣል። በእስካሁኑ የመንገድ ግንባታ ስራ እንቅስቃሴ የአስፋልት ንጣፍ ፣ የድልድዮች፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ፣ የስትራክቸር ፣ ሰብ ቤዝ እና ቤዝ ኮርስ ስራዎችን ጨምሮ በርካታ የስትራክቸር ሥራዎችን እየተከናወነ ይገኛል። ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 1,673,300,137.71/ አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ሰባ ሶስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሺ አንድ መቶ ሰላሳ ሰባት ብር ከ ሰባ አንድ ሣንቲም ብር የሚሸፈነው በፌደራል መንግስት ነው ። የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ዲ.ኤም.ሲ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ ኤስ.ጂ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ/የተ/የግ/ማ እያከናወነው ይገኛል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት መገንባቱ በአካባቢው ማህበረሰብ ኑሮና በኢኮኖሚው እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል። የመንገዱ መገንባት የጤና ፣ የትራንስፖርት እና የሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ተደራሽነትን ከማስፋፋቱም በተጨማሪ አርሶ አደሩምርቶቹን ወደ መሃል ገበያ በማውጣት ተጠቃሚ ያደርጋል። የግንባታው ሥፍራ ግሽ አባይ በተለይም የታላቁ አባይ ወንዝ መነሻ ከመሆኑም ባለፈ አካባቢው የበርካታ ታሪካዊ እና ጥንታዊ መስህቦች እንዲሁም የተለያዩ ገዳማት እና አብያተ-ክርስቲያናት መገኛ እንደመሆኑ ለጎብኚዎች ምቹ አጋጣሚን ይፈጥራል። መስመሩ ከደንበጫ - ሰቀላ - አዴት መንገድ የሚያገናኝ ሲሆን ወደ ባህር ዳር ለመጓዝም አማራጭ ሆኖ ከማገልገሉም ባሻገር ከአዲስ አበባ - ደብረማርቆስ - ባህር ዳር ዋና መንገድ ጋር የሚያገናኝ ነው። የግንባታው መጠናቀቅ ቋሪት፣ ሰከላ፣ ባንጃ እና ጓጉሳ ሽጉዳድ ወረዳዎችን እንዲሁም አርብ ገበያ፣ አቻኖ፣ አጃሌ፣ጎለምታ፣ አምቢሲ እና ጉንድል ቀበሌዎችን በአስፋልት ኮንክሪት መንገድ የሚያገናኝ ይሆናል። የመንገድ ግንባታው በወረዳ ከተማ 21.5 ሜትር፣ በቀበሌ 12 ሜትር እና በገጠር ሜዳማ ቦታዎች 10 እንዲሁም ተራራማ ቦታዎች ላይ 8 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው እየተገነባ ያለው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከአገር በቀል የስራ ተቋራጮች ጋር ውይይት አካሄደ አዲስ አበባ፣ የካቲት 28 ፣ 2017 (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በአገር በቀል ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ዘርፍ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን እንዲሁም የቀጣይ መፍትሄና አካሄዶችን አስመልክቶ ከአገር በቀል የስራ ተቋራጮች ጋር ውይይት አካሂዷል። በውይይት መድረኩ የኢፌዲሪ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ማኒስትር ድኤታ አቶ የትምጌታ አስራት ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን ፣ ሌሎች የፌዴራል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ ሀገር በቀል የስራ ተቋራጭ ድርጅት ባለቤት እና ስራ አስኪያጆች እና ከኢትዮጵያ መሃንዲሶች ማህበር የተውጣጡ እንግዶች ተሳትፈዋል፡፡ በባለፋት ዓመታት ሲያጋጥሙ የነበሩ አለምአቀፍና ሀገር አቀፍ ተፅዕኖዎች በመንገድ ግንባታ ዘርፉ ላይ ተፅዕኖ ሲያሳድሩ ስለመቆየታቸው በመድረኩ ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። አሁን ላይ ዘርፉን እየፈተኑ ይገኛሉ ተብለው በጥናታዊ ፅሁፉ ከቀረቡ ተፅዕኖዎች መካከል የፀጥታ ችግር ፣ የወሰን ማስከበር ፣ የኮንስትራክሽን ቁሳቁሶች እና ማሽነሪዎች ዋጋ መጨመር ፣ የአንዳንድ የስራ ተቋራጮች ደካማ ፕሮጀክት አስተዳደር ችግር እና የክፍያ እጥረት በዋንነኛነት የሚጠቀሱ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በእነዚህ ጫናዎች ምክንያት የግንባታ ሂደት መዘግየት ፣ የዋጋ ልዩነት መፈጠር ፣ የጥራት ችግሮች መስተዋል ፣ በኮንትራት ሂደት ላይ የሚያተኩሩ የህግ ክርክሮች መፈጠር እና የፕሮጀክት መቋረጥ ሂደቶች እየተስተዋሉ ስለመሆናቸው ታውቋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከተለያዩ የመስተዳድር ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በርካታ ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ በመሆኑ ከዚህ ቀደም ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮች አሁን ላይ በከፊል እየተቀረፉ ስለመሆናቸው በሰነዱ ቀርቧል። ኢመአ በስራ ተቋራጮች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በአግባቡ ፈትሾ ለውይይት ማቅረቡ የሚያስመሰግነው ስለመሆኑ አስተያየታቸውን የሰጡ የስራ ተቋራጮች ተጨማሪ ያሏቸውን አስተያየቶችም ገልፀዋል። በዘርፉ ከዋጋ ግሽበት ፣ የፀጥታ ፣ የክፍያ ፣ የታክስ ፣ የወሰን ማስከበርና የመሳሰሉ ዘርፈ ብዙ ተግዳሮቶች እየፈተኑን በመሆኑ የሚመለከተው የመንግስት አካላት አፋጣኝ መፍትሄ ሊሰጠን ይገባል ሲሉ የስራ ተቋራጮቹ ጠይቀዋል ። በወቅቱ በከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ የትምጌታ አስራት እና በኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን የማጠቃለያ ሃሳቦች ተሰጥተዋል። አሁን ላይ እየተስተዋሉ ያሉ ችግሮች የአንድ ወገን ብቻ አለመሆናቸውን በመገንዘብና ሁላችንም ራሳችንን በመፈተሽ እየተስተዋሉ ያሉ ችግሮችን በጋራ ልንቀርፍ ይገባል ሲሉ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን ገልፀዋል፡፡ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ የትምጌታ አስራት በበኩላቸው በከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ደረጃ ሊቀረፉ የሚችሉ ጉዳዮችን ለመቅረፍ ከዛሬ ጀምሮ እንቅስቃሴ ይደረጋል ያሉ ሲሆን ፣ መንግስት ዘርፉን ለማጠናከር በርካታ ስራዎች እየሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads